በዝረቱል ኸይር የተርቢያ ማዕከል

Description
ይህ ቻናል ልጆቻችንን በተርቢያ ለማሳደግ የሚጠቅሙ ጉዳዮች የሚዳሰሱበት ቻናል ነው።
ለሃሳብ አስተያየት እና በአስተዳደግና ተያያዥ ጉዳዮች ማማከር ለምትፈልጉ @Bezretulkheyrterbiya ያናግሩን።
አድራሻ፡ እንቁላል ፋብሪካ ገተር ሕንጻ 3ኛ ፎቅ 303B
0913993130
We recommend to visit

Welcome To Amharic films Best Place To find Amharic Movies

አዳዲስ እና የድሮ አማርኛ ፊልሞችን እና አማርኛ ተከታታይ ድራማዎችን ለማግኝት ቻናላችንን Join ይበሉ ።
Share:- @Amharic_Films

ለማስታወቂያ - @Abusheymc & @Alpha6249

Buy ads: https://telega.io/c/Amharic_films

Last updated 1 year, 8 months ago

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @Aymu_xo

Last updated 3 weeks, 1 day ago

╔╦╦═╦╔╦═╦═╦═╗
║ እንኳን ደህና መጡ | |
╚══╩═╩═╩╩╩╩═╝
➟ እንኳን ወደ ትልቁ የሊቨርፑል ( መርሲሳይድ) ቻናል በደህና መጡ ።
◉ ስለ ሊቨርፑል ◉
? ዝውውሮች

? ውጤቶች

? የጨዋታ ፕሮግራሞች

? እንዲሁም የተጨዋቾች ግለ ታሪክ

? ጨዋታዎችን በቀጥታ ወደናንተ የምናደርስ ይሆናል።

Owner:- @hackersolo0⭐️

Last updated 2 months, 2 weeks ago

1 month, 1 week ago

ለልጆችዎ ጥፋት ምላሽ ከመስጠትዎ በፊት እነዚህን ጥያቄዎች ይመልሱ፦
1. ተግባሩ ጥፋት ነው ወይስ በወቅቱ ስላናደዶት ብቻ ነው?
2. ልጆቹ ጥፋቱን ያጠፉት ሆን ብለው ነው ወይስ በድንገት ነው?
3.ያጠፉትን ጥፋት ልጆቹ በራሳቸው ማረም ይችላሉ ወይስ የኛን ጣልቃ መግባት ይፈልጋል?
4.በሰዓቱ ምላሽ ለመስጠት የተረጋጋ ስሜት ላይ ኖት ወይስ ጊዜ ይፈልጋሉ?
እነዚህን ጥያቄዎች ቆም ብለን ማሰባችን ለድርጊቱ የምንሰጠው ምላሽ ተገቢ እንዲሆንና ልጆቹን ከጥፋታቸው እንዲታረሙ ለማድረግ ያግዘናል።
https://t.me/bezretulkheyr

1 month, 2 weeks ago

ኃላፊነት የሚሰማው  አባት :-👉ከሁሉም ቅድሚያ የተፈጠረበትን አላህን በብቸኝነት የመገዛት ዓላማ ጠንቅቆ ያውቃል
👉 ትክክለኛ አርዓያውን ለይቶ የሚያውቅና የሚከተልም ነው
لَّقَدْ كَانَ لَكُمْ فِي رَسُولِ اللَّهِ أُسْوَةٌ حَسَنَةٌ لِّمَن كَانَ يَرْجُو اللَّهَ وَالْيَوْمَ الْآخِرَ وَذَكَرَ اللَّهَ كَثِيرًا
ለእናንተ አላህንና የመጨረሻውን ቀን የሚከጅል ለሆነ ሰው፣ አላህንም በብዙ ለሚያወሳ በአላህ መልዕክተኛ መልካም መከተል አልላችሁ፡፡(33፡21)
👉 የተሰጠውን ቤተሰቡን የማስተዳደር ኃላፊነት በአግባቡ ይወጣል
👉 ለቤተሰብ ስኬት መሪው ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው የሚረዳና የመሪነት ኃላፊነቱን በአግባቡ የሚወጣ ነው
👉 የቤተሰቡ መከታና ጋሻም ነው።
👉በእያንዳንዱ ተግባሩ በእውቀትና በማስተዋል ለመጓዝ ጥረት ያደርጋል
👉 ንግግሩና ተግባሩ ልጆቹ ላይ ያለውን ተጽዕኖ ጠንቅቆ ያውቃልና መልካም አርዓያ ለመሆን ይጥራል
👉ለቤተሰቡ ጊዜን ይሰጣል
👉እንደ ፍጹም ወላጅ ሳይሆን ከስህተት እንደማይነጻ ማንኛውም ሰው ለስህተቱ ኃላፊነት የሚወስድናና ይቅርታንም የሚጠይቅ ነው።
👉የልጅ አባት የመሆንን ኒዕማ እንደ ትልቅ እድል ተጠቅሞ ኃላፊነቱን በአግባቡ ለመወጣት ይጥራል
👉በእያንዳንዱ እንቅስቃሴው የአላህ እርዳታ ካልታከለበት ከንቱ እንደሆነ ያውቃልና ሁሌም ነገራቶችን ወደ ጌታው ከማስጠጋትና እሱን ከመለመን አይዘናጋም
أَلَا كُلُّكُمْ رَاعٍ وَكُلُّكُمْ مَسْئُولٌ عَنْ رَعِيَّتِهِ
<ሁላችሁም እረኛ ናችሁ በጠበቃችሁትም ትጠየቃላችሁ>
https://t.me/bezretulkheyr

1 month, 2 weeks ago
**ሁሉም በእድሜ ነው!**

ሁሉም በእድሜ ነው!
ልጆቻችንን እያንዳንዱ እንቅስቃሴያቸውን በመቆጣጠር የጨዋታ ጊዜ እንኳን እንዳይኖራቸው ማድረግ፣እንዲፈጽሙ ምንፈልገውን ተግባር በኛ ፍጥነት እንዲያደርጉት መጠበቅ፣በነገራቶች ላይ ከእድሜያቸው በላይ እንዲፈጽሙ መጠበቅ...የመሳሰሉት ተግባራት ተዋህዶን መኖር ከጀመረ ሰነባብቷል ፤ምናልባትም የየዕለት ተግባራችን ከመሆኑ የተነሳ ስህተት መሆኑንም ልብ ላንለው እንችላለን።
ልጆቻችንን ከአቅማቸው በላይ ስናቻኩላቸው፦
👉 ለጭንቀት ተጋላጭ ይሆናሉ
👉 በእድሚያቸው ማጣጣም ያሉብንን ትውስታዎች ያልፋሉ
👉 ከወላጅ ጋር ሊኖር የሚገባ ቁርኝት እንዳይኖር ያደርጋል
📌ውድ ወላጅ! እኛ ልጅነታቸውን ሳንረዳ በኛ ልክ ፍጥነት እየጠበቅን ምናልባትም ለሚፈልጉት ነገር ትዕግስት ማጣታቸው ሊገርመን አይገባም!
ስለዚህ ልጆችን በልጅነታቸው ልክ ዝቅ ብሎ መረዳትና በተግባራቸው ውስጥ ትዕግስት ልንላበስ ይገባል፤አላህ ያግዘን

https://t.me/bezretulkheyr

1 month, 2 weeks ago

ከመፍረድ መረዳት፤ከመታገል በጥበብ መያዝ!
ጉርምስና እድሜ ላይ የደረሱ ልጆች ቅሬታ፦ ቤተሰብ አይረዳንም፣የራሳቸውን ስሜት ብቻ ነው የሚያዳምጡት...
የወላጆቻቸው ስጋት፦ ባህሪያቸው ከባድ ነው፣ለጓደኛ የሚሰጡት ቦታ፣የሚባሉትን አይሰሙም፣የተጋረጠባቸው ፈተና ብዛት...
👉 ወላጅነት የውድድር ሜዳ አይደለም ልጆች ከአላህ የተሰጡን ኃላፊነቶች ናቸውና ቅናቻውን መንገድ ይመሩ ዘንድ የአቅማችንን ጥረት የምናደርግበት እንጂ የበላይነታችንን የምናሳይበት ስልጣን አይደለም።
👉እዚህ እድሜ ላይ በአብዛኛው ጎልቶ የሚታየው ወላጅም ኑ ወደ እኔ ፤ ልጅም ኑ ወደኔ አይነት መልዕክት ያለው በአጠቃላይ ገመድ ጉተታ የሚመስል ሁኔታ ነው።
ውድ ወላጅ! በየትኛውም እድሜ ያሉ ልጆችን ለማሳደግ ዋነኛ ከሚባሉት ውስጥ አንዱ ልጆችን የመረዳት ጥበብ ነው፤ የእድሜ ነገር ሆኖ ያሉበት ተጨባጭ እየገባቸው አይደለምና ካለእድሜያቸው ወደኛ ከመጎተት ይልቅ ወደ እነሱ ዝቅ ብለን ፍርጃ ባልተቀላቀለበት ቀረቤታ ከጎናቸው በመሆን መንገድ እንዳይስቱ በጥበብ ይዘን ልናግዛቸው እንጂ ይበልጥ እልህ ውስጥ እየከተትን ወደማይሆን አቅጣጫ ለመብዘንበላቸው ምክንያት ልንሆን አይገባም!
ከምንም በላይ ለእያንዳንዱ ጉዞዋችን ስንቅ የሚሆነን ወደ አላህ ማስጠጋቱ ነውና በዱዓ እንበርታ!

**يُؤْتِي الْحِكْمَةَ مَن يَشَاءُ ۚ وَمَن يُؤْتَ الْحِكْمَةَ فَقَدْ أُوتِيَ خَيْرًا كَثِيرًا ۗ وَمَا يَذَّكَّرُ إِلَّا أُولُو الْأَلْبَابِ

ለሚሻው ሰው ጥበብን ይሰጣል፤ ጥበብንም የሚስሰጥ ሰው ብዙን መልካም ነገር በእርግጥ ተሰጠ፡፡ የአእምሮዎች ባለቤቶች እንጂ (ሌላው) አይገሰጽም፡፡(2፡269)**
https://t.me/bezretulkheyr

1 month, 2 weeks ago
ለመመዝገብ [@Bezretulkheyrterbiya](https://t.me/Bezretulkheyrterbiya) ያናግሩን።

ለመመዝገብ @Bezretulkheyrterbiya ያናግሩን።

1 month, 2 weeks ago
**በቀን ውስጥ ምን ያህል ጊዜ ልጆችዎን …

በቀን ውስጥ ምን ያህል ጊዜ ልጆችዎን በአሉታዊ ቅጥል ስም ይጠሯቸዋል?
ደርቅ፣ቀጮ፣ባሪች፣ድንች፣ልበ ቢስ፣አሮጊቴ፣ሼባው፣ሰነፍ፣ፈዛዛና የመሳሰሉትን አይነት ቃላቶች ለልጆቻችን መጠቀም የተለመደና ምናልባትም ከመላመዳችን የተነሳ እየተጠቀምነው እንዳለን በራሱ ላናስተውለው እንችላለን።
ተጽዕኖው፦
👉 የሰጠናቸው ስያሜ ከባህሪ ጋር ከተቆራኘ እየተባባሰ ይሄዳል
👉 የማንነታቸው አካል ሊያደርጉትና ለራሳቸው ዝቅተኛ አመለካከት እንዲኖራቸው ያደርጋል
👉 አዲስ ነገር መሞከር የሚፈሩና ያለመቻል ስሜት ሊሰማቸውም ይችላል
👉 ትክክለኛ አቅማቸውን የማያውቁና የራሳቸውን ማንነት ያልተረዱም ሊሆኑ ይችላሉ
👉 የሰው ልጅ ሚያውቀውን ነውና የሚያደርገው ሌሎችን ተቺና ተሳዳቢም ሊሆኑ ይችላሉ
**አስተውሉ! የልጆችዎን ባህሪና ማንነታቸውን መለየት ይልመዱ፤ልጆችዎ ስህተታቸውን አይደሉምና አሉታዊ ስያሜ በመስጠት ስህተታቸው የነሱ መገለጫ ከማድረግ ይልቅ ባህሪውን ማስተካከል ላይ ያተኩሩ!

يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا لَا يَسْخَرْ قَوْمٌ مِّن قَوْمٍ عَسَىٰ أَن يَكُونُوا خَيْرًا مِّنْهُمْ وَلَا نِسَاءٌ مِّن نِّسَاءٍ عَسَىٰ أَن يَكُنَّ خَيْرًا مِّنْهُنَّ ۖ وَلَا تَلْمِزُوا أَنفُسَكُمْ وَلَا تَنَابَزُوا بِالْأَلْقَابِ ۖ بِئْسَ الِاسْمُ الْفُسُوقُ بَعْدَ الْإِيمَانِ ۚ وَمَن لَّمْ يَتُبْ فَأُولَٰئِكَ هُمُ الظَّالِمُونَ

እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ወንዶች ከወንዶች አይቀልዱ፡፡ ከእነርሱ የበለጡ ሊኾኑ ይከጀላልና፡፡ ሴቶችም ከሴቶች (አይሳለቁ)፡፡ ከእነርሱ የበለጡ ሊኾኑ ይከጀላልና፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታነውሩ፡፡ በመጥፎ ስሞችም አትጠራሩ፡፡ ከእምነት በኋላ የማመጽ ስም ከፋ፡፡ ያልተጸጸተም ሰው እነዚያ እነርሱ በዳዮቹ ናቸው፡፡(49:11)**
https://t.me/bezretulkheyr

1 month, 2 weeks ago
በዝረቱል ኸይር የተርቢያ ማዕከል
1 month, 3 weeks ago

ስነ ምግባር በተግባር!
የሰውን እቃ ሳያስፈቅዱ መንካት፣የሰውን መብት አለማክበር፣ድንበር አለመጠበቅና የመሳሰሉትን ባህሪዎችን "ወይ የዘንድሮ ልጅ" ብሎ ከመፍረድ ባሻገር ምናልባት የኛ አስተዋጽዖ ሊኖረው ይችላልና ቆም ብሎ እራስን መገምገም አንዱ መፍትሔ ነው!
👉ልጆች የሌላውን ድንበር እንዲያከብሩ ከልጅነታቸው ጀምሮ በእድሜያው ልክና አግባብ በሆነ መልኩ ልናስተምራቸውና የነሱንም መብት ልንጠብቅላቸው ይገባል። ለምሳሌ ክፍላቸው ስንገባና የራሳቸው ብለን የሰጠናቸው ንብረት ላይ ክብርን ማሳየት ያስፈልጋል።(መከታተላችንና የመምራት ኃላፊነታችን እንደተጠበቀ ነው)

**يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا لِمَ تَقُولُونَ مَا لَا تَفْعَلُونَ
كَبُرَ مَقْتًا عِندَ اللَّهِ أَن تَقُولُوا مَا لَا تَفْعَلُونَ

እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የማትሠሩትን ነገር ለምን ትናገራላችሁ?
የማትሠሩን ነገር መናገራችሁ አላህ ዘንድ መጠላቱ ተለቀ፡፡(ሱረቱ ሰፍ 2-3)**
https://t.me/bezretulkheyr

1 month, 3 weeks ago

ማስታወሻ
وَالَّذِينَ آمَنُوا وَاتَّبَعَتْهُمْ ذُرِّيَّتُهُم بِإِيمَانٍ أَلْحَقْنَا
بِهِمْ ذُرِّيَّتَهُمْ وَمَا أَلَتْنَاهُم مِّنْ عَمَلِهِم مِّن شَيْءٍ ۚ كُلُّ امْرِئٍ بِمَا كَسَبَ رَهِينٌ

እነዚያም ያመኑትና ዝርያቸውም በእምነት የተከተለቻቸው ዝርያቸውን በእነርሱ እናስጠጋለን፡፡ ከሥራቸውም ምንም አናጎድልባቸውም፡፡ ሰው ሁሉ በሠራው ሥራ ተያዢ ነው፡፡(ሱረቱ ጡር፡21)
https://t.me/bezretulkheyr

1 month, 3 weeks ago

ልጆት ሲያለቅስ በጣም ይረብሻል፣ሱቅ ይዘውት ቢሄዱ ያስቸግራል፣የሚፈልገው ነገር ካልተሰጠው መሬት ላይ ፍርፍር ብሎ ያለቅሳል፣ሲናደድ እራሱን ይቧጭራል፣ሰው ላይ ይታፋል፣ይናከሳል... ማለት ሁሉ ነገረ አከተመለት ማለት አይደለም!
👉 በልጅነት እድሜ ስሜትን የመግዛት ክህሎት አይዳብርም፣አዕምሯቸው ገና እድገት ላይ ነው፣ይህ በወላጅነት ጉዞ ላይ ከሚገጥሙ አንዱ ተግዳሮት እንጂ እርሶ ላይ ብቻ የተከሰተ አይደለም...
እናም ውድ ወላጅ ይህን እውነት ከመቀበል ጋር ልጅዎ እንዲህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ሲሆን የሚሰጡት ምላሽ ወሳኝ ነው!
እንደወላጅ ምላሻችን ምን ይሁን?
🔸 በጩኸት፣በዱላ፣በግብግብ በሃሪው ይበልጥ እንዲባባስ ያደርጋልና በመረጋጋት ይጀምሩ
🔸 ልጆቹን መረዳት፣በተቻለ አቅም በማቀፍና በቁመት ዝቅ ብሎ በማናገር ሃሳብ መግለጽ ማለማመድ
🔸ልጆቹን አሉታዊ ስያሜ ከመስጠት አልፎተርፎም ቤተሰብ ውስጥ በአስቸጋሪነት መነጋገሪያ ከማድረግ ይቆጠቡ(አስቸጋሪ፣ባለጌ፣ሰነፍ...)
🔸 ቅድሚያ የራሶትን ስሜት የሚገዙበትን መንገድ በመግራት ጥሩ አርዓያ ይሁኑ
🔸ሁሌም በዱዓ ከመታገዝ አይዘናጉ

**وَإِذَا سَأَلَكَ عِبَادِي عَنِّي فَإِنِّي قَرِيبٌ ۖ أُجِيبُ دَعْوَةَ الدَّاعِ إِذَا دَعَانِ ۖ فَلْيَسْتَجِيبُوا لِي وَلْيُؤْمِنُوا بِي لَعَلَّهُمْ يَرْشُدُونَ

ባሮቼም ከእኔ በጠየቁህ ጊዜ (እንዲህ በላቸው)፡- እኔ ቅርብ ነኝ፡፡ የለማኝን ጸሎት በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ፡፡ ስለዚህ ለኔ ይታዘዙ፤ በኔም ይመኑ፤ እነሱ ሊመሩ ይከጀላልና፡፡(2:186)**
https://t.me/bezretulkheyr

We recommend to visit

Welcome To Amharic films Best Place To find Amharic Movies

አዳዲስ እና የድሮ አማርኛ ፊልሞችን እና አማርኛ ተከታታይ ድራማዎችን ለማግኝት ቻናላችንን Join ይበሉ ።
Share:- @Amharic_Films

ለማስታወቂያ - @Abusheymc & @Alpha6249

Buy ads: https://telega.io/c/Amharic_films

Last updated 1 year, 8 months ago

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @Aymu_xo

Last updated 3 weeks, 1 day ago

╔╦╦═╦╔╦═╦═╦═╗
║ እንኳን ደህና መጡ | |
╚══╩═╩═╩╩╩╩═╝
➟ እንኳን ወደ ትልቁ የሊቨርፑል ( መርሲሳይድ) ቻናል በደህና መጡ ።
◉ ስለ ሊቨርፑል ◉
? ዝውውሮች

? ውጤቶች

? የጨዋታ ፕሮግራሞች

? እንዲሁም የተጨዋቾች ግለ ታሪክ

? ጨዋታዎችን በቀጥታ ወደናንተ የምናደርስ ይሆናል።

Owner:- @hackersolo0⭐️

Last updated 2 months, 2 weeks ago