Unlock a World of Free Content: Books, Music, Videos & More Await!

የዳሌ አቡነ ተክለሃይማኖት ቅዱስ ሚካኤል እና እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ምዕራፈ ቅዱሳን ሰንበት ት/ቤት

Description
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው
ምሳ፩፥፯
@Kidu1mirafeKidusanSenbet
@Kidu1mirafeKidusanSenbet
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት በበርህ ወረዳ የዳሌ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ምዕራፈ ቅዱሳን ሰንበት ት/ቤት።
We recommend to visit

ከእሁድ እስከ እሁድ ፈጣን የመረጃ ምንጭ!

➮የሃገር ቤት ትኩስ ትኩስ መረጃዎች
➮የአፍሪካ መረጃዎችን በሙሉ
➮የአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ሙሉ መረጃ
➮ቁጥራዊ መረጃዎች እና ዳሰሳዎች
➮ጨዋታዎችን በቀጥታ ከየስታዲየሙ

➮በስልክ ጥሪ ምንም አይንት የማስታወቂያ ስራ አንቀበልም!

ለማስታወቂያ ስራ @Promotion_4_3_3_Bot

Cʀᴇᴀᴛᴏʀ @Simera10

⓸-⓷-⓷ስፖርት በኢትዮጵያ| 2016

Last updated 3 weeks, 3 days ago

ሙሌ ስፖርት ስፖርታዊ መረጃዎችን ከእሁድ እስከ እሁድ ያገኙበታል

የሃገር ቤት መረጃ
የአውሮፓ ሊግ መረጃ
ቀጥታ ስርጭት
የዝውውር ዜና

ለማስታወቂያ ስራ @Mulesporta
@Teme_Ayu

ስልክ ቁጥር +251911857852

Last updated 1 month, 4 weeks ago

–The Best Arsenal Football Club Telegram Channel in Ethiopia.

–በኢትዮጵያ ትልቁ የአርሰናል ቴሌግራም ቻናል ነው። ስለ አርሰናል አዳዲስና ትኩስ መረጃዎች የዝውውር ፣ ዜናዎች ፣ኃይላይቶች፣ቪዲዬች፣ ትንታኔ በቀጥታ ያገኛሉ። ____________________

📥 For advert : @Mex_classic

Last updated 3 weeks, 5 days ago

4 years, 2 months ago

እስኪ መንፈሳዊነትን እንለካካ? ሐሰት የሐሰት አባት ልጆች ግብር ነው። እውነት ደግሞ የእውነትና የብርሃን ልጆች መገለጫ ነው።

  1. የክርስትና ስምህ?
  2. የክርስትና ስምሽ?
  3. መንፈሳዊ ሕይወትህ ምን ይመስላል?
  4. መንፈሳዊ ሕይወትሽ ምን ይመስላል?
  5. ወጣት ከሆንክ በኋላ ቆርበህ ታውቃለህ?
  6. ወጣት ከሆንሽ በኋላ ቆርበሽ ታውቂያለሽ?
  7. አንድ የምትወደውን መዝሙር በድምጽ ዘምርልኝ
  8. የምትወጂውን መዝሙር በድምጽ ዘምሪልኝ?
  9. በሕይወትህ እግዚአብሔር ምን እንዲያሳካልህ ትፈልጋለህ?
  10. በሕይወትሽ እግዚአብሔር ምን እንዲያሳካልሽ ትፈልጊያለሽ?
  11. ስልክህ ላይ በብዛት ያለው ዘፈን ነው ወይስ መዝሙር?
  12. ስልክሽ ላይ በብዛት ያለው ዘፈን ነው መዝሙር?
  13. ኢየሱስን እንዴት ትገልጸዋለህ?
  14. ኢየሱስን እንዴት ትገልጪዋለሽ?
  15. ስዕላድኖ profileህ አድርግ?
  16. ስዕላድኖ profileሽ አድርጊ?
  17. እስኪ መዝሙር ጋብዘኝ
  18. መዝሙር ጋብዢኝ?
  19. ፍቅር ላንተ ምንድነው?
  20. ፍቅር ላንቺ ምንድነው?
  21. የፍቅር አጋር አለህ? ካለህ ስምና ፎቶዋን?
  22. የፍቅር አጋር አለሽ? ካለሽ ስምና ፎቶዋን?
  23. ድንግል ማርያምን ምን ያህል ትወዳታለህ?
  24. ድንግል ማርያምን ምን ያህል ትወጃታለሽ?
  25. በጣም የተደሰትክበትና ያዘንክበት ቀን?
  26. በጣም የተደሰትሽበትና ያዘንሽበት ቀን?
  27. ሕይወት ላንተ ምንድናት?
  28. ሕይወት ላንቺ ምንድናት?
  29. በጣም የምትወደው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ?
  30. በጣም የምትወጂው የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ?
  31. ሰይጣንን ብታገኘው ምን ትጠይቀዋለህ?
  32. ሰይጣንን ብታገኚው ምን ትጠይቂዋለሽ?
  33. ለአንድ ቀን ፈጣሪ በፍጥረት ላይ ሁሉ ሥልጣን ቢሰጥህ ምን ታደርጋለህ
  34. ለአንድ ቀን ፈጣሪ በፍጥረት ሁሉ ላይ ሥልጣን ቢሰጥሽ ምን ታደርጊያለሽ?
  35. ጸጋህ ምንድነው ብለህ ታስባለህ?
  36. ጸጋሽ ምንድነው ብለሽ ታስቢያለሽ?
  37. የምትወደው ቀን ከ1-30? ልዩ ምክንያትህ አለህ?
  38. የምትወጂው ቀን ከ1-30? ልዩ ምክንያት አለሽ?
  39. ጸሎት ትጸልያለህ? መች መች?
  40. ጸሎት ትጸልያለሽ?መች መች?
  41. ቤ/ክ በየምን ያህል ጊዜ ትሄዳለህ? በየቀኑ፣ በየሳምንቱ፣ የንግስ የንግስ ዕለት፣ ታላላቅ በዓላት መስቀልና ጥምቀት ለት? አንዳንዴ አልፎ አልፎ?
  42. ቤ/ክ በየ ምን ያህል ጊዜው ትሄጃለሽ?
  43. ለኔ ልዩ ነው/ናት ያደረገልኝ አለ የምትለው ቅዱስ? ወይም ቅድስት?
  44. ለኔ ልዩ ነው(ናት) ያረገልኝ(ያረገችልኝ) ነገር አለ የምትይው ቅዱስ/ቅድስት?
  45. ከቅዱሳን ታሪክ እጅግ በጣም የሚደንቅህ የማነው?
  46. ከቅዱሳን ታሪክ እጅግ በጣም የሚገርምሽ የማነው?
  47. መጽሐፍ ቅዱስ ታነባለህ? አንብበህ ታውቃለህ?
  48. መጽሐፍ ቅዱስ ታነቢያለሽ? አንብበሽ ታውቂያለሽ?
  49. እስኪ አንብበህ የወደድከውን መንፈሳዊ መጽሐፍ ጋብዘኝ
  50. አንብበሽ የወደድሽውን መንፈሳዊ መጽሐፍ ጋብዢኝ
  51. ስዕለት ተሥለህ ታውቃለህ? የሰመረልህስ አለ? ካለ ምን?
  52. ስዕለት ተሥለሽ ታውቂያለሽ? የሰመረልሽስ ነገር አለ? ካለ ምን?
  53. ቢኖረኝ ብለህ የምትመኘው ጸጋ?
  54. ቢኖረኝ ብለሽ የምትመኚው ጸጋ?
  55. መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ገዳማት ሄደህ ታውቃለህ? ካወቅክ የት የት?
  56. መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ገዳማት ሄደሽ ታውቂያለሽ? ካወቅሽ የት የት?
  57. የምትችለውን አንድ የንስሃ መዝሙር በድምጽ ዘምርልኝ?
  58. የምትችይውን አንድ የንስሃ መዝሙር በድምጽ ዘምሪልኝ?
  59. ግጥም መጻፍ ትችላለህ? ከቻልክ እስኪ ስለ ኢየሱስ ቲኒሽ መስመር ጻፍ?
  60. ግጥም መጻፍ ትችያለሽ? ከቻልሽ እስኪ ስለ ኢየሱስ ቲኒሽ መስመር ጻፊ?
  61. ቤ/ክ አገልጋይ ነህ? ወይም ሆነህ ታውቃለህ? (ሰ.ት ተማሪ?) ከሆነ ለምን ያህል ጊዜ?ለምንስ አቋረጥክ?
  62. ቤ/ክ አገልጋይ (ሰ.ተማሪ) ነሽ? ወይም ሆነሽ ታውቂያለሽ? ከሆነ ለምን ያህል ጊዜ?ለምንስ አቋረጥሽ?
  63. አያድርገውና የመጨረሻ ቀንህ ዛሬ ብቻ እንደሆነ ቢነገርህ ባለህ አንድ ቀን ምን ታደርጋለህ?
  64. አያድርገውና የመጨረሻ ቀንሽ ዛሬ ብቻ ቢሆን ባለሽ አንድ ቀን ምን ታደርጊያለሽ?
  65. ክርስትና የተነሳኸው የት ሃገር የት ደብር ነው?
  66. ክርስትና የተነሳሽው የት ሃገር? የት ደብር ነው?
  67. ቅዳሴ ታስቀድሳለህ? ተሰጦውን ምን ያህል ትችላለህ?
  68. ቅዳሴ ታስቀድሻለሽ? ተሰጦውን ምን ያህል ትችያለሽ?
  69. ሁሉንም አጽዋማት ትጾማለህ? እስከ ስንት ሰዓት?
  70. ሁሉንም አጽዋማት ትጾሚያለሽ? እስከ ስንት ሰዓት?
  71. ቤ/ክ አድረህ፣ ማኅሌትና ኪዳን ቆመህ ታውቃለህ?
  72. ቤ/ክ አድረሽ፣ ማኅሌትና ኪዳን ቆመሽ ታውቂያለሽ?
  73. ከበሮ መምታት ትችላለህ? ከቻልክ የመዝሙር ነው የማኅሌት?
  74. የመዝሙር ከበሮ መምታት ትችያለሽ? (የማኅሌት አይጠየቅም)
  75. በሕይወትህ መለወጥ የምትፈልገው ነገር?
  76. በሕይወትሽ መለወጥ የምትፈልጊው ነገር?
  77. ላንተ መንፈሳዊ ሰው ማለት ምናይነት ነው?
  78. መንፈሳዊ ሰው ማለት ላንቺ ምናይነት ነው?
  79. ብሄድ ብለህ የምትመኘው ገዳም?
  80. ብሄድ ብለሽ የምትመኚው ገዳም?
  81. እግዚአብሔርን ከእስከዛሬ ከሁሉም በላይ ከልብህ ሆነህ እንዲያደርግልህ የተማጸንከው የለመንከው ነገር?
  82. እግዚአብሔርን ከእስከዛሬው ከሁሉም በላይ ከልብሽ ሆነሽ እንዲያደርግልሽ የተማጸንሽው ነገር?
  83. ክርስቶስ ለአንተ ሲል የተቀበለውን መከራ ከልብህ አስበህ ከልብህ አዝነህ ታውቃለህ?
  84. ክርስቶስ ላንቺ ሲል የተቀበለውን መከራ ከልብሽ አስበሽ ከልብሽ አዝነሽ ታውቂያለሽ?
  85. ሲጨንቅህና ስታዝን ስትከፋ ዝማሬ ታደምጣለህ?
  86. ሲጨንቅሽና ስታዝኚ ስትከፊ ዝማሬ ታዳምጫለሽ?
  87. ከመናፍቃን ጋር ተከራክረህ ታውቃለህ?
  88. ከመናፍቃን ጋር ተከራክረሽ ታውቂያለሽ?
  89. እስኪ ቢያንስ 10 የቅዱሳንን ስም ጻፍ?
  90. እስኪ ቢያንስ 10 የቅዱሳንን ስም ጻፊ?
  91. ማዕተብህን በጥስ፣ ክርስቶስን "አምላኬ አይደለም" በል፣ ማርያምንም ካዳት አልያም በፊትህ ቤተሰቦችህን እንገድላለን ከዛን አንተም ትገደላለህ ብትባል የእውነት ሞትን ትቀበላለህ? ዝግጁ ነኝ ብለህ ታስባለህ?
  92. የላይኛውን ጥያቄ መልሺ? አንቺ ብትሆኚስ?
  93. ገዳም ለመግባት (ለመመንኮስ) አስበህ ታውቃለህ?
  94. ገዳም ለመግባት (ለመመንኮስ) አስበሽ ታውቂያለሽ?
  95. ድንግል ማርያምን እንድታማልድልህ የጨነቀህን ነገር ነግረሀት ታውቃለህ?
  96. ድንግል ማርያምን እንድታማልድልሽ የጨነቀሽን ነገር ነግረሻት ታውቂያለሽ?
  97. ስትደነግጥ የምትጠራው ስም አለ? ማን?
  98. ስትደነግጪ የምትጠሪው ስም አለ? ማን?
  99. መንፈሳዊ ስፍራ የተነሳኸው ወይም ነጠላ ለብሰህ የተነሳኸው ፎቶ ካለ ላክልኝ? ከሌለ በዚ ሳምንት ስትሄድ ተነስተህ ትልካለህ
  100. መንፈሳዊ ሥፍራ የተነሳሽው ወይም ነጠላ ለብሰሽ የተነሳሽው ፎቶ ካለ ላኪልኝ? ከሌለሽ በዚህ ሳምንት ስትሄጂ ተነስተሽ ትልኪያለሽ!

  101. Bones question
    (የጥያቄዎቻችሁን መልስ የወጣቶች ቻናል ታውቀዋለህ? እና ምን ትሰራለህ እስካሁን ቶሎ ተቀላቀላ @Hamongog2 )

4 years, 2 months ago

💫🌿💫🌿💫🌿💫🌿💫🌿
ሞት በጥር ነሀሴ መቃብር ።
🌿💫🌿💫🌿💫🌿💫🌿💫
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን፡፡

ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩላ?
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ይዞ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ እመቤታችን
ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኮ የሔደው የዕረፍቷ ጊዜ መድረሱን ለማብሠር ነበር፡፡ የድል
ምልክት የሆነውን ፍሬው የተንዠረገገ የቴምር ፍሬ የሚያፈራውን ዘንባባ ይዞ ለሁለተኛ ጊዜ
እርሷ ወዳለችበት ይዞ ገብቶ ደስ ይበልሽ ሲላት አሁንም እየሰገዳና እጅ እየነሣ ነበር፡፡
ጌታችን እንዳዘዘውም "ልጅሽና ጌታሽ እናቴ ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ ጊዜው ደርሷል ብሏል፡፡
ከሴቶች ተለይተሸ የተባረክሽ ቅድስት ሆይ ስለዚህም ለሁለተኛ ጊዜ ይህን መልካም
የምሥራች እነግረሽ ዘንድ ላከኝ፡፡ ብፅዕት ሆይ በምድር የሚኖሩትን ሁሉ በደስታ
እንደሞላሻቸው አሁን ደግሞ በዕረፍትሽና በዕርገትሽ ምክንያት የሰማይ ኃይላት በደስታ
ይሞሉ ዘንድ በሰማይ ያሉ ነፍሳትም ሁሉ ከመቼውም ጊዜ በላይ በክብር ያበሩ ዘንድ
ምክንያት ትሆኛለሽ፡፡ ደስተኛይቱ ፍስሕት የሚል ማዕረግ ለዘላለም ተስጥቶሻልና ስታዝኝና
ስታለቅሽ በኖርሽው መጠን ደስ ይበልሽ፡፡ ጸሎቶችሽና አስተብቁዖቶችሽ በሙሉ በልጅሽ
ፊት ወደ ሰማይ ዐርገዋል፤ ስለዚህም ይህን ዓለም ትተሽው ወደ ሰማይ ትሔጅና ፍጻሜ
በሌለው የዘላለም ሕይወት ከልጅሽ ጋር ትኖሪ ዘንድ አዝዟል" ብሎ ዘንባባውንም በእጇ
ሰጣት፡፡ የነበረውን ትውፊት ሁሉ አሰባስቦና አጠናቅሮ በሰባተኛው ክፍለ ዘመን በግሪክ
ቋንቋ ሕይወቷንና ተጋድሎዋን በተሻለ ሁኔታ የጻፈው መክሲሞስ ዘኢየሩሳሌም
እንደመዘገበው እመቤታችን የመልአኩን ብሥራት በሰማች ጊዜ እጅግ ተደስታ እንደ
ቀድሞው ሁሉ በፍጹም ትሕትና "እነሆ የእግዚአብሔር አገልጋዩ፤ አሁንም እንደቀድሞው
እንደቃልህ ይደረግልኝ አለችው" ይላል፡፡ ከዚህ በኋላ አሁን በዚህ ጽሑፍ የማልገልጻቸው
እጂግ ብዙ ገቢረ ተአምራት ተፈጽመዋል፡፡ እመቤታችን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የሰጣትን
ዘንባባ ይዛ በደብረ ዘይት ተራራ ሔዳ ከጸለየች በኋላ ቀድማ ትነግረው ዘንድ ትፈልገው
የነበረውን ወንጌላዊና ነቢየ ሐዲስ ንጹሕ ድንግል ዮሐንስን በደመና አምጥቶላታል፡፡
ከዚያም ልዩ የእግዚአብሔር መቅደስ ወዳደረገቻት ቤቷ ከተመለሰች በኋላ ሐዋርያትና ብዙ
ተላውያነ ሐዋርያት ድንገት አንድ ጊዜ በደመና ደረሱ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ከደመናው
ከተቀበላቸው በኋላ ወደ እርሷ ይዟቸው ገባ፡፡ ሁሉም አንድ በአንድ እየሆኑ በፊቷ እያለፉ
ተሳለሟት፤ እርሷም አነጋገረቻቸው፡፡ ከአርድእት አንዱ የሆነው ተላዌ ቅዱስ ጳውሎስ
የሆነውና ከፍልስፍና የተመለሰው የአቴናው ዲዮናስዮስ ከተገኙት አርድእት መካከል እርሱ
ቅዱስ ጤሞቴዎስና ቅዱስ ሔሮቴዎስ እንደነበሩና ቅዱስ ጴጥሮስን፤ ቅዱስ ጳውሎስንና
ሌሎቹን ሐዋርያት ስታናግራቸው በዓይኑ እንዳየና ራሱም በፊቷ አልፈው እማሔ ካደረጉት
መካከል መሆኑን ለጢሞቴዎስ በላካት መልእክት ላይ መዝግቦታል፡፡ ከዚያም በኋላ መንፈስ
ቅዱስ ወርዶባቸው ሁሉም ሐዋርያትና አርድእት መንፈስ ቅዱስ እንደሰጣቸው መጠን
ተሰምቶ የማያውቅ ልዩ ምስጋና ማቅረባቸውን መዝግቧል፡፡ ከዚህም በኋላ የተደረጉት
ተአምራት ብዙዎች ስለሆኑ በሌላ ጽሑፍ እስክምለስ ድረስ አሁንም እነርሱን ከመዘርዘር
እቆጠባለሁ። በመጨረሻም ጌታችን በሚያስፈራና በልዩ ግርማ ከቅዱሳኑ ሁሉ ጋር
መውረዱንና እነሙሴ እነዳዊት በአንድነት ከአእላፋት መላእክት ጋር ሲዘምሩና የሰማይ
ሠራዊት በደስታ ሲጥለቀለቁ ጽዮንም ስትናወጥ ማየታቸውን በእኛ የጥር ወር በልዩ ከብር
ማርፏን የነበሩት ሐዋርያትና አርድእት ሁሉ መስክረዋል፡፡
የአካላዊ ቃልን ወደዚህ ዓለም መምጣት ማብሠር እንደተሰጠህ የድንግሊቱንም
ወደዚያኛው ዓለም መሔድ ማብሠር ድጋሜ የተሠጠህ የታመንህና የከበርክ ቅዱስ
ገብርኤል ሆይ እባክህ መልካም ነገር እያለ የራቀውን የእኛን ትውልድም ከመልካሙ ነገር
አገናኝልን፤ መልካሙን አሰማን፡፡ ከድንግሊቱና ከደስተኛይቱ እናታችን በረከትም
አድርስልን፡፡ ክብሯን ግለጥ ፤ እኛንም ፈጽመህ አማልደን።
እንግዲያውስ ቅዱሳኑን ተከትለን እኛም እየዘመርንና እያመሰገንን የሰው ዘር መመኪያ
የሆነችውን የእናታችንና የእመቤታችን የንጽሕተ ንጹሐን የቅድስተ ቅዱሳን የድንግል
ማርያምን በዓለ ዕረፍት በተከበረው ትውፊታችን መሠረት እናክብር፡፡
ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ አባ ጊዮርጊስና ሶርያዊ ማር ኤፍሬም የመሥዋዕቱን በግ
ያስገኘሽልን፤ እረኛችን የወልድሽልን ንጽሕት በግ ሆይ የሚሉሽ ፍጽምትና የታመንሽ አማላጅ
ሆይ በፍጹም ምልጃሽ ሁላችን አስምሪ ።
እንኳን ለበዓለ ዕረፍታ ለንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም አደረሳችሁ፡፡
🌿💫🌿💫🌿💫🌿💫
@tekletewoflos
💫🌿💫🌿💫🌿💫🌿

4 years, 4 months ago
የዳሌ አቡነ ተክለሃይማኖት ቅዱስ ሚካኤል እና …
4 years, 4 months ago
የዳሌ አቡነ ተክለሃይማኖት ቅዱስ ሚካኤል እና …
4 years, 4 months ago
የዳሌ አቡነ ተክለሃይማኖት ቅዱስ ሚካኤል እና …
4 years, 4 months ago
የዳሌ አቡነ ተክለሃይማኖት ቅዱስ ሚካኤል እና …
4 years, 4 months ago
የዳሌ አቡነ ተክለሃይማኖት ቅዱስ ሚካኤል እና …
4 years, 4 months ago

🗣🗣🗣ጆሮ ያለው ይስማ : ልብ ያለው ልብ ይበል

ይህ የበረኸኞች ቅዱሳን አባቶቻችን የንስሐ ግቡ ጥሪ ነው።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ቢያንስ ለ 21 የተዋህዶ ልጆች Share በማድረግ ክርስትያናዊ ግዴታችንን እንወጣ

ነገ ከባድ የመከራ ጊዜ አለና ዛሬውኑ ንስሐ ገብታችሁ ተዘጋጁ።

2012፣ 2013፣2014፣ የኢትዮጵያ የምጥ ዘመናት ናቸው።

😭ንስሐ ያልገባ በቶሎ ንስሐ ይግባ። ንስሐ የገባ ደግሞ በየሳምንቱ ለነፍስ አባቱ ራሱን ያስመርምር
የመዳን ቀን ዛሬ ነውና

😴በስንፍና ነገ ንስሀ እንገባለን ያላችሁ ነገ አባቶችን ላታገኙቸዉ ትችላላችሁ እና እንዳይረፍድባችሁ

ሥጋወደሙ የተቀበሉ፣ ንስሐ የገቡ ሰዎች ብቻ ጨለማውን ይሻገሩታል። ንጉሡ ከመምጣቱ በፊት አባጣ፣ ጎርባጣው የግድ መስተካከል አለበት። ተራራው ዝቅ ማለት አለበት። ጉድባው ጉድጓዱ መሙላት አለበት። በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር እስከ 2014 መጨረሻ ድረስ መከራው እንዲሁ
ይቀጥላል። ዘመኑ የምንጣሮ ዘመን ነው። ከኢትዮጵያ መከራ
ፍጻሜ በኋላ የመላዋ ዓለም መከራ ደግሞ ከዚያ በኋላ
ይጀምራል።

🗣🗣በቶሎ ንስሐ ገብታችሁ የታዘዛችሁትን ቀኖና ፈፀሙ ።

ዜጎች ቀን በቀን ይታረዳሉ ። አለቃው ይበዛል። አዛዥ እንጂ ታዛዥ አይኖርም። ሁሉ አለቃ፣ ሁሉ አዛዥ ይሆናል። ፍትሕና ሕግ ስፍራቸውን ለቀው ይሰደዳሉ። ትርምስምሱ ይወጣል። የሚያዝ የሚጨበጠው ይጠፋል። ክስ አድማጭ አይኖረውም። ወታደር ግራ ይጋባል። ዜጎች አማራጭ ያጣሉ። የውስጥም የውጪም ጠላቶች መግቢያ ቀዳዳው ይሰፋላቸዋል።

በአራቱም አቅጣጫ ኢትዮጵያ ትወረራለች። ሰላም በማስከበር
በሚል ሰበብም በ2 ሃያላን ሀገራት የሚመሩ ሰባት የሙስሊም ሀገራት በኢትዮጵያ ምድር ላይ እሳት ያዘንባሉ። በአሰብ ወደብ ላይ በልዩ ሁኔታ የተከማቸው የጦር መሣሪያ በኢትዮጵያ ምድር ላይ እንደበረዶ ይዘንባል። ብዙ ፍጅትም ይሆናል።
ኦርቶዶክሳውያን በያሉበት፣ በየተገኙበት እንደከብት ይታረዳሉ። የኢትዮጵያ ምድር በደም ትጨቀያለች። የደም ጎርፍ፣ የደም አበላ በምድሪቱ ላይ ይፈሳል ።

🗣🗣ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ

ክፉ ረሃብ በኢትዮጵያ
ይመጣል። የሚበላ የሚጠጣ ከምድሪቱ ይጠፋል። ከጦርነቱ
የተረፈውን ህዝብ ረሃብ ይፈጀዋል። በስደት ምክንያት የዐቢይ ጾም የማይጾምበት ጊዜም ይመጣል። በረሃቡ ጊዜ ግን ጥቂቶችን የመትረፊያ ገዳማት ግን አሉ። ሰው የሚተርፍባቸው ገዳማትና አድባራት አሉ። ታቦተ ኢየሱስ ያለባቸው ገዳማትና አድባራት በሙሉ ሰው ይተርፍባቸዋል። በጊዜው እስከ አሁን ዝግ
የሆኑ ዋሻዎች ይከፈታሉ። የሚተርፉ ኢትዮጵያውያንም በዚያ
ይጠለላሉ። ከአሁኑ ጨውና የማይነቅዙ እህሎች አከማቹ።

🗣🗣ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ

ከዚያም ክፉ በሽታ ይመጣል። ክፉ ወረርሽኝ ይከሰታል። ወረርሽኙ የ12 ሁለት ሰዓት ዕድሜ ብቻ የሚሰጥ ክፉ በሽታ ሲሆን ይኼም ጦርነቱንና ረሃቡን ተከትሎ ይመጣል።

🗣🗣መፍትሄው ንስሐ መግባት፣ ሥጋወደሙ መቀበል ነው።

አባቶች እንዲህ አሉ: ነገ ንስሐህን የሚቀበል ካህንም ላታገኙ
ትችላላችሁና ይሄን መልእክት የማንበብ ዕድል የገጠማችሁ
ልጆቻችን ሆይ ጨርቄን፣ ማቄን፣ ሳትሉ፣ ወገቤን ደረቴን ሳትሉ፣
ምክንያት ሳትደረድሩ፣ ዕለቱኑ ዛሬውኑ ንስሐ ግቡ።

🗣🗣ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ

2015 በዘመነ ሉቃስ ንጉሱ ይመጣል። ለሳምንት ዝናብ ይዘንባል። የፈሰሰውን ደም አጥቦ ያስወግዳል። ምድር ትባረካለች።
የተረፉት ሰዎች እርስ በእርስ ይፈቃቀራሉ። ጠማማ ሰው አይኖርም። ንጉሱ ቴዎድሮስ በፍቅር ለ40 ዓመታት ይመራል።

🗣🗣 በመላው ኢትዮጵያ የምትኖሩ ልጆቻችን ሆይ እነሆ አስቀድሞ በአባቶቻችን የተነገረው ሊፈፀም ግድ ነውና ልብ ያለው ልብ ይበል። በሗለኛው ጊዜ አልሰማንም : አላየንም እንዳትሉ እነሆ ከመከራው አስቀድሞ ይህ መልዕክት ከብዙ በጥቂቱ ለአእምሮ በሚመጥን ልብን በሚገዛ መልኩ ለመላው ህዝበ ክርስቲያን አስተላልፈናል።

🗣በጸሎት የምንለምንና የምንማልድ ሁላችንንም በሰላም በመንፈስ ይጠብቀን ፍቅርንም ይስጠን ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን ፈቃዱም ሆኖ ጸሎታችንን ይቀበል ዘንድ ቀርበን እግዚአብሔርን እንለምነው!
ዐውቀን በሃብቱ እናድግ ዘንድ በእርሱም ስም እንመካ
ዘንድ...በነቢያት በሐዋርያትም መሰረት ላይ እንታነጽ ዘንድ
እንግዲህ በመንፈስ ቅዱስ እንነሳ!
ቀርበን አምላካችን እግዚአብሔርን እንለምነው ወዶ ጸሎታችንን
ይቀበል ዘንድ። አሜን!

🗣🗣🗣ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ : ንስሐ ግቡ

ቅዱስ አባ ዘወንጌል፣ ፍካሬ ኢየሱስ፣ ራዕየ ባሮክ ፣
የአባቶች ትንቢት
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

Share share share share share share

1 ሰው ለ 21 ምዕመን

ለመላው ህዝበ ክርስትያን መልዕክቱ እንዲደርስ በማድረግ የአባቶቻችንን አደራ እንወጣ

🗣ጆሮ ያለው ይስማ : ልብ ያለው ልብ ይበል

🗣መንግስተ ሰማያት ቀርባለች እና ንስሐ ግቡ

ውድድርሙኒ አስሙናኤል 21፣ ለምለምሊጊኖን 21 አካ ክስብኤል ቤቃ ጼቃ ሴቃ አልፋ ወኦ ቤጣ የውጣ ዮድ አህያ ሸራህያ ኤልሻዳይ ጸባዖት አማኑኤል እልመክኑን 21 .......

🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
Share share share share share share
ለ 21 የተዋህዶ ልጆች Share በማድረግ ክርስትያናዊ ግዴታችንን እንወጣ

4 years, 5 months ago

​​ሰማዕቱ ቅዱስ ሚናስ ከቅዱሳን ሰማዕታት አንዱ የሆነው ማር ሚና በ 4ኛውመቶ ክፍለ ዘመን ተጋድሎውን የፈፀመ ግብፃዊ ሰማዕትሲሆን ህዳር 15 ቀን የሚነበበው ስንክሳር ቅዱስ ሚናስበሚል ስያሜ ይገልፀዋል። በሶሪያ ቋንቋ ማር የሚለውቃል ‘ቅዱስ’ የሚልትርጉም ሲኖረው ለወንድ የሚሰጥቅጥያ ሲሆን ለሴት ደግሞ ማርታ ይሆናል ይሄውምቅድስት ማለት ነው። ቅዱስ ሚናስ ከእናቱ ከአውፌምያ እና ከአባቱከአውዶስዮስ…

4 years, 5 months ago

አድራሻ ለጠየቃችው
↔️ከመገናኛ ወደ ለገ ጣፎ የባስ(97 ,44) ና የታክሲ አማላጮች አሉ
↔️ከጣፎ ጋሪ ተራ ወደ ዳሌ ሰፈር የጋሪ ና የታክሲ(ቅጥቅጥ) አማራጭ አለ (በሁለቱም አማራጮች 5 ብር ነው )
በተጨማሪም የአካባቢውን ሰው ተክልዬ ወዴት ነው ብትሉ በቅን ልቦና ያመላክቷችኋል።
ሰላመ ክርስቶስ ከሁላችን ጋር ይሁን!!
@kidu1mirafeKidusanSenbet

We recommend to visit

ከእሁድ እስከ እሁድ ፈጣን የመረጃ ምንጭ!

➮የሃገር ቤት ትኩስ ትኩስ መረጃዎች
➮የአፍሪካ መረጃዎችን በሙሉ
➮የአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ሙሉ መረጃ
➮ቁጥራዊ መረጃዎች እና ዳሰሳዎች
➮ጨዋታዎችን በቀጥታ ከየስታዲየሙ

➮በስልክ ጥሪ ምንም አይንት የማስታወቂያ ስራ አንቀበልም!

ለማስታወቂያ ስራ @Promotion_4_3_3_Bot

Cʀᴇᴀᴛᴏʀ @Simera10

⓸-⓷-⓷ስፖርት በኢትዮጵያ| 2016

Last updated 3 weeks, 3 days ago

ሙሌ ስፖርት ስፖርታዊ መረጃዎችን ከእሁድ እስከ እሁድ ያገኙበታል

የሃገር ቤት መረጃ
የአውሮፓ ሊግ መረጃ
ቀጥታ ስርጭት
የዝውውር ዜና

ለማስታወቂያ ስራ @Mulesporta
@Teme_Ayu

ስልክ ቁጥር +251911857852

Last updated 1 month, 4 weeks ago

–The Best Arsenal Football Club Telegram Channel in Ethiopia.

–በኢትዮጵያ ትልቁ የአርሰናል ቴሌግራም ቻናል ነው። ስለ አርሰናል አዳዲስና ትኩስ መረጃዎች የዝውውር ፣ ዜናዎች ፣ኃይላይቶች፣ቪዲዬች፣ ትንታኔ በቀጥታ ያገኛሉ። ____________________

📥 For advert : @Mex_classic

Last updated 3 weeks, 5 days ago