A place to learn English easily.
Owner - @Samson_G
Buy ads: https://telega.io/c/English_Ethiopian
Last updated 3 months, 2 weeks ago
NGO, የመንግስት እና የግል ድርጅቶች የስራ ማስታወቂያ እና ነፃ የትምህርት እድሎችን ያገኛሉ ቤተሰበ ይሁኑ ሌሎችንም ይጋብዙ
ለማስታወቂያ @Human133 ላይ አናግሩን
We need promoters
Website: www.abayjobs.com
Facebook: https://www.facebook.com/abayjobs12
Last updated 2 months ago
Today after megrib we will have meftahu tejweed program insha Allah!!!
﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)
"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)
اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد
Today after megrib we will have sefenetu neja dress program insha Allah!!
*? የግቢ(ዩንቨርስቲ) ፈተናውና መፍትሄው*
? ክፍል አንድ
ቢስሚላህ አልሃምዱሊላህ
እንደሚታወቀው ግቢ ላይ ፆታዊ የስሜት ፈተናዎች ይበዛሉ በተለይ ግቢ ከመግባታቸው በፊት ጠንካራ ማንነት የሌላቸው ልጆች በፍጥነት ከአለባበሳቸው ጀምሮ ሁኔታቸው ሲቀየር ይታያል። ምክንያቱም ቤተሰብጋ እያሉ ለቤተሰብ ብለው ከወንጀል ይርቃሉ ወደ ግቢ ሲሄዱ ግን አላህን ለማትፈራ ነፍስ ሁሉም ነገር መንገዱ ምቹ ይሆንላታል። በፊት ቁጥብ የነበሩት ለአላህ ብለው ቢሆን ግን አቋማቸው አይቀየርም ነበር። ለዛም ነው አንዳንዶች ግቢ ሲገቡ ከቤተሰብጋ እያሉ ኒቃብ የተከለከሉ ኒቃባቸውን ይለብሳሉ። በተቃራኒው ደግሞ ነፃነት ያገኙ መስሏቸው ሱሪ መልበስና ከወንዶች ጋር እንደፈለጉ ይሆናሉ። ከዛም ካንዱ የስሜት አሳዳጅ ከሆነ ወንድ እጅ ላይ ትወድቅና ህይወቷ ይመሰቃቀላል። አዎ አላህን በመፍራታችንና የአላህን ትእዛዝ በመጠበቃችን ተጠቃሚዎች ራሳችን ነን። በተቃራኒው የደስታ መንገድ መስሎን ስሜቷን የምትከተል ነፍስ ግን በየአቅጣጫው የሚያጠፋት ይከባታል።
ነገር ግን እኔ እንደ ወንድም ባጭሩ መሰረታዊ ብየ ማስታወስ የምፈልገው ነገር ትክክለኛ ቋሚ የሆነን ደስታ ከፈለግን፦ አለባበሳችንን እናስተካከል፣ ቂርአት(ኪታባችንን እንድንቀራ /አቂዳችንን እንድናስተካከልና እንድናጠራ)፣ ከመጥፎ ጓደኞች እንድትርቁና ከፆታዊ ፈተና ራሳችሁን እንድታርቁ ነው። እነዚህን መንገዶች ከተጠነቀቃችሁ ከብዙ ፈተናዎች ትድናላችሁ በአላህ ፍቃድ።
በተለይ ፆታዊ ፊተና ላይ ራሳችንን እንጠብቅ ብዙ የገጠሙኝ ልጆች አሉ በግቢ(በዩንቨርስቲ)ህይወታቸው ላይ ዚና ላይ የወደቁ ነገር ግን ሁሉም ማለት ይቻላል መጨረሻው ተለያይተዋል። ምክንያቱም ለስሜታቸው ብቻ ነው የሚፈልጓቸው። ሴቶችም ኢማናቸው ደካማ በመሆኑ በተለያዩ ጥቅማጥቅምና በውሸት የዕዝነት ቃላቶች ይምበረከካሉ። የሚያሳዝነው መጨረሻ ላይ ነው ተጠቅመውባቸው ሲሄዱ የሚባንኑት። እኛ ደግሞ ካለፉት ትምህርት ልንወስድ ይገባል።!
?አንዳንዶች ግቢ እስክንወጣ ጊዜያዊ ኒካህ ቤተሰብ ሳያውቅ እንሰር ይፈቀዳል በማለት የማያውቁ እህቶች ላይ ሊጫወቱ ይሞክራሉ። ይሄ መንገድ አይቻልም ዚና ነው። አላህን እንፍራ።!ራሳችንን እንጠብቅ።
? ከላይ በትንሹ ልጅቷ እየመጣባት ያለውን ፈተና ነው የተናገረችው። ያው ግቢ ላይ የሴትን ስልክ ማግኘት ቀላል ነው። ነገር ግን በተለይ ስልክ ስለሆነ ብዙ ፈተናና መግባባቶች ከዛም አልፎ የዚናን በር የሚያፋጥነው።
ስለዚህ ሴቶች ምንም አይነት መልእክት አትመልሱ ሰላማችሁን መጠበቅ ከፈለጋችሁ ይሄን አድርጉ። ፁሁፍ(ቴክስት)አለመመለስ ብቻ በቂ መፍትሄ አይደለም ብሎክም አድርጉ እስከመጨረሻው። አሰላሙአለይኩም የሚል እንኳ መልእክት ቢልኩላችሁ ለአላህ ሰላምታ ለምን አልመልስም ብላችሁ እንዳታስቡ ሳትፅፈሁ ሰላማታውን በምላሳችሁ መልሳችሁ ብሎክ ልታደርጉ ይገባል። አሁንም ደግሜ የምነግራችሁ ነገር አለመመለሳችሁ ብቻ መፍትሄ አይደለም የግድ ብሎክ ማድረግ አለባችሁ በተለያዩ ቁጥሮችም ሊፅፉላችሁ ይችላሉ እስከመጨረሻው ብሎክ አድርጉ። በስልክም ቢሆን አዲስ ቁጥር አታንሱ ወይም የቤተሰብ መስሏችሁ ድንገት ካነሳችሁት ወንድ መሆኑን ካወቃችሁ ዝጉት መዝጋታችሁም ብቻ መፍትሄ አይደለም ብላክ ሊስት አስገቡ ቁጥራቸውን።!
?ክፍል ሁለት ይቀጥላል?
(አላህ የላቀና ይበልጥ አዋቂ ነው)
መልእክቱን በምንችለው ሼር እናድርገው ለአንድ ሰው የመመለሰ ሰበብ መሆን ትልቅ ነገር ነው። ባረከላሁ ፊኩም!
✍ወንድማችሁ ሙሂዲን ሰኢድ
? የላኢላሀ ኢለላህ መስፈርቶች?
ላኢላሀ ኢለላህ የሚለው የምስክርነት ቃል ስምንት መስፈርቶች አሉት። እነሱም፡-
?1- ማወቅ፤
?2- እርግጠኝነት፤
?3- ፍጹምነት፣
?4- እውነተኝነት፤
?5- መውደድ፤
?6- መታዘዝ፣
?7- መቀበልና
?8- ከአላህ ውጭ በሚመለኩ ነገሮች መካድ ናቸው።
?የእነዚህ መስፈርቶች ዝርዝርና ማብራሪያ፦
▫️1-ማወቅ የሚለው መስፈርት፡-
ላኢላሀ ኢለላህ የሚለው የምስክርነት ቃል የሚያስረዳውን የማንሳትና የማፅደቅ(አሉታዊና አዎንታዊን) ትርጉም አውቆ በተግባር ላይ ማዋል ማለት ነው።
?አላህ እንዲህ ይላል፡-
{ فَاعْلَمْ أَنَّهُ لا إِلَهَ إِلا اللَّهُ } محمد: (19)
“እነሆ ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚገዙት አምላክ አለመኖሩን እወቅ” ( ሙሐመድ፡19)
▫️2- እርግጠኝነት የሚለው መስፈርት፦
ከአላህ ሌላ በሀቅ የሚገዙት አምላክ የለም የሚለውን የተውሒድን ቃል በእርግጠኝነት መናገር ማለት ነው።
? አላህ እንዲህ ይላል፡-
{ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ الَّذِينَ آمَنُوا بِاللَّهِ وَرَسُولِهِ ثُمَّ لَمْ يَرْتَابُوا وَجَاهَدُوا بِأَمْوَالِهِمْ وَأَنْفُسِهِمْ فِي سَبِيلِ اللَّهِ أُولَئِكَ هُمُ الصَّادِقُونَ} ( الحجرات:15)
“ ትክክለኛ አማኞች እነዚያ በአላህ እና በመልእክተኛው ያመኑና ከዚያም በእምነታቸው ያልተጠራጠሩ በገንዘቦቻቸውና በነፍሶቻቸውም በአላህ መንገድ ላይ የሚታገሉ ናቸው። እነዚያ እነርሱ እውነተኛ አማኞች ናቸው” (አል-ሁጁራት፡15)
▫️3-ፍፁምነት የሚለው መስፈርት ሊረጋገጥ የሚችለው የአምልኮ ዓይነቶች በሙሉ ለአላህ ብቻ ሲውሉ ነው።
? አላህ እንዲህ ይላል፡-
{وَمَا أُمِرُوا إِلَّا لِيَعْبُدُوا اللَّهَ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ حُنَفَاءَ} (البينة :5)
“ቀጥተኞች እና ኃይማኖትን ፍፁም ለአላህ ብቻ አድርገው ሊገዙት እንጂ አልታዘዙም” ( አል-በይነህ: 5)
▫️4- እውነተኝነት ማለት የተውሂድን የምስክርነት ቃል( ላኢላሀ ኢለላህን) በምላሱ ሲናገር በልቡ አምኖ መናገር ማለት ነው።
? አላህ እንዲህ ይላል :
{ الم (1) أَحَسِبَ النَّاسُ أَنْ يُتْرَكُوا أَنْ يَقُولُوا آمَنَّا وَهُمْ لا يُفْتَنُونَ (2) وَلَقَدْ فَتَنَّا الَّذِينَ مِنْ قَبْلِهِمْ فَلَيَعْلَمَنَّ اللَّهُ الَّذِينَ صَدَقُوا وَلَيَعْلَمَنَّ الْكَاذِبِينَ}(العنكبوت :1-3).
“ሰዎች ሳይፈተኑ /ሳይሞከሩ አምነናል በማለታቸው ብቻ የሚተዉ መሰላቸውን? ከእነሱ በፊት የነበሩትን በእርግጥ ፈትነናቸዋል አላህ እነዚያን እውነተኞችንና ሀሰተኞችን ለይቶ ያውቃል” ( አል-ዐንከቡት: 1-3 )።
▫️ 5- መውደድ የሚለው መስፈርት ላኢላሀ ኢለላህ የሚለውን የምስክርነት ቃል ሲናገር አላህንና መልእክተኛውን፤ የቃሏን መልእክትና ትርጉም በልቡ ወዶ መናገር ማለት ነው።
?አላህ እንዲህ ይላል፡-
{ وَمِنَ النَّاسِ مَنْ يَتَّخِذُ مِنْ دُونِ اللَّهِ أَنْدَادًا يُحِبُّونَهُمْ كَحُبِّ اللَّهِ وَالَّذِينَ آمَنُوا أَشَدُّ حُبًّا لِلَّه } ( البقرة :165)
“ከሰዎችም እንደ አላህ አድርገው የሚወዷቸው የሆኑ ጥዖታትን የሚገዙ አሉ እነዚያ ያመኑትም አላህን ከማንኛውም በላይ ይወዳሉ” (አልበቀረህ- 175)።
▫️6- መታዘዝ የሚለው መስፈርት፦
አላህን ብቻ መገዛትና ለሕጉ ታዛዥ መሆን ማለት ነው።
? አላህ እንዲህ ይላል.፡-
{ وَأَنِيبُوا إِلَى رَبِّكُمْ وَأَسْلِمُوا لَهُ } : الزمر: 54)
“ወደ ፈጣሪያችሁም ተመለሱ ለእሱም እጅ ስጡ” ( አዙመር: 54)
▫️ 7- መቀበል የሚለው መስፈርት፦
የምስክርነት ቃሏንና መልእክቷን ከልቡ አምኖ መቀበል ማለት ነው ይህም የሚረጋገጠው ከአላህ ውጭ የሚመለኩ ነገሮችን ትቶ አላህን ብቻ በመገዛት ነው ።
▫️ 8- ከአላህ ውጭ በሚመለኩ ነገሮች መካድ የሚለው መስፈርት ደግሞ ከአላህ ሌላ የሚመለኩ ነገሮች በሙሉ የውሸት አማልክት መሆናቸውን አውቆና አምኖ እነሱን ከመገዛት መፅዳትና መራቅ ማለት ነው።
?አላህ እንዲህ ይላል፡-
{ فَمَنْ يَكْفُرْ بِالطَّاغُوتِ وَيُؤْمِنْ بِاللَّهِ فَقَدِ اسْتَمْسَكَ بِالْعُرْوَةِ الْوُثْقَى لا انْفِصَامَ لَهَا وَاللَّهُ سَمِيعٌ عَلِيمٌ } البقرة: 256)
“በጣዖትም የካደና በአላህ ያመነ ለእርሷ መበጠስ የሌላትን ጠንካራ ዘለበት በእርግጥ ጨበጠ(ያዘ)። አላህም ሰሚና አዋቂ ነው” (አል-በቀረህ: 256) ።
⚠️ማሳሰቢያ
✧ አንድ ሰው እነኝህን መስፈርቶች ሳያረጋግጥና ሳያሟላ በአንደበቱ ብቻ ላኢላሀ ኢለላህ ማለቱ ተጠቃሚ አያደርገውም።
©
Today's meftahu tejweed program is as scheduled.
Today's tajweed program is as scheduled.
የሰላም ጊዜ ዒባዳ፣ የምቾት ጊዜ ወደ አላህ መቅረብ ከፈተና መውጫ ሰበብ፣ ከጭንቅ መገላገያ መሳሪያ ነው። የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ይላሉ፦
احفظِ اللهَ يحفظْك ، احفظِ اللهَ تجدْه أمامَك ، تعرَّفْ إلى اللهِ في الرخاءِ يعرفُك في الشدَّةِ
"አላህን ጠብቅ፣ ይጠብቅሃል። አላህን ጠብቅ፣ ፊት ለፊትህ ታገኘዋለህ። በድሎት ጊዜ ወደ አላህ ተዋወቅ። በፈተና ጊዜ ያውቅሃል።"
አላህን ትእዛዙን በመጠበቅ፣ ክልከላውን በመራቅ ጠብቀው። ከጉዳት፣ ከክፋት፣ ከሸይጧን፣ ከነፍሲያ ክፋት ይጠብቅሃል። በምቾትህ ጊዜ ለትእዛዙ በማደር ወደሱ ተዋወቅ። በመከራህ ጊዜ ይደርስልሃል። የላቀው አላህ ባህር ውስጥ ተጥለው ዓሳ ስለዋጣቸው ነብዩ ዩኑስ እንዲህ ይላል:-
﴿فَلَوۡلَاۤ أَنَّهُۥ كان من ٱلۡمُسَبِّحِینَ * لَلَبِثَ في بَطۡنِهِۦۤ إلى يوم یُبۡعَثُونَ﴾
"እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤ እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር።" [አሷፋት፡ 143-144]
ዚክር ጋሻ ነው። ዚክር መድህን ነው። ኢብኑ መስዑድ ረዲየሏሁ ዐንሁ እንዲህ ይላሉ፦
ما كُرِب نبيٌ من الأنبياء إلا استغاث بالتسبيح .
"ከነብያት አንድም ነብይ ጭንቅ ላይ አልወደቀም፣ በተስቢሕ (ጌታውን) እርዳታ የጠየቀ ቢሆን እንጂ።"
"ሱብሓነላሂ ወቢሐምዲሂ፣ ሱብሓነላሂል ዐዚም"
منقول
Today after megrib we will have meftahu tejweed kitab program.
Today after megrib we will have meftahu tejweed kitab program.
A place to learn English easily.
Owner - @Samson_G
Buy ads: https://telega.io/c/English_Ethiopian
Last updated 3 months, 2 weeks ago
NGO, የመንግስት እና የግል ድርጅቶች የስራ ማስታወቂያ እና ነፃ የትምህርት እድሎችን ያገኛሉ ቤተሰበ ይሁኑ ሌሎችንም ይጋብዙ
ለማስታወቂያ @Human133 ላይ አናግሩን
We need promoters
Website: www.abayjobs.com
Facebook: https://www.facebook.com/abayjobs12
Last updated 2 months ago