Infinite Entertainment, Zero Cost: Get Your Free Books, Music, and Videos Today!

Tᴏʟᴇʜᴀ Aʜᴍᴇᴅ (ጦለሃ አህመድ)☪️

Description
Ethɪo Short Dᴀ'wa
ለአስተያየትዎ እና ለጥያቄያቹ
ጦለሃን ለማግኘት 👉🏿 @tolehaahmedbot👈🏿
ቢንት አብደላህን ለማግኘት 👉🏿 @bintabdellahbot👈🏿
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።

ያግኙን +251913134524

Last updated 1 month, 2 weeks ago

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @MKHI7

Last updated 1 month, 2 weeks ago

BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot

Last updated 3 weeks, 5 days ago

1 month, 2 weeks ago

( وللَّهِ عتقاءُ منَ النَّارِ وذلِك في كلِّ ليلة )
ለአላህም ከዕሳት ነፃ የሚላቸው ሰዎች አሉት ይህም በእያንዳንዱ የረመዷን ሌሊት ነው

ያ አላህ ነፃ ከምትላቸው ባሮችህ አድርገኝ! እናንተንም ያድርጋችሁ!  አሚን!

1 month, 2 weeks ago
  1. የለይለተል ቀድር ደረጃዎች፦

  2. ቁርኣን የወረደባት ሌሊት ነች። ጌታችን “እኛ (ቁርኣኑን) በለይለተል ቀድር አወረድነው”ብሏል። [አልቀድር፡ 1]

  3. በሷ ውስጥ የተፈፀመ ዒባዳ ከሌሎች ሌሊቶች ምንዳው የበለጠ ነው። አላህ “የመወሰኛዋ ሌሊት ከሺህ ወር በላጭ ናት” ይላል። [አልቀድር፡ 3]
  4. በሷ ውስጥ መላእክት ኸይርን ይዘው ወደ ምድር ይወርዳሉ። ጌታችን “በርሷ ውስጥ መላእክትና መንፈሱ (ጂብሪል) በጌታቸው ፈቃድ በነገሩ ሁሉ ይወርዳሉ” ብሏል። [አልቀድር፡ 4]
  5. ሌሊቷ ዒባዳ የሚበዛባት፣ ሰላም የሚሰፍንባት ለሊት ናት። ጌታችን “እርሷ እስከ ጎህ መውጣት ድረስ ሰላም ብቻ ናት” ብሏል። [አልቀድር፡ 5]
  6. የተባረከች ሌሊት ናት። ጌታችን “እኛ (ቁርኣኑን) በተባረከች ሌሊት ውስጥ አወረድነው” ብሏል። [ዱኻን፡ 3]
  7. በዚች ሌሊት አላህ በአመቱ ውስጥ ያሉ የፍጡራኑን የእድሜና የሲሳይ ልኬታዎችን ይፅፋል። “በውስጧ የተወሰነው ነገር ሁሉ ይልለያል” ብሏል አላህ። [ዱኻን፡ 4]
  8. በዚያች ሌሊት ምድር ላይ የሚኖሩት የመላእክት ብዛት ከጠጠሮች ብዛት የበዛ ነው። [አልባኒይ ሐሰን ብለውታል]
  9. ለተጠቀመባትና አጅሩን ከአላህ ላሰበ ሰው ከወንጀል መማርያ ሌሊት ነች። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- “ለይለተል ቀድርን አምኖና አስቦ የቆመ ሰው ያለፈ ወንጀሉ ይታበስለታል።” [ቡኻሪና ሙስሊም]
    ስለዚህ ይህቺን ወሳኝና እጅግ የላቀ ዋጋ ያላት ሌሊት ለማገኘት የምንችለውን ሁሉ ልንጣጣር ሌሎችንም ልናበረታታ ይገባል። ኢብኑል ቀይም ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፡- “ለይለተል ቀድር በአመት ውስጥ የምትገኝ አንዲት ቀን ብትሆን እሷን ለማገኘት ስል አመቱን ሁሉ እቆም ነበር። በ(ረመዳን) አስር ሌሊቶች ውስጥ ከሆነችማ ምን ነካህ? (እንዴት እዘናጋለሁ?!)” [በዳኢዑል ፈዋኢድ፡ 1/55]

  10. ለይለቱል ቀድር የምትገኘው በየትኛው ጊዜ ነው?

የምትገኘው በረመዷን ብቻ ነው። ከረመዷንም በመጨረሻዎቹ አስሮች ውስጥ። ነብዩ ﷺ “ይቺን ሌሊት እየፈለግኩ የመጀመሪያውን አስር ኢዕቲካፍ አደረግኩኝ። ከዚያም መካከለኛውን አስር ኢዕቲካፍ አደረግኩኝ። ከዚያም (የሆነ አካል) መጥቶኝ ‘እሷ በርግጥም የመጨረሻው አስር ላይ ናት’ አለኝ” ማለታቸው ይህን ያስረግጣል።
ይቺ ታላቅ ሌሊት እንዳታልፈን የምንችለውን ሁሉ ልንጣጣር ይገባል። ነብዩ ﷺ በሐዲሣቸው እንዲህ ብለዋል፡- “በሱ ውስጥ ከአንድ ሺ ወር የምትበልጥ ሌሊት አለች። የሷን ኸይር የተነፈገ በእርግጥም (ትልቅ ነገር) ተነፍጓል።” [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 2247]

  1. መቼ እንፈልጋት?

ይበልጥ የሚገመተው 27ኛዋ ሌሊት ናት። ይሁን እንጂ “ለይለተል ቀድርን በ23ኛዋ ሌሊት ፈልጓት” ማለታቸው እንዲሁም “ለይለተል ቀድርን በመጨረሻዎቹ አስሩ (ሌሊቶች) ፈልጓት። ከተረታችሁ በመጨረሻዎቹ 7 ላይ አትረቱ” ማለታቸው ለይለተል ቀድር ሁሌ በአንድ ሌሊት ላይ እንደማትገደብ ያስረዳል። በተለይ ደግሞ በዊትሮቹ (21፣ 23፣ 25፣ 27፣ 29) የመሆን እድሏ ሰፊ ነው። ይህን አስመልክተው ነብዩ ﷺ “ለይለተል ቀድርን ከረመዷን በመጨረሻዎቹ አስሩ (ሌሊቶች) በዊትሮቹ ፈልጓት” ብለዋል።  [ቡኻሪይና ሙስሊም]
ይህ ማለት ግን ከነጭራሹ በሸፍዕ ለሊቶችም (22፣ 24፣ 26፣ 28፣ 30) አትሆንም ማለት አይደለም። ምክንያቱም ነብዩ ﷺ “ከረመዷን የመጨረሻዎቹ አስሮች ውስጥ ፈልጓት። ዘጠኝ ሲቀረው፣ ሰባት ሲቀረው፣ አምስት ሲቀረው” ብለዋልና። ወሩ 29 ቀን ከሆነ 9፣ 7፣ 5 ሲቀር ዊትር የሚሆኑት ከመጨረሻ ወደ ኋላ ሲቆጠር ነው። ከመጀመሪያ ለሚቆጥር ግን ዊትር ሳይሆን ሸፍዕ ቁጥር ነው የሚሆኑት። ይህም ሸፍዕ ሌሊቶችም ላይ የመሆን እድል እንዳለ ያስረዳናል። ቢሆንም ግን “ከ(መጨረሻው አስር) በዊትሩ ፈልጓት” ስላሉ ዊትሩ ላይ ይበልጥ ማተኮር ይገባል።

  1. በለይለተል ቀድር ምን ይጠበቅብናል?

ዒባዳ ማብዛት። ነብዩ ﷺ “ለይለተል ቀድር አምኖና አስቦ የቆመ ሰው ያለፈ ወንጀሉ ይታበስለታል” ይላሉ። [ቡኻሪና ሙስሊም] እናም በዚች ሌሊት ታላቅነትና መደንገግ አምኖ፣ ከዚያም ለታይታ፣ ለጉራና መሰል አላፊ ኒያ ሳይሆን አጅሩን ከአላህ በማሰብ እንደ ሶላት፣ ዱዓእ፣ ቁርኣን መቅራት፣.. የፈፀመ ሰው ወንጀሉ ይታበስለታል ማለት ነው።

  1. ምልክቶቿ

  2. “በዚያን ቀን ማለዳ ላይ ፀሀይዋ ነጭ ሆና ጨረር ሳይኖራት ትወጣለች።” [ሙስሊም]

  3. በዚያን ሌሊት ዝናብ ሊዘንብ ይችላል። [ቡኻሪና ሙስሊም]
  4. ቀጣዩ ቀን አየሩ ሞቃትም ብርዳማም ሳይሆን የተስተካከለ ይሆናል። ፀሀይዋም ደካማና ቀይ ትሆናለች። [ሶሒሑል ጃሚዕ]
    እነዚህ ምልክቶች ግን አንፃራዊ ናቸው ይላሉ ሸይኹል አልባኒይ ረሒመሁላህ። በአካባቢው ባለው የአየር ሁኔታ ሊወሰን ይችላል። ስለሆነም በትክክል ለይለተል ቀድር በተከሰተበት ጊዜም እነዚህን ምልክቶች ብዙ የማያያቸው ሊኖር ይችላል።

  5. ለይለተል ቀድር ለሰጋጆች ብቻ አይደለችም!

የወር አበባ ላይ፣ የወሊድ ደም ላይ ያሉ፣ መንገደኞች፣ … የዚች ሌሊት ትሩፋት አያልፋቸውም። ማስረጃው ጠቅላይ ነውና። ባይሆን ከሶላት ውጭ ባሉ ዒባዳዎች ላይ ሊበራቱ ይገባል። በዚያች ሌሊት ዱዓእ ማብዛት ጥሩ ነው። እንዲያውም ሱፍያኑ ሠውሪይ ረሒመሁላህ “በሌሊቷ ከሶላት ይልቅ ዱዓእ እኔ ዘንድ የተወደደ ነው” ይላሉ።

  1. ለይለተል ቀድር በአይን ትታያለች?

አንዳንዶች በረመዷን የመጨረሻው አስር ሌሊት ላይ እግራቸውን ዘርግተው፣ እያወሩ ሰማይ ሰማይ ያንጋጥጣሉ። የሚጠባበቁት ተወርዋሪ ኮከብ ነው። እሱን ሲያዩ “አኑረን አክብረን” ብለው ይንጫጫሉ። ይሄ ባዶ እምነት ነው። ለይለተል ቀድር አላህ በአንዳንድ ባሮቹ ቀልብ ላይ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ የመረጋጋት ወይም የመለየት ስሜት ከማሳደሩ ውጭ በአይን የሚታይ ነገር አይደለም። የሚታየው ምልክቶቿ እንጂ እራሷ አይደለችም። ሰዎች የሚጠበቅባቸውን ከተወጡ ሌሊቱ ለይለተል ቀድር መሆኑን ባያውቁ እንኳን ትሩፋቷን አያጡም።

  1. ለይለተል ቀድር እንደሆነ ውስጡ ያደረ ሰው ምን ያድርግ?

በተለይ ደግሞ ሌሊቱ ለይለተል ቀድር እንደሚሆን ውስጣችንን ከተሰማን ይበልጥ ልናተኩርበት የሚገባን ዱዓእ “አሏሁመ ኢነከ ዐፉውዉን ቱሒቡል ዐፍወ ፈዕፉ ዐኒ” (“ጌታዬ ሆይ! አንተ በርግጥም ይቅር ባይ ነህ። ይቅር ማለትን ትወዳለህ። ስለሆነም ከኔ ይቅር በለኝ” የሚለው ነው። [አልባኒይ ሶሒሕ ብለውታል] ስለዚህ ዋናው ትኩረታችን የአላህን ይቅርታ ለማግኘት ይሁን።

  1. ግን ለምን አላህ ለይለተል ቀድርን ስውር አደረጋት?

ዑለማዎች እንደሚሉት ታላላቅ ትሩፋቶች በሚገኝባቸው የረመዷን የመጨረሻ ሌሊቶች ሙስሊሞች በዒባዳ ይበራቱና ይጠናከሩ ዘንድ ነው አላህ ይቺን ሌሊት ስውር ያደረጋት። እናም ለይለተል ቀድርን እንዳታመልጣቸው ሲጣጣሩ ለይተው ቢያውቋት ሊኖራቸው ከሚገባው በበለጠ ለዒባዳ ይተጋሉ። በዚህም ይበልጥ ይጠቀማሉ። ለይተው ቢያውቋት ግን እሷ ብቻ ላይ አነጣጥረው ሌሎቹ ሌሊቶች ላይ ይዘናጉ ነበር። እናም መሰወሯ ነብዩ ﷺ እንዳሉት ለኛ ኸይር ነው። [ቡኻሪይ]

©ኢብኑ ሙነወር

1 month, 2 weeks ago

ዱዓ ስታደርግ፤ በልብህ ውስጥ ብዙ ጉዳዮች ያሉ ሆነው ሳለ ወቅቱ አልበቃ ካለክ ዱዓህን አላህ ካንተ ይቅር እንዲልህ አድርገው
አላህ ካንተ ይቅር ካለህ ከዚያ ውጭ ያሉ ጉዳዮችህ በሙሉ ያለምንም ጥያቄ ይፈፀሙልሃል ይላሉ ኢማም ኢብኑል ቀይም ረሂመሁሏህ

ብዙ ወንድም እና እህቶች አሉህ በዚህ ረመዷን ተጨንቀው ዱዓ አድርግልን አደራ እንዳትረሳን ሀጃ አለብን ያሉህ
ብዙ ወንድም እና እህቶች አሉህ ካንተ ዱዓህን ብቻ እና ብቻ የሚፈልጉ የሆኑ
ለራስህ ለወላጆችህ ለወዳጆችህ ለወንድም ለእህቶችህ ዐለም ላይ ላሉ ሙስሊሞች ሁሉ በህይወት ያሉም ይሁኑ ያለፉ ዱዓ አድርግላቸው አድርጊላቸው
በዱዓ ላይ እንበርታ
አላህ ሆይ ይቅር ባይነህ ይቅር ማለትን ትወዳለህና ይቅር በለን አሚን
https://t.me/tolehaahmed

3 months, 2 weeks ago

⛅️ የጠዋት መልዕክት⛅️

🍂እነዚህን ነጥቦች ለሰዎች አትናገር

① የወደፊት እቅድህን አትናገር…  አንዳንዶች ለማበላሸት ይጣደፋሉና

② ደካማ ጎንህን ለማንም አትናገር… በሆነ ጊዜ አንተን ለማጥቃት ሊጠቀሙበት ይችላሉና

③ በሙከራዎችህ ላይ ምን ያህል እንዳልተሳካለህ ለሰዎች አትናገር… ምክንያቱም የሆነ እድልን ስትሞክር  ሁሌ እንደማይሳካለት ሰው አድርገው ይቆጥሩሀልና

④ ሚስጥሮችህን ለማንም አትናገር…  ይህንንም ባደረክ ጊዜ በእርግጥ ለሁሉም ሚስጥርህን ይፋ አደረክ ማለት ነው

⑤ የቀጣይ እርምጃዎችህን ለማንም አትናገር … ሁሌም ቢሆን ድምፅህን አጥፍተህ ተንቀሳቀስ… ሰዎችን ከሰራህ በኃላ አስደንግጥ ! የደረስክበት ስኬት ስላንተ እንዲናገር አድርግ !

⛅️⛅️ መልካም ንጋት ⛅️⛅️

🀄🀄ሉን👇👇 share👇
┏━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┓
@tolehaahmed
┗━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┛

3 months, 2 weeks ago

"اللهم قد تجبر "المغضوب عليهم" و"الضالين"
‏وأمعنوا قتلاً وإفسادًا في أرضك
‏اللهم رد كيدهم في نحورهم
‏اللهُمّ قاتل اليهود في جوهم، وبحرهم، وبرّهم
‏يا ربّ أرنا بهم عجائب قدرتك
‏واشفِ صدور قومٍ مؤمنين🤲🏻"

☁️ ..

"اللهُمَّ اجعلنَا ووالدينا ممن عـفوت ورضيت عنهم ، وحرمت عليهم النار وكتبت لهم الدرجات العلى من الجنة ، يـارب العـالـمـيـن"

-

☁️ ..

احتضنوا الأموات بدعائكم ..
فلا أحد يعلم بأي حال هم الآن ..

اللهُم ارحم كل غالي فقدناه وكل ميت لم يجد من يدعو له ومن سكنوا القبور ، اللهُم آنس وحشتهم ونوّر قبورهم واغفر ذنوبهم وابنِ لهم بيوتًا في الجنة اللَّهم ارحم موتانا الذين هُم بجوارك، واجعلهم في نعيمٍ لا ينفد ، وأُنسٍ لا ينضب ، وهناءٍ لا ينقطع ، اللَّهم اجعل ميعادنا بهم جناتك جنات الخلود
اللهم اغفر لنا ولوالدينا و المسلمين اجمعين.
‏‌ #ساعة_استجابة

3 months, 2 weeks ago

የአላህ ሱብሀነሁ ወተአላ ጥሪ
┈┉┅━💐🌷💐━┅┉┈

ካንተ የተብቃቃ ሁኖ ወደሱ እንድትመጣ ይፈልገል… 
የሰማይ መላኢኮች ሁሉ እሱን በማጥራት ላይ እያሉ ካንተ ግን ችላ አይልም…  አንተን መምራት የሚፈልገው ለእሱ ሳይሆን ላንተ ለራስህ ነው !  ያንተ ማፈንገጥ ከእሱ ንግስና ቅንጣትን አይቀንስም…  ያንተ ኢማንም ከንግስናው ቅንጣትን አይጨምርም ። እንደዛም ሁኖ ስታምፀው ይታገሰሀል ይለግሰሀል ፣ ወደሱ እንድትመለስ እድል ይሰጠሃል ። በተመለስክ ጊዜም ባንተ በደካማው ባሪያ መመለስ እጅግ ይደሰታል። ሱብሀን አላህ !  አሰበኽዋል ! አላህ ሱብሀነሁ ወተአላ የምድርና የሰማይ ፈጣሪ ፣ የነገስታት ሁላ ንጉስ ባንተ ደካማ በዳይ ፍጡር ወደሱ በመመለስህ ሲደሰት !
ይህ ነው የአላህ ጥሪና የአላህ እዝነት…  ታድያ ወደ አላህ የመመለሻ ጊዚያችን አልደረሰምን ?! አላህ እንዲህ ይለናል ፦

{ أَلَمْ يَأْنِ لِلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ أَن تَخْشَعَ قُلُوبُهُمْ لِذِكْرِ ٱللَّهِ }
« ለነዚያ ለአመኑት ለአላህ ተግሳጽ ልቦቻቸው ሊፈሩ ጊዜው አልቀረበምን? »

【 አልሀዲድ 16】

┈┉┅━💐🌷💐━┅┉┈
أنا مُخطئٌ أنا مذنبٌ أنا عاصي
                   هو راحمٌ هو غافرٌ هو كافي
قابلتهنَّ ثلاثةٌ بثلاثةٍ
                    ولتغلبُنْ أوصافُه أوصافي
*🌷አላህ በእሱ ቅርበት ከሚደሰቱ ባሪያዎቹ ያድርገን*

ቢንት አብደላህ

🀄🀄ሉን👇👇 share👇
┏━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┓
@tolehaahmed
┗━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┛

5 months, 2 weeks ago

ሁሉም ሰው ከሌላው በተለየ ሁኔታ የተፈተነ ይመስለዋል ። ወይም ከሌላው በበለጠ መከራ  የደረሰበት አደርጎ ራሱን ይመለከታል ።

እውነታው ግን እያንዳንዱ ሰው የራሱ የሆነ ሃሳብና መከራ አለበት ። እኛ የምንለያየው የአላህን ውሳኔ በአቀባበላችን መጠን  ልክ ነው።

አንድ ሰው ጤናን ይዞ  ገንዘብ የተቸገረ  ሊሆን ይችላል። ወይም ገንዘብ ይዞ  ልጅ ላይኖረው ይችላል  ።  ጤንነት፣ ገንዘብንና ልጆች አላህ ሰጥቶት   የልጆቹን ሳሊህነት  የተከለከለም ይኖራል ።  ልጆቹ ጥሩ ሁነውለት  ደግሞ እሱ ልጅነቱን የቲም ሁኖ አድጎ ሊሆን ይችላል። ልጅነቱን በወላጆቹ እቅፍ ሁኖ አድጎ   ደግሞ ደስተኛና የተረጋጋ  የትዳር ህይወት ላይኖር ይችላል …………

በአጠቃላይ በዚች ዱንያ ላይ ሙሉ ህይወት የለም ። ጉድለቶቻችንን  መሙላት የምንችለው  በህይወታችን ለሚያጋጥሙን ችግሮች  የአላህን  ውሳኔዎችን ስንቀበልና በነሱም  ደስተኛ ስንሆን ብቻ ነው  !!!

🌸ለአላህ በ ችሮታዎቹና  በውሳኔዎቹ ሁላ ደስታ የተሞላው ከፍ ያለ ምስጋና ይገባው🌸

ቢንት አብደላህ

🀄🀄ሉን👇👇 share👇
┏━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┓
@tolehaahmed
┗━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┛

5 months, 2 weeks ago

📌 ነቢዩላህ ዩሱፍ አለይሂ አሰላም  እስር ቤት ውስጥ  በነበሩበት ጊዜ አብሯቸው 2 ወጣቶች ነበሩ ።

ዩሱፍ አለይሂ አሰላም ከሁላቸውም የበለጠ  ውስጣቸውም የውጭ ገፅታቸው ያማረ ነበር ። ይህም እንዳለ ሆኖ ሁለቱ  ወጣቶች ቀድመዋቸው  ከ እስር ወጥተው እሳቸው ግን ለተወሰኑ አመታት እዛው ቆዩ ።

የመጀመሪያው ወጣት ወጥቶ አገልጋይ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የወጣው ሊገደል ነበር !!!

ዩሱፍ አለይሂ አሰላም ግን ከጊዜ በኃላ
ወጥተው የግብፅ ንጉስ ሆኑ !!!

ምኞቶች የሚዘገዩት ብዙ ስጦታዎችን በውስጣቸው  ይዘውልን  ሊመጡ  ስለሆኑ በ  አላህ ተስፋ በማድረግ  እንጠብቃቸው  !!!

🖊 ቢንት አብደላህ

🀄🀄ሉን👇👇 share👇
┏━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┓
@tolehaahmed
┗━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┛

5 months, 2 weeks ago

በዚህም ምክንያት አል-ሲዲቅ የሚለውን ቅፅል ስም አገኘ።
(ሐኪም ሙስተድረክ ላይ ዘግበውታል አልባኒም ሶሒሕ ብለውታል)

🍃ይህም ጠንካራ የሆነ እምነት ከትላልቅ የየቂን ፍሬዎች መካከል አንዱ ነው።
አላህ በሰውየው ላይ የኢኽላሱን እውነተኝነት፣ ነብያችንን ﷺ የመከተል እና እውነትን የመፈለግ ትጋትን ካወቀ ይህን ሰው ወደዚህ ትልቅ ደረጃ ላይ እንዲደርስ መንገዱን ያቀልለታል።
ይቀጥላል ...
Toleha Ahmed
🀄🀄ሉን👇👇 share👇
┏━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┓
https://t.me/tolehaahmed
https://t.me/tolehaahmed
            ┗━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┛

5 months, 3 weeks ago

#ቁርአንን_ለመሀፈዝ_የሚጠቅሙ_6_ምክሮች

① ►ኢኽላስ የሁሉም ነገር ቁልፍ ነው

ስራ ላይ ኢማን እና ኢኽላስን ማጣት ትልቅ ክስረት ውስጥ ያስገባል ። የለፋህበትን የደከምክበት ሁሉ በአንዴ ያወድምብሃል ። ስለዚህ ልብህን ተጫንና በውስጥህ ኢኽላስ‥ ኢኽላስ‥ ኢኽላስ እያልክ ወደ 2ተኛው ምክር‥

②► አላማ

አንድን ነገር ለመስራት አላማዬ ብለህ ከያዝክ ምንም ነገር አላማህን ከማሳካት አያግድህም ። ብቻ አንተ ውስጥህ ላይ ያለውን ፍላጎት ፣ ቆራጥነት ፣ ሀይልን እና ምኞትህን ቀስቅሰህ እችላለሁ በልና ወደ 3ተኛው ምክር‥

③ ►ትኩረት

ዛሬ ላይ መለኩል መውት መጥቶ በእርግጠኝነት ከ2 ወር በኋላ ትሞታለህ ቢልህ ምን ታደርጋለህ??

- አንዱ በ2 ወር ቁርአን ሀፍዜ እጨርሳለሁ ይላል ። ሌላው ደግሞ በ1 ወር ሀፍዤ እጨርስና ቀሪውን ኢባዳ ብቻ አደርጋለሁ ይላል‥
ይህ ሁሉ ችሎታ እና ሀይል አሁን የት አለ?

๏ ሰው በተሰጥኦ ምናምን ይለያል ብለህ አታስብ ። በተወሰነ % ቢኖርም ግን ሁላችንም ውስጥ ምኞት ፣ ፍላጎትና ጉጉት አለ ። እያንዳንዳችንም ፍላጎታችን ላይ መድረስ እንችላለን ብለህ እራስህን አሳምነህ ወደ 4ተኛው ምክር‥

►የምትሀፍዝበትን ጊዜ ወስነህ ለየው

አብዛኛውን ጊዜ ቁርአን ለመሀፈዝ የተሻለ ጊዜ ነው የሚባለው ሱሁር የሚበላበት ጊዜ ነው ። ከዛ ቀጥሎ ከፈጅር ሰላት በኋላ ነው ።
ሱሁር ላይ የተሻለበት ምክኒያት : የሰው ልጅ በዛ ሰአት ከእንቅልፉ ሲነቃ አእምሮው ለመቀበል ክፍትና ዝግጁ ስለሚሆን ነው ።

⑤ ►አንድ አይነት ሙስሀፍ/ቁርአን ብቻ መጠቀም

የአንድ አንድ ሙስሀፎች ገፅ አቀማመጥ ይለያያል ። እዚህኛው ሙስሀፍ ገፅ ላይ ያየኸው አንቀፅ በዛኛው ሙስሀፍ ገፅ ለይ ደግሞ ሌላ አንቀፅ ሊኖር ይችላል እና ሁሌም የምትቀራበትን ሙስሀፍ አዘጋጅ ።

⑥ ►ወንጀሎችን መራቅ

የወንጀል ፅልመት እና የእውቀት ብርሃን በአንድ ቦታ ላይ ሊሰበሰቡ አይችሉም ።

- የሰው ልጅ ወንጀል ሲሰራ ወንጀሉ ሀዘን ፣ ጭንቀት እና የመሰሰሉ ነገሮች ስለሚያመጣበት ሀሳቡ ሁሉ ይቀየርና ከበጎ ነገራቶች ያርቁታል ። ስለዚህም በተቻለን አቅም ወንጀል ከሚባሉ ነገሮች መራቅ ይኖርብናል ።

አላህ ያግራልን‥🀄🀄ሉን👇👇 share👇
┏━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┓
https://t.me/tolehaahmed
https://t.me/tolehaahmed
            ┗━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┛

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።

ያግኙን +251913134524

Last updated 1 month, 2 weeks ago

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @MKHI7

Last updated 1 month, 2 weeks ago

BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot

Last updated 3 weeks, 5 days ago