የእውቀት-አቡጊዳ ✏️💧💦❀✿

Description
_____________✔✿❀✔__________

✍... እንኳን ደህና መጣችሁ
"ኑ እናንብብ አብረን በእውቀት ከፍታ እናብብ!"

_____________✔❀✿✔___________
መልካም መስራት ክፉ ከማሰብ ይልቅ የበለጠ ደስ ይላል፡፡

✍ ለማንኛውም፦
✔ መልዕክት
✔ጥቆማና ቅሬታ @Ayuma
Advertising
We recommend to visit

★ሰውን በማዝናናት የብቃት ማረጋገጫ ያለው ብቸኛው ቻናል ሁሌም Telegram ላይ በጥበብ ደምቀን እናሸበርቃለን

💌 Contact us, @Modenyazbot

»የተመረጡ እና ማንም ያላያቸው የአማሪኛ ቀልዶች እንዲሁም የሚያስደንቁ ስዕሎችንና ቪዲዮ ያገኛሉ።

° ° [ ሙድ እንያዝ በእኛ የአራዶች መዝናኛ ] ° °

° ° Creator @Teke_Man ° °

Last updated 2 weeks, 1 day ago

☕ ስለ ኢትዮጲያ ቡና የሚወጡ ወቅታዊና ትክክለኛ የክለቡ መረጃዎች አዚህ ያገኛሉ!

➪የዝዉዉር ዜና
☞የአሰልጣኞች አስተያየት
➪ጎሎች እና ቪዲዮዎች
☞የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
➪ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት ከየስታድየሙ !

➡መወያያ ግሩፓችን @Ethiopia_coffee_Sc

📩ሀሳብ ወይም አስተያየት ካሎት
በዚህ 👉 @EthiopianCoffeeScBot ✍
BOT ማድረስ ይችላሉ!

Last updated 2 weeks, 2 days ago

እንኳን ወደ # ሉሲ የቴሌግራም ቻናል በደህና መጡ
#የሉሲ /LUCY DINKINESH E/ቤተሰብ ሰለሆኑ ደስብሎናል።

መረጃ መስጠት የምትፈልጉ በዚ አድርሱን 👉 @CACA77

# የኢትዬጵያዊነት የአሸናፊነት መገለጫ አርማችን ነው!
ነፃነታችንን 💪በፈርጣማው ጡንቻችን ይረጋገጣል
👉 ኢትዬጵያዊነት አርበኝነት የማንነት አርማች ነው
🙏🙏🙏

Last updated 1 month, 3 weeks ago

2 months, 1 week ago

#የፍቅር_አቦጊዳዬ ❣️#ክፍል12 💓
እንደ አጋጣሚ ሆኖ #ሀናም አብራኝ እዚው ት/ት ቤተ ተመዝግባ አገኘዋት፡፡ የትምርት የመጀመሪያው ቀን ላይ የዜግነት ክብር ከተዘመረ በኀላ "ተማሪዎች ስማችሁ በተለጠፈበት ክፍል ግቡ፤ ስማችሁ ያልተለጠፈ ካላችሁ እንደ አዲስ እንድትመደቡ አመልክቱ፡፡" ተባለ፡፡ እኔም በቀጥታ አመልክቱ ወደተባለበት ቦታ አመራው፡፡ አንደ መላጣ አስተማሪ ወንበር ላይ ተቀምጧል፡፡ "ምን ነበር?" አለኝ በቀና መልኩ፡፡ "ስመዘገብ የተነገረኝ ክፍል ጋር ስሜ አልተለጠፈም።" አልኩ አይኔን ግንባር ያርገው ብዬ፡፡
ስመዘገብ 9A እንደተመደብኩ ተነግሮኛል፡፡ ስሜም ተለጥፏል፡፡ ነገር ግን ሳጣራ #ፀጊ 9E ነው የተመደበችው፡፡ እና ምናልባት አጭበርብሬም ቢሆን ለአንዴ እንኳን እሷን እያየው ብማር ብዬ ነበር በውሸት ስሜ አልተለጠፈም ያልኩት፡፡ መላጣውም "የት ነበር ተመድበሀል የተባልከው?" አለኝ፡፡ ወፈርና ጠንከር ባለ ድምፅ "9A ነው" ብዬ መለስኩ፡፡ "ok ሲፅፉ ዘለውት ይሆናል፤ መጨረሻ ላይ ልፃፍክና ይስተካከላል" ብሎ ስሜን ከ9E የስም ማህደር ላይ ለማስፈር እስክርቢቶ አነሳ፡፡
"ግን ቆይ እስኪ ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ አብረን ቼክ እናርገው፤ maybe ሌላ ክላስ መድበውክ ይሆናል።" አለና ደስታዬ ላይ ውሃ ቸለሰበት፡፡ ከዛም የሁሉንም ክላስ የስም ዝርዝር አውጥቶ ሲፈልግ ብዙም ሳይለፋ ስሜን 9A ላይ አገኘው፡፡ እኔም "ማሽላ እያረረ ይስቃል" እንዲሉ የይስሙላ ያህል ፈገግ ብዬ አመስግኜው ወጣው፡፡
9A ገባውና ባዶ ወንበር ፈልጌ ተቀመጥኩ። ወዳው ክላሱን ከዳር እስከዳር በእይታዬ አካለልኩት፡፡ እንኳን ከእኔ ት/ት ቤት የመጣ ለመተዋወቅ ነፃነትን የሚጋብዝ አንድም ተማሪ የለም፡፡ አብዛኞቹ ግን ከምኔው ተዋወቁ በሚያስብል መልኩ አፍ ለአፍ ገጥመው ያወራሉ፡፡ ለነገሩ እኔ ነኝ እንጅ ፍቅርን ብዬ ተሰድጄ የመጣውት በብዛት 8ኛንም እዚው የተማሩ እንደሆኑ ያስታውቃሉ፡፡
👇👇👇👇👇
📩 ክፍል 13 ይቀጥላል ........
👉♥️ @Yewqetabugida67🌹🌷
👉 ለማንኛውም ቅሬታም ሙገሳም ሆነ አስተያየት 👉📩 @Ayuma የሚለውን ተጭነው ይጣፉና ይላኩለት ይመልሳልም

2 months, 2 weeks ago

#የፍቅር_አቦጊዳዬ ❣️#ክፍል11
ውጤት ሊወጣ 2ሳምንት አካባቢ ሲቀረው እቤት አዲስ የምመደብበት ት/ት ቤት እንደማልማር፤ በአንፃሩ ከሰፈራችን ወደ 2ኪሜ ርቆ በሚገኝ #አፄ_ናኦድ የሚባል ት/ት ቤት መግባት እንደምፈልግ በቁጣ ጭምር ተናገርኩ፡፡ እናቴ ት/ት ቤቱ ከተማ ስለነበር "ማን ሊያመላልስህ ነው? መኪና ይባላሀል፤ አይሆንም እዚው ምትመደብበት ት/ት ቤት ትማራለህ አለች፡፡ እኔ ግን ስለምመደብበት ት/ት ቤት እውነት የሆነውንም ያልሆነውንም ብዙ መጥፎ ነገር ተናገርኩ፡፡ በተጨማሪም የሚወስደኝና የሚያመጣኝ ትራኖስፖርት ነው፤ በዛ ላይ የማቃቸው ብዙ ተማሪዎች አሉ፤ ስለዚህ እዛ ነው ምገባው ብዬ ደመደምኩ፡፡
በስተመጨረሻ በእኔ ኩርፊያ ታግዞ በአባቴ አፅዳቂነት ከአንድ አመት በኀላ ከልቤ ላይ ንግስት ከፀጊ ጋር አንድ ት/ት ቤት እንደምማር ተወሰነ፡፡ የተሰማኝ ደስታ ልክ እሷን በእጄ ያስገባው ያህል ነበር፡፡
ክረምቱ አለቀና የሚኒስትሪ ውጤትም ወጣ 87.5 አምጥቼ አለፍኩ፡፡ ውጤትን ከተመለከቱ በኀላ እቤት አዲሱ ት/ት ቤት መግባቴን ይበልጥ ደገፉት፡፡ የምዝገባውን ቀን ካጣራው በኀላ ከእናቴ ጋር ለምዝገባ የሚያስፈልገኝን ሙሉ መረጃ ይዤ #አፄ_ናኦድ ት/ት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ተገኘው፡፡ ተመዝግቤ ከግቢው እንደወጣው #ፀጊን ከማላቃቸው እና 8ኛ ክፍልን ስትማር ካፈራቻቸው ጓደኞቿ ጋር አብራ ቁማ አየዋት፡፡ ከእናቴ ጋር በአጠገባቸው አልፈን ስንሄድ ለጓደኞቿ "ይሄ ነው ኤርሚያስ ማለት" ብላ በሌለውበት ስታስተዋወቅኝ ድንገት ሰማው፡፡ "አዎ ሁለት አመታትን እሷን በማፍቀር የከሳውት፣ የጠቆርኩት፤ እንዲሁም 7ኛ ክፍል የጀመርኩትን አሁን ለመጨረስ ተከትያት የመጣውት አዎ ኤርሚያስ እኔ ነኝ" አልኩ በውስጤ፡፡ ፍቅሬ አይጠወልግም፤ እንዲ እንደቀላል ደርቆ አይከስምም ብዬ በአዲስ ት/ት ቤት ዳግም ላፈቅራት አንድ ብዬ ጀመርኩ፡፡
👇👇👇👇👇
📩 ክፍል 12 ይቀጥላል ........
👉♥️ @Yewqetabugida67🌹🌷
👉 ለማንኛውም ቅሬታም ሙገሳም ሆነ አስተያየት 👉📩 @Ayuma የሚለውን ተጭነው ይጣፉና ይላኩለት ይመልሳልም

2 months, 3 weeks ago

#የፍቅር_አቦጊዳዬ ❣️#ክፍል10
8ኛ ክፍል አብራኝ በምትቀመጠው #ሀና የመረጃ አቅራቢነት እና የደብዳቤ አመላላሽነት ወደማለቅ ተቃረበ፡፡ አሁን ካየዋት ወደ 7-8 ወራት ሆነኝ፡፡ ነገር ግን ለአንድም ቀን ተረስታኝ ውላና አድራ አታቅም ነበር፡፡

ሚኒስትሪ ተፈታኝ ስለነበርኩ በተወሰነ መልኩ ወደ ትምርቴ ትኩረት አረኩ፡፡ ግን ያ የድሮውን ጎበዝ ኤርሚያስ መልሼ ላመጣው አልቻልኩም፡፡ እናም እንደምንም የቻልኩትን በራሴ፤ ያልቻልኩትን ደሞ ከጎኔ ፈተና ላይ አብሮኝ ከተቀመጠው የት/ት ቤታችን ጎበዝ ተማሪ ኤርሚያስ ሰርቼ ፈተናውን ጨረስኩ፡፡

አሁን ት/ት ተዘግቷል፡፡ ለ3 ወራት ያለምንም ስራ እቤት ልቀመጥ ነው፡፡ ይህ ማለት ደሞ ለ3 ወራት ቀንም ሌትም ስለፀጊ እያሰብኩ ልቆዝም ነው፡፡ እናም እሷም እንደኔው ተፈትና እቤት ስለሆነ ውሎዋ በሆነ መንገድ እሷን የማየቱን መንገድ ማመቻቸት እንዳለብኝ አሰብኩ፡፡

እንደተለመደው ሁሌም የሚረዳኝ #ወገን ጋር ሄድኩ፡፡ እሱም አጣርቶ የሆነ ወጣት ማዕከል ሰርከስ እንደምትሰራ ነገረኝ፡፡ አላቅማማውም እገባለው አልኩ፡፡

ከሰፈር ልጆች ጋር አብረን ሂደን ተመዘገብን፡፡ ባያችኝ ግዜ በመገረም ፈገግ አለች፡፡ ግን አውርታኝም አውርቻትም አላቅም፡፡ ሰርከስ እንደሚታወቀው አንዱ በአንዱ ላይ የመደራረብ የቡድን ስራ ነውና እኔን ከእሷ የሚያነካካ ስራ ቢኖር ብዬ ተመኘው፡፡ ሁሌም ስንሰራ እሷ ከሌሎች ልጆች ጋር ነበር የምትመደበው፡፡ እና አንዳንዴ ሳላስበው አብረዋት በሚሰሩ ወንዶች እቀናለው፡፡ በተለይ እያወሯት ከሳቀችላቸው የቀሙኝ ያህል ይሰማኝ ነበር፡፡

ክረምቱ እያለቀ ሲመጣ ስለ 9ኛ ክፍል ማሰብ ጀመርኩ፡፡ ምክንያቱም እስካሁን የተማርኩበት ት/ት ቤት የሚያስተምረው እስከ 8ኛ ብቻ ስለነበር፤ ወደ 9 ያለፈ ተማሪ ሌላ ቦታ ነው ሚመደበው፡፡ ይህን የምመደብበትን ት/ት ቤት ደሞ ገና ማለፍ እና መውደቄን ሳላቅ ጠልቼዋለው፡፡ ምክንያቱም አልፌ የተመደብኩበት ት/ት ቤት ገባው ማለት ሙሉ በሙሉ ከፀጊ ተለያየው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ እንደምንም ብዬ ቤተሰቦቼን አሳምኜ #ፀጊን ተከትዬ እሷ የገባችበት ት/ት ቤት መግባት አለብኝ ብዬ ወሰንኩ፡፡
👇👇👇👇👇
📩 ክፍል 11 ይቀጥላል ........
👉♥️ @Yewqetabugida67🌹🌷
👉 ለማንኛውም ቅሬታም ሙገሳም ሆነ አስተያየት 👉📩 @Ayuma የሚለውን ተጭነው ይጣፉና ይላኩለት ይመልሳልም

1 year, 1 month ago

#የፍቅር_አቦጊዳዬ #ክፍል 4

ከወራቶች በኀላ #ወገን እንዳናግራት አደፋፈረኝና ላናግራት ወሰንኩ፡፡ በሰዓቱ እንደሷ የምፈራው ሰው አልነበረም፡፡ በሆነ አጋጣሚ ሳያት ከያዘችኝ የምገባበት ነበር የሚጠፋኝ፡፡ ነገር ግን የሚሰማኝን በውስጤ አምቄ ከምሰቃይ ልተንፍሰውና ይለይለት ብዬ ወሰንኩ፡፡ እንደነገ ላወራት እንደዛሬ አዳር ላይ የምላትን እና ከእሷ ሊመጡ ይችላሉ የምላቸውን ምላሾች በመገመት በድጋሚ የምላትን ከእራሴ ጋር ስለማመድ አደርኩ፡፡

አይነጋ የለም ነግቶ ት/ት ቤት ገባን፡፡ ላናግራት የወሰንኩት ምሳ ሰዓት ስለነበር እስከዛ ያለው ሰዓት በጣም እራቀኝ። ሙሉ ሰውነቴን የፍራት ካባ ሲለብሰኝ ተሰማኝ፡፡ ምሳ እንደበላን ከትምርት ቤታችን ባለ 4 ፎቅ ህንፃ እራሱን እንደሚያጠፋ ሰው 4ኛው ላይ ሁኜ አስጠራዋት፡፡ ቦታውን የመረጥኩበት ምክንያት አንድም ተማሪዎች በምሳ ሰዓት ስለማይበዙበት ነበር። ሌላው ደሞ በሰዓቱ ሴትን ቀጥሮ ስለማውራትም ሆነ ምቹ ስለሆኑ ቦታዎች እውቀቱ ስላልነበረኝ ነው፡፡

ከትንሽ መንቆራጠጦች በኀላ በደም ፈንታ በደም ቧንቧዎቼ የምትዘዋወረው ቆንጆ ከህንፃው መወጣጫ ደረጃዎች በአንዱ በኩል መጣች፡፡ ልክ እንዳየዋት ውስጤ ይረበሽ ጀመር፤ ማታ የተዘጋጀውበት በሙሉ እንደ ጉም ተኖ ጠፋ፡፡ አጠገቤ እንደደረሰችም ልብን በሚያቀልጠው ፈገግታዋ ሞቅ ያለ ሰላምታ ከሰጠችኝ በኀላ እንዳላወቀ ሰው "ለምን ነበር የፈለከኝ?" አለች ትኩር ብላ እያየችኝ፡፡ አይኖቼ ከአይኖቿ ጋር ሲላተሙ ይባስ እፈራትና እረበሽ ጀመር፡፡

ትንፋሽ እንዳጠረው ሰው እያቃሰትኩ "እየውልሽ #ፀጊ አፍቅሬሻለው፤ ጓደኛ እንሁን" አልኳት አንዴ እሷን አንዴ መሬቱን እያየው፡፡

"አይ እኔ እንደዚህ አይነት ነገር ማሰብ አልፈልግም፤ አልችልም፡፡" አለች እጥር ምጥን ብሎ ለጆሮ በሚከብድ አማርኛ፡፡

"እሺ፤ ቻው" ብያት እኔ በአንዱ ደረጃ እሷ በሌላኛው ዳግም ላንገናኝ በሚመስል መልኩ እየተጣደፍን ሄድን፡፡ ቀጥታ ክላሴ ገባውና እራሴን ካረጋጋው በኀላ ለምን ልናገር ያሰብኩትን እንዳልተናገርኩና "አልችልም" ስትለኝ "ለማስረዳት በመሞከር ፈንታ ለምን "እሺ" የምትለው ቃል ከአፌ እንደወጣች እራሴን ጠየኩት፡፡ ለካ ከሚያፈቅሩት ሰው ፊት መቆም ለሞት ፍርድ ከመቆም ባልተናነሰ ልብን ሰልቦ በፍርሀት ይለውሳል፡፡

.....👉 ይቀጥላል
🌹@Yewqetabugida67

1 year, 1 month ago

#የፍቅር_አቦጊዳዬ #ክፍል3
ከዛን ቀን ጀምሮ በእየቀኑ ስለሷ ማሰብና መጨነቅ ስራዬ ሆነ፡፡ ት/ት ቤት፣ ሰፈር፣ ማታ አልጋዬ ላይ ተኝቼ የማስበውም የማልመውም እሷኑ ሆነ፡፡ በሰዓቱ ገና የ14 አመት ልጅ ስለነበርኩ በተጨማሪም ለእንደዚህ አይነት ስሜት አዲስ በመሆኔም ስሜቱ ምን እንደሆነ አላቅም ነበር፡፡ ነገር ግን ህንድ ፊልም ላይ እንደምናየው ነገሩ ቀስ በቀስ ፍቅር መሆኑ እየገባኝ መጣ፡፡

በእየቀኑ ምሳ ስትበላ፣ ስትጫወት፣ ወደ ቤቷ ስትሄድ በቅርብ ዕርቀት እከታተላታለው፡፡ ነገር ግን በዛ በልጅነት አንደበት ማን ቀርቦ ያውራ? ዝም ብቻ፡፡

ይህ ስሜት ቀስ በቀስ የውስጥ መንፈሴን እየጎዳኝ መጣ፡፡ ለወትሮው ተጫዋች የነበርኩ ልጅ አሁን መቆዘም ትልቁ ስራዬ ሆነ፡፡ ትምርቴንም እየደከምኩ መጣው፡፡ በፍቅሯ መነደፌን ከጓደኛዬ #ወገን በስተቀር ማንም እንዳያውቅብኝ ብጥርም የማሳያቸው ያልተለመዱ ባህሪያት ሚስጥሬን አደባባይ አወጡት፡፡ አብዛኞቹ የክላሴ ልጆች እንዲሁም የፀጊ ጓደኞች እና እራሷ ፀጊ ጭምር እሷን ማፍቀሬን ደረሱበት፡፡ ይህ ደሞ ይበልጥ ኑሮን አከበደብኝ፡፡

ማንኛውም ሰው እኔን እያየ ከተጫወተና ከሳቀ በፍቅሬ ያፌዘና ያላገጠ መስሎ ይሰማኝ ጀመር፡፡ በቃ በሰዓቱ እራሴን ሙሉ በሙሉ እሷን በማለምና በመፈለግ ውስጥ አጣውት፡፡

ከወገን ውጪ ቀርቤ የማወራውም የማማክረውም ጓደኛ አልነበረኝም፡፡ ት/ት ቤት ስሆን ከእሱ ጋር እቤት ስሆን ከግጥም ደብተሬ ጋር ሆነ ግዜዬን የማሳልፈው፡፡ በሰዓቱ የግጥም ደብተሬ የምለው አሁን ላይ ግጥም የሚለውን መጠሪያ ለመያዝ ይከብዳል፡፡ ነገር ግን በእዛን ወቅት ስለሷ የሚሰማኝን እና ለእሷ መንገር አለብኝ ብዬ የማስበውን በሙሉ ለእኔ ብቻ ትርጉም በሚሰጡ ቃላት የማሰፍርበት፣ የምተነፍስበት ጓደኛዬ ነበር፡፡......4
🌹@Yewqetabugida67

1 year, 1 month ago

#የፍቅር_አቦጊዳዬ
#ክፍል 2
በሰዓቱ እረፍት አልቆ ተደውሎ ስለነበር እሷ ከጓደኞቿ ጋር እየሮጠች ወደ ክፍሏ ሄደች፡፡ እኔም በወደኩበት ከእይታ እስክትርቅ ድረስ በአይኔ ሸኘዋት፡፡

ክላስ ገብቼ ልክ እንደሌሎቹ ደብተር አውጥቼ እስክርቢቶ በእጄ ይዣለው፡፡ ነገር ግን በአእምሮዬ ከደቂቆች በፊት አይኔን ስለወጋኝ ውበት እያሰላሰልኩ ነው፡፡ "ስንተኛ ክፍል ናት? የት ነው ሰፈሯ? ስሟ ማነው? እንዴት እስከዛሬ አላየዋትም? " በዛች ቅፅበት ፍቅርን አዝለው ወደ አእምሮዬ የመጡ ጥያቄዎች ነበሩ፡፡

እንዳያልቅ የለም ቀሪው የት/ት ክፍለ ግዜ አልቆ ምሳ ተደወለ፡፡ ምሳ አብሬው ምበላ፣ ወደቤት የሆነ መንገድ ድረስ አብሬው የምሄድ፣ አብዛኛውን ግዜዬን አብሬው ማሳልፈው #ወገን የሚባል ጓደኛ ነበረኝ፡፡

እናም ምሳ እየበላን "ስማ ቅድም አባሮሽ ስንጫወት እኔ እንዳባራት የተሰጠችኝን ልጅ ታቃታለህ እንዴ?" ብዬ ጠየኩት፡፡

"እእእእእ ፀገነትን ነው? አዎ" በማለት መለሰ፡፡

"ፀገነት ነው ስሟ! ማለት ስንተኛ ክፍል ናት? የት ነው ሰፈሯ? የነማን ጓደኛ ናት? ምሳ የት ነው ምትበላው?" በማለት ስለሷ ለማወቅ እንደጓጓው በሚያሳብቅ መልኩ የጥያቄ ናዳ አወረድኩበት፡፡

እሱም "እንደኛው ሰባተኛ ነች፡፡ ሰፈሯ ከእኔ ሰፈር ብዙም አይርቅም፤ ቅርብ ለቅርብ ነን፡፡ እና ቆንጆ ነች፡፡" አለ እየሳቀና በእጁ መታ እያደረገኝ፡፡

ወዳው እንዴት እንደሆነ በማላውቀው መልኩ ውስጤ እሷን እሷን ሲለኝ ተሰማኝ፡፡ "ምሳ የት ነው ሚበሉት?" አልኩት፡፡

እሱም በልተን እንጨርስና እወስድሀለው ብሎ የሚበሉበት ቦታ ወሰደኝ፡፡ የመማሪያ ክላስ ሲሆን ግድግዳው በጠፍጣፋ ጣውላ ተደርድሮ የተሰራ ነው፡፡ በጣውላና ጣውላው መካከል ባላው ቀዳዳ አጮልቄ እንዳይ ጠቆመኝ፡፡ አዎ #ፀጊ ከሶስት ጓደኞቿ ጋር ምሳዋን እየበላች ነበር፡፡ በሰውነት ሁሉም ይበልጧታል፡፡ በመልክ ግን አዳላህ አትበሉኝ እንጂ ትቦንሳቸዋለች፡፡ ስትስቅ ደሞ ላለመሳቅ ቀጠሮ የያዘ ሰውም ቢሆን ፈገግ ይላል፡፡ በቃ እንዴት እንደሆነ ባላቅም ገና በ14 አመቴ ፍቅር ይዞኛል፡፡ ግን ፍቅር ምንድን ነው? አላቅም!!!....... ፫ ❤️
@Yewqetabugida67

1 year, 2 months ago

#የፍቅር_አቦጊዳዬ
#ክፍል1

በወቅቱ እንደማንኛውም ታዳጊ ጨዋታን አብዝቼ የምወድ የ7ኛ ክፍል ተማሪ ነበርኩ፡፡ በትምርቴ ከ1-10 ባለው ደረጃ እወጣ ነበር፡፡ በብዛት 4ኛ እና 5ኛ የኔ ደረጃዎች ነበሩ፡፡ ከዛ በዘለለ ግን ሙሉ ቀን ሙሉ ለሊት ስጫወት በውልና ባድር ጨዋታ የማልሰለች ልጅ ነበርኩ፡፡

ከቀኖች ሁሉ በቅጡ በማላስታውሰው በአንዱ ቀን ከተወሰነ የት/ት ክፍለ ግዜ በኀላ ለእረፍት ተለቀን ከተወሰኑ ተማሪዎች ጋር ተመራርጠን አባሮሽ እየተጫወትን ነው፡፡

በሰዓቱ እኔ አባርሬ እንድይዝ የተሰጠኝ አንዲት ቀይ ቀጠን ያለችን ልጅ ነበር፡፡ ልጅቷን ከዚህ በፊት ልብ ብዬ አይቻት አላቅም፤ ስሟንም ሰምቼው አላቅም፡፡ ጨዋታው ተጀመረና እኔ ነብር እሷ ሚዳቆ ሆነን በረጅሙ የት/ቤታችን የሳር ሜዳ ላይ ያዝኩሽ አመለጥኩህ ሩጫ ያዝን፡፡

ልይዛት በጣም እቀርብና በድንገት የእኔ ፍጥነት ቀንሶ የእሷ በመጨመር ታመልጠኛለች፡፡ ከብዙ ልብ አፍርስ ሩጫ በኀላ ከነብር እጅ ሚያመልጥ የለምና ሚዳቆዋን ያዝኳት፡፡ ነገር ግን እሷ ልታመልጠኝ እኔም ይዣት ለማስቀረት ስንሞክር እኔ በእሷ ላይ ወደቀን ተገኘን፡፡

ዩኒፎርሟ እንደመገላለጥ ብሎ ነበርና እንደማፈር ብላ ልብን በሚያቀልጥ ሁኔታ በእነዛ ሁለት አይኖቿ ለመጀመሪያ ግዜ አይኖቼን ተመልክታ እየተሽኮረመመች ከመሬት ተነስታ ሄደች፡፡ በዛች ቅፅበት ያቺ ቀጭን ቀይ ቆንጆ የመጀመሪያ ፍቅሬ ልትሆን ሳታስፈቅድ ወደ ልቤ ዘልቃ ገባች። 👇 ክፍል ሁለት ይቀጥላል

1 year, 2 months ago

አዲስ የፍቅር ታሪክ ሊጀመር ነው።

1 year, 3 months ago
የእውቀት-አቡጊዳ ✏️💧💦❀✿
We recommend to visit

★ሰውን በማዝናናት የብቃት ማረጋገጫ ያለው ብቸኛው ቻናል ሁሌም Telegram ላይ በጥበብ ደምቀን እናሸበርቃለን

💌 Contact us, @Modenyazbot

»የተመረጡ እና ማንም ያላያቸው የአማሪኛ ቀልዶች እንዲሁም የሚያስደንቁ ስዕሎችንና ቪዲዮ ያገኛሉ።

° ° [ ሙድ እንያዝ በእኛ የአራዶች መዝናኛ ] ° °

° ° Creator @Teke_Man ° °

Last updated 2 weeks, 1 day ago

☕ ስለ ኢትዮጲያ ቡና የሚወጡ ወቅታዊና ትክክለኛ የክለቡ መረጃዎች አዚህ ያገኛሉ!

➪የዝዉዉር ዜና
☞የአሰልጣኞች አስተያየት
➪ጎሎች እና ቪዲዮዎች
☞የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
➪ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት ከየስታድየሙ !

➡መወያያ ግሩፓችን @Ethiopia_coffee_Sc

📩ሀሳብ ወይም አስተያየት ካሎት
በዚህ 👉 @EthiopianCoffeeScBot ✍
BOT ማድረስ ይችላሉ!

Last updated 2 weeks, 2 days ago

እንኳን ወደ # ሉሲ የቴሌግራም ቻናል በደህና መጡ
#የሉሲ /LUCY DINKINESH E/ቤተሰብ ሰለሆኑ ደስብሎናል።

መረጃ መስጠት የምትፈልጉ በዚ አድርሱን 👉 @CACA77

# የኢትዬጵያዊነት የአሸናፊነት መገለጫ አርማችን ነው!
ነፃነታችንን 💪በፈርጣማው ጡንቻችን ይረጋገጣል
👉 ኢትዬጵያዊነት አርበኝነት የማንነት አርማች ነው
🙏🙏🙏

Last updated 1 month, 3 weeks ago