ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።
ያግኙን +251913134524
Last updated 1 month, 2 weeks ago
ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም
- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት
ለማስታወቂያ ስራ --> @MKHI7
Last updated 1 month, 2 weeks ago
BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot
Last updated 3 weeks, 5 days ago
ኢስላምን በመስበካቸው ብቻ ነቢዩን ሶ.ዐ.ወ. በመካ ቁረይሾች ዘንድ እንደትልቅ ወንጀለኛ ነበር የተቆጠሩት፡፡ ለዚህም የግድያ ቅጣት ሊፈጽሙባቸው ብለው አሳልፈው እንዲሠጧቸው በቤተዘመዶቻቸው በበኒ ሃሺም ላይ ማዕቀብ ተጣለ። እንዳትገዟቸው፣ እንዳትሸጡላቸው፣ እንዳታናግሯቸው፣ እንዳትቀርቧቸው ተባለ።
በኒ ሃሺም ከሰዎች ተገልለው በአንድ ዋሻ ዉስጥ እንዲቆዩ ተደረገ።
ነቢያዊው ቤተሰብ ከባድ መከራ ላይ ወደቁ። ታረዙ፣ ተቸገሩ፣ ከርሃብ የተነሳ ቆዳ፣ ቅጠል፣ ጨርቅ፣ እስከመብላት ደረሱ።
ከሰዎች መካከል የነርሱ መከራ የተሰማቸው ሰው ሰው የሚሸቱ ሰስብእናዎች ነበሩ ። እኛ እንበላለን እንጠጣለን እንለብሳለን በኒ ሃሺሞች በርሃብና እርዛት ያልቃሉ? አሉና የተጣለባቸው ማዕቀብ እንዲነሳ አነሳሱ። በዚህም በኒ ሃሺሞች ከ3 ዓመታት በኋላ ከከበባ ማዕቀብ ወጡ፡፡
ዛሬ የፍልስጤም ጋዛ ሕዝብ በሁሉም አቅጣጫ ተከቦ ቦንብ ይዘንብበታል። 8ኛ ወሩን በያዘው ጭፍጨፋ ከ35ሺ በላይ ወገን ሲያልቅ ከሰዉነት ተራ የወጡት የዐረብ መሪዎች ዛሬም ድረስ አልሞቃቸው አልበረዳቸው፡፡ በተቃዉሞ ትንፍሽ የሚል የለም። የሚሞግትላቸው አታገኝም።
ከዚያ ይልቅ በደምና ሃይማኖት የማይገናኟቸው ደቡብ አፍሪካውያን በፍርድ ቤት ቆመው ሲከሱላቸው፤ የአሜሪካ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መኖሪያቸዉን ጎዳና አድርገው ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተው ሲጮኹላቸው ታያለህ። የሙስሊሙ ዓለም ዝም ጭጭ ያስደነግጣል። የመካ ቁረይሾችና የዛሬዎቹን ካፊሮች ያህል እዝነት ማጣታቸው ግራ ያጋባል፡፡ እኛ አቅም የለሾቹ መላ ጠፍቶናል፡፡ በሙስሊሞች የእልቂት የዕለት ዜና ደከመን፡፡ መተንፈስ አቃተን፡፡
ሰሞኑን በዋናነት የማደርገው ዱዓ ቢኖር
"አላህ ሆይ የዐረብ መንግሥታትን አጥፋቸው!" የሚል ነው፡፡
ያ አላህ አጥፋቸው!!።
በዚህ የኢንተርኔትና ሶሻል ሚዲያ ዘመን በሚገርም ፍጥነት ወደ ጃሂሊያው ዘመን እየተመለስን ነው። የሚያሳዝነው ደግሞ የመጨረሻው ነቢይ አልፈዋል። ካሁን በኋላ ነቢይ አይመጣም።
እናም ለራሳችሁ ሁኑ። ራሳችሁን ምከሩ። ከደጋግ የአላህ ባሮችና ዑለሞች ተጠጉ። የማይጠቅሟችሁን ግንኙነቶች በድፍረት በጥሱ። መጥፎ መድረኮችን ራቁ። ብቸኝነትን ምረጡ። ብዙ ወሬያችሁ ስለሰው ሳይሆን ስለራሣችሁ ይሁን።
መሳአል ኸይር
እኛ ማለት ሞኞች ያልተጠቀሙብን ዉድ ዕድሎች ነን ብዬ ለመሰከስ አስብና መልሸ እተወዋለሁ።
መቸሰ በቅርብ መሞታችን ስለማይቀር ብንጠቃቀም ይሻላል ብዬ እኮ ነው።
እውነቴን ነው የምላችሁ ይህንን ቻናል ለሌሎችም ብትጠቁሙ መልካም ነው።
ባለፈው በቁምነገር አስተዋውቁ ስላችሁ ሳቃችሁ። ቆይ ይህችን ምልክት 😀 አጠፋትና በምን ጥርስ እንደምትስቁ አያለሁ ።
"ምን አርጌው ነው ግን የቦለከኝ?" ብለህ አሁን ድረስ የምትብከነከንበት ሰው አጋጥሞህ ያውቃል ?
ካላጋጠመህ ወደፊት ያጋጥምሃል አብሽር ።
ያኔ ባጋጠመህ ጊዜ ደግሞ ብዙ አትገረም።
ሞኝ አትሁን፣ አትብሰልሰል፣ ብቻህንም አታውራ።
ቆይ እጠይቀዋለሁም አትበል።
ወዳጄ!
ሰው ከራሱ ጋር ተጣልቶ ምንም ሳታረገው ሰው ላይ በብሎኬት ማለቴ በብሎክ ብሶቱን የሚወጣበት ዘመን ላይ ደርሰናል ።
አትረበሽ፡፡
ዝምብለህ ኑር ያልኩህ እኔ ነኝ።
መሳአል ኸይር!
ደስ የሚለው ነገር ...
ጠዋት ላይ የምትወጣው ፀሐይ ብቻ አይደለችም፡፡
ለመኖር ተስፋ እንዲኖረን የሚገፋፉ መልካም ሰዎች፣
ማማረር እንደማይገባንና በሕይወት ለመቆየት ብዙ ምክንያት እንዳለን የሚመመክሩ ደጋግ ባሮችም አብረዋት ይወጣሉ፡፡
አላህን የሚያስታውሱን ዉብ ፊቶችም ይወጣሉ፡፡
ነግቶ እስክናያቸው የምንጓጓላቸው፣ የምንወዳቸው፣ የምንናፍቃቸው ሰዎችም ይወጣሉ፡፡
አላህ ያቆይልን።
እናንተን በማየቴ ደስ ብሎኛል በሉ፡፡
ተደሰቱ!።
ሰዎችም ከአንደበታችሁ በሚወጣው ቃል ይደሠቱ፡፡
ሶባሐል ኸይር
ስለራስህ ታሪክ አንተ የማታውቀዉን ሁሉ መልሰው ይነግሩሃል፡፡
አትከራከር፤ ዝምብለህ አዳምጣቸው ምን አደከመህ፡፡ የጉድ ዘመን፡፡
አለመፈለግህን ከሚያመለክቱ መገለጫዎች መካከል ስልክ ሰትደዉል አለማንሳት አንዱ ነው፡፡ አንድ ሁለት ምክንያት ፈጥረው ለዚህ ነው ያላነሳሁት ብለው ዑዝር ካቀረቡ ለክፉዉም ለበጎዉም ትንሽ ጠብቅ፡፡ ከዚያ በላይ ከሆነ ግን ተሠልችተሃል ማለት ነዉና ነቃ በል፡፡
ደዉለህ በሌላ ሰው አስነስተው “የለም” ወይም ቻርጅ ላይ ነው ከተባልክማ ሞተሃል፡፡ ጅሎች ጊዜ ባለፈበት ሙድ እየቀጡህ ነዉና ክብርህን ጠብቅ መልሰህ አትደዉል፡፡
በመጨረሻም ...
ያሸማቀቁንን፣ ያሳፈሩንን፣ ያዋረዱንን፣ የተዉንን፣ የተጠራጠሩንን፣ የሰደቡንን፣ የናቁንን ... ሁሉ የምናመሰግንበት ጊዜ ይመጣል ።
ምክንያቱም እነኚህ ሁሉ ቀና ለማለታችንና ለመጠንከራችን ምክንያት ሆነዋል።
ሶባሐል ኸይር ወዳጆች
ሶባሐል ኸይር መጽሐፍ
የመገኛ አድራሻዎች
በዉጭ አገር
ደቡብ አፍሪካ
MAYFAIR JOHANNESBURG
ሱመያ ሱፐር ማርኬት
ከመንዲ ሬስቶራንት በግራ በኩል
ጀማል ዳውድ
NO- 0622117711
ሪያድ
0535109794
ጂዳ
0509230683
0592348102
ዱባይ
971565542936
971551482240
ኩዌት
+965 55949211
ባሕሬን
0097332002858
ኳታር
+97455799676
በመላው አውሮፓ
+31 6 26063873
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።
ያግኙን +251913134524
Last updated 1 month, 2 weeks ago
ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም
- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት
ለማስታወቂያ ስራ --> @MKHI7
Last updated 1 month, 2 weeks ago
BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot
Last updated 3 weeks, 5 days ago