Welcome To Amharic films Best Place To find Amharic Movies
አዳዲስ እና የድሮ አማርኛ ፊልሞችን እና አማርኛ ተከታታይ ድራማዎችን ለማግኝት ቻናላችንን Join ይበሉ ።
Share:- @Amharic_Films
ለማስታወቂያ - @Abusheymc & @Alpha6249
Buy ads: https://telega.io/c/Amharic_films
Last updated 1 year, 8 months ago
ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም
- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት
ለማስታወቂያ ስራ --> @Aymu_xo
Last updated 3 weeks, 1 day ago
╔╦╦═╦╔╦═╦═╦═╗
║ እንኳን ደህና መጡ | |
╚══╩═╩═╩╩╩╩═╝
➟ እንኳን ወደ ትልቁ የሊቨርፑል ( መርሲሳይድ) ቻናል በደህና መጡ ።
◉ ስለ ሊቨርፑል ◉
? ዝውውሮች
? ውጤቶች
? የጨዋታ ፕሮግራሞች
? እንዲሁም የተጨዋቾች ግለ ታሪክ
? ጨዋታዎችን በቀጥታ ወደናንተ የምናደርስ ይሆናል።
Owner:- @hackersolo0⭐️
Last updated 2 months, 2 weeks ago
ለዘይድ ኢብኑ ሳቢት የቁርአን ማህበር እና ለሀሩን ሚዲያ ሽልማት ተበረከተላቸው!
- ሀሩን ሚዲያ፣ የካቲት 3/2017
መቀመጫውን በአሜሪካን ሀገር ያደረገው ተቅዋ ሀበሻ አለም አቀፍ የሙስሊም የሴቶች ማህበር ሁለተኛው አለም አቀፍ የቁርአን እና የአዛን ውድድር አዘጋጅ ለሆነው ዘይድ ኢብኑ ሳቢት የቁርአን ማህበር፣ ለኡስታዝ ኑረድን ቃሲም እና የቁርአን ውድድሩ የተሳካ እንዲሆን በሚዲያ በኩል ትልቅ አስተዋጽኦ ላበረከተው ሀሩን ሚዲያ የምስጋና ሽልማት አበርክቷል።
ሁለተኛው አለም አቀፍ የቁርአን እና የአዛን ውድድር የሀገራችን ኢትዮጵያን ሌላኛውን ገፅታ ለአለም ያስተዋወቀ መሆኑን የገለፁት የተቅዋ ሀበሻ ተወካዮች ለዚህም አዘጋጁ ዘይድ ኢብኑ ሳቢት የቁርአን ማህበርና የማህበሩ መስራች እና ስራ አስኪያጅ ኡስታዝ ኑረድን ቃሲም ምስጋና የሚገባቸው በመሆኑ የዛሬው ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
ውድድሩ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ በሚዲያ በኩል የተለያዩ ሽፋኖችን በመስጠት ለውድድር ስኬታማ መሆን አስተዋጽኦ ላበረከተው ሀሩን ሚዲያ የምስጋና ሽልማት ተበርክቶለታል።
የውድድሩ አዘጋጅ ዘይድ ኢብኑ ሳቢት የቁርአን ማህበር መስራች እና ዋና ስራአስኪያጅ አለም አቀፍ ዳኛ ኡስታዝ ኑረድን ቃሲም ባደረጉት ንግግር ተቅዋም ሀበሻ ውድድሩን በተለያየ መንገዶች ሲያግዙ እንደነበር ገልፀው ዛሬ ለተደረገላቸው የምስጋና ሽልማት አመስግነዋል።
ኡስታዝ ኑረድን አክለውም ሀሩን ሚዲያ ውድድሩ ገና ወራቶች ሲቀሩት ጀምሮ ያለምንም ስምምነት ውድድሩ የራሴ ነው በማለት ያደረገው አስተዋጽኦ ለታሪክ የሚቀመጥ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ከሚዲያው በተጨማሪ የሀሩን ሚዲያ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ ጋዜጠኛ አብዱረሂም አህመድ የቁርዓን ውድድሩ እንዲሳካ በተለይ ዲያስፖራውን በማንቃት ትልቅ ስራ መስራቱን ኡስታዝ ኑረዲን ገልጿል።
የሀሩን ሚዲያ የሀገር ውስጥ ስቱዲዮዎች ስራ አስኪያጅ ወንድም ባህሩ አባስ ባደረገው ንግግር ሀሩን ሚዲያ የሙስሊሙን ጉዳዮች ቀዳሚ አጀንዳው አድርጎ የሚሰራ ወደፊትም ይህንኑ አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጿል።
ተቅዋ ሀበሻ አለም አቀፍ የሙስሊም ሴቶች ማህበር በዛሬው ዕለት ከሰጠው የምስጋና ሽልማት በተጨማሪ በቁርአን ውድድሩ የሴቶችን ሽልማት መሸፈኑ ተገልጿል።
© ሀሩን ሚዲያ
"መስጂዱ በመኖሩ የውሃ ችግራችንን ቀርፎልናል"
▪ በለገጣፎ ለገዳዲ የሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች
- የክርስትና እምነት ተከታዮች የመሰከሩለት በለገጣፎ ለገዳዲ ክፍለከተማ የሚገኘው ሱመያ መስጂድ
- ሀሩን ሚድያ ሕዳር 19/2017
በለገጣፎ ለገዳዲ ክፍለከተማ ህጋዊ ካርታ ያለው ሱመያ መስጂድ በፍርድ ቤት መስጂዱ እንዲነሳ ያለአግባብ ውሳኔ መሰጠቱን አስመልክቶ በቀኑ ክፍለ ጊዜ ዘገባ መስራታችን ይታወሳል።
ሀሩን ሚድያ በለገጣፎ ለገዳዲ የሚኖሩ የክርስትና እምነት ተከታዮች ከመስጂዱ ምን አገልግሎት እያገኙ እንደሚገኝ ጠይቀን በምላሻቸው ሱመያ መስጂድ አካባቢው ላይ ውሃ ባለመኖሩ የከርሰ ምድር ውሃ በማውጣት ያለምንም ክፍያ ከግቢው ውጪ ባንቧ በመዘርጋት የአካባቢው ነዋሪዎችን የውሃ ችግር እየቀረፈ ይገኛል ብለዋል።
በለገጣፎ ለገዳዲ የሚገኘው ከ2014 ዓ.ል ጀምሮ ህጋዊ ካርታ ያለው ሱመያ መስጂድ ያለምንም የእምነት ልዩነት በደንበል ጣፎ ወረዳ ሮዚታ ሪል ስቴት አካባቢ ለሚገኙ ነዋሪዎች የነፃ ውሃ በማቅረብ የአካባቢውን የውሃ ችግር እየፈታ እንደሚገኝ ነዋሪዎቹ የገለፁ ሲሆን ይበልጥ ተጠቃሚዎቹ ደግሞ የክርስትና እምነት ተከታይ ወገኖቻችን መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።
ሱመያ መስጂድ አስመልክቶ አንዳንድ የመስጂዱ መኖር ያላስደሰታቸው አካላት መስጂዱ እንዲነሳ ጥያቄ አቅርበው የነበረ ቢሆንም መስጂዱ ህጋዊ ነው አይነሳም በሚል ከተማ አስተዳደሩ ገልፆ አንደነበር ኮሚቴዎቹ ገልጸዋል።
በ2001 ዓ.ል ካሳ የወሰደ አርሶአደር መስጂዱ 1000 ካሬ ሜትር ወስዶብኛል በሚል ክስ መስርቷል።
ፍርድ ቤት በነበረው ክርክርም የመስጂዱ ካርታ ህጋዊ መሆኑንና ለገበሬው ካሳ መከፈሉን በማስረጃ ቢያቀርብም ፍርድ ቤቱ መስጂዱ እንዲነሳ በሚል ያለአግባብ ውሳኔ መወሰኑን የመስጂዱ ኮሚቴዎች ተናግረዋል።
የመስጂዱ ኮሚቴዎች የመስጂድ ጉዳይ የህዝብ ስለሆነ ለሸገር ከተማ አስተዳደርና ለለገጣፎ ለገዳዲ ክፍለከተማ አስተዳደር መስጂዱን በተመለከተ አስተዳደራዊ ዉሳኔ እንዲሰጡ መጠየቃቸውን ለሀሩን ሚድያ ገልፀዋል።
© ሀሩን ሚድያ
የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የቦርድ አመራሮች የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት በመገኘት የጉብኝትና የልምድ ልውውጥ መርሀግብር አከናወኑ!
_ሀሩን ሚድያ ሕዳር 19/2017፤አዲስ አበባ
በአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አዘጋጅነት “ትብብርና አብሮነትን ማጎልበት ለዘላቂ ሰላም" በሚል መሪ ቃል የጉባኤው የቦርድ አመራሮች በአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በመገኘት የጉብኝትና የልምድ ልውውጥ መረሃ ግብር አከናውኗል።
የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ፕሬዝደንት እና የጉባኤው ም/የቦርድ ሰብሳቢ ሼህ ሱልጣን ሀጂ አማን ኤባ ባደረጉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር እንደዚህ አይነት ጉብኝት እና የልምድ ልውውጥ መድረክ ያለንን ግንኙነት የበለጠ ያጠነክረዋል ብለዋል።
የመረሃ ግብሩን ዋና አላማ ያብራሩት የአዲስ አበባ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊ መጋቢ ታምራት አበጋዝ የአዲስ አበባ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ከሚያከናውናቸው ተግባራት አንዱ በሃይማኖት ተቋማት መከካል የአብሮነትና የወንድማማችነት እሴቶቻቻንን ማጠናከር በመሆኑ የጉባኤው የቦርድ አባላት በየእምነት ተቋማት በመገኘት የጉብኝትና ልምድ ልውውጥ መርሀግብር እያካሄዱ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የጉባኤው የቦርድ ሰብሳቢ ብጹዕ አቡነ ሄኖክ በበኩላቸው አሁን ያለው ትውልድ መገፋፋትን በመተው አንድነቱን እንዲያጠናክር ትኩረት ሰጥተን ልንሰራ ይገባል ብለዋል።
በመረሃ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ዋና ፀሐፊ ሼህ ሁሴን በሽር ም/ቤቱ ከተመሰረተበት ጀምሮ በመዲናችን አዲስ አበባ ያከናወናቸውን እና እያከናወናቸው ያሏቸውን መንፈሳዊ እና ማህበረሰብ ተኮር ስራዎችን በተመለከተ የም/ቤቱን ልምድ ለአባቶች አቅርበዋል።
የልምድ ልውውጡ ተሳታፊ የሆኑ የተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤን ወክለው የተገኙ አባቶች በአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ባዩት ነገር መደሰታቸውን ገልጸው ለትውልዱ ይሄን ሰላማዊ ግንኙነት አጠናክሮ ማስተላለፍ እንደሚያስፈልግ በመጥቀስ እስከታችኛው መዋቅሮች ድረስ በመውረድ ሥራዎችን ለትውልድ ማስተላልፍ እንደሚገባ ተናግረዋል።
“ትብብርና አብሮነትን ማጎልበት ለዘላቂ ሰላም በሚል መሪ ቃል” በሃይማኖት ተቋማት መከካል የአብሮነትና የወንድማማችነት እሴቶችን ለማጠናከር የሚደረገው ጉብኝት እና ልምድ ልውውጥ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን ከዚህ ከቀደም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጉብኝት እና ልምድ ልውውጥ መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን በቀጣይም በሌሎች የጉባኤው አባል ቤተ ዕምነት የሚከወናወን መሆኑ ተገልጷል።
_ሀሩን ሚድያ በዝግጅቱ በመገኘት ያጠናቀርነውን የቪድዮ ዝግጅት በአላህ ፍቃድ ወደናንተ ሚያደርስ ይሆናል።
©ሀሩን ሚድያ
ለሀላባ ዘመናዊ ኢንተርናሽናል ስቴዲየም ግንባታ ፈረሱን ለሰጠው አርሶ አደር ነዋሪነቱን ዱባዩ ካደረገ ባለሀብት ሌላ ከፍ ያለ የፈረስ በስጦታ ተበረከተለት!
- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ ፣13/2017
ለሀላባ ዘመናዊ ኢንተርናሽናል ስቴዲየም ግንባታ ፈረሱን ለሰጠው አርሶ አደር በዱባዩ ዲያስፖራ አ/ሹኩር ናስር ሌላ ከፍ ያለ ፈረስ በስጦታ ተበረከተለት።
ነዋሪነቱ በዱባይ ያደረገው ወጣት አብዱሽኩር ናስር በክልሉ ርዕስ መስተዳደርና አቶ እንዳሻው ጣሰውና በዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙሂዲን ሁሴን የተመራው ልዑክ ለስቴዲየሙ ገቢ ማሰባሰቢ ዱባይ በሄዱበት ወቅት ይሄን ታሪክ በመስማቱና ህዝቡ ለልማቱ ያለው ቁርጠኝነት ውስጤን ስለነካኝ በራሴ ለስቴዲየሙ ቃል ከገባሁት ገንዘብ በተጨማሪ ለዚህ የልማት አርበኛ አርሶ አደር በክብር ለመሸለም ቃል ገብቼ ቃሌን በዛሬው እለት የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙሂዲን ሁሴንና ሌሎች አስተባባሪ አካላት በተገኙበት ፈርሱን አስረክቢያለው በማለት ገልጿል።
አያይዞም ወጣቱ በዚህ ፕሮጀክት ላይ ሁሉም ልማት የሀላባ ወዳጅና ተወላጅ ፕሮጀክቱ እስኪጠናቀቅ ድጋፉን አጠናክሮ መቀጠል አለበት በማለት መልዕክቱን አስተላልፏል።
የሀላባ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙሂዲን ሁሴን በበኩላቸው ይህ ወጣት ዲያስፖራ ያደረገውን ድጋፍ አድንቀው በሀላባ ህዝብ ስም አመስግነዋል አስተዳዳሪው ሁሉም ህዝብ ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት ንቁ ተሳትፎ ማድረጉን አውስተው አሁንም እስከመጨረሻው ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
- ሀሩን ሚዲያ ደቡብ ስቱዲዮ ስፍራው ተገኝቶ ያጠናቀረውን የቪዲዮ ዘገባ በተከታይ ወደናንተ የሚያደርስ ይሆናል።
© ሀሩን ሚዲያ
Welcome To Amharic films Best Place To find Amharic Movies
አዳዲስ እና የድሮ አማርኛ ፊልሞችን እና አማርኛ ተከታታይ ድራማዎችን ለማግኝት ቻናላችንን Join ይበሉ ።
Share:- @Amharic_Films
ለማስታወቂያ - @Abusheymc & @Alpha6249
Buy ads: https://telega.io/c/Amharic_films
Last updated 1 year, 8 months ago
ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም
- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት
ለማስታወቂያ ስራ --> @Aymu_xo
Last updated 3 weeks, 1 day ago
╔╦╦═╦╔╦═╦═╦═╗
║ እንኳን ደህና መጡ | |
╚══╩═╩═╩╩╩╩═╝
➟ እንኳን ወደ ትልቁ የሊቨርፑል ( መርሲሳይድ) ቻናል በደህና መጡ ።
◉ ስለ ሊቨርፑል ◉
? ዝውውሮች
? ውጤቶች
? የጨዋታ ፕሮግራሞች
? እንዲሁም የተጨዋቾች ግለ ታሪክ
? ጨዋታዎችን በቀጥታ ወደናንተ የምናደርስ ይሆናል።
Owner:- @hackersolo0⭐️
Last updated 2 months, 2 weeks ago