ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።
ያግኙን +251913134524
Last updated 1 month, 2 weeks ago
ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም
- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት
ለማስታወቂያ ስራ --> @MKHI7
Last updated 1 month, 2 weeks ago
BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot
Last updated 3 weeks, 5 days ago
ወንድምኽን ለመቃወም፣
ክፉ አሳብ በተነሣብኽ ጊዜ ጸልይ፤
በአንተ ላይ የሠራዉን ክፋት፣
[ከውስጥኽ] ልታስወግደው የሚቻልኽም
በጸሎት ነው፤
👉 ለሰው ልጆች ኹሉ
ወንድማዊ የኾነ ፍቅር፥
በአንተ ውስጥ እንዲያድግ መንገዱ ይኼው ነው።
ለሰው ልጆች መጸለይ ስትጀምር፣
ወንድማዊ ፍቅር በአንተ ውስጥ
ተፀንሶ ይወለዳል፤
ያድጋልም፤
አንድ ሰው ክፉ ነገር ሲፈጽምብህ፥
ለርሱ ትሑት እና በጎ ሰው ኹንለት፤
በትሕትና ቅረበው፤
ከሥጋ ፈተናም ታድነዋለኽ።
[{ከአበው አንዱ}]
'ነፍስኽ'
የእግዚአብሔርን ቃል፣
ማንበብ ስትሰለች፣
ቃለ እግዚአብሔር መስማት፣
ደስ የማይላት ሲኾን እና ሲያስጠላት፣
እንዲኹም፦
መንፈሳዊ ተግሣፅን፣
ስታቃልል ካየሃት፣
👉 በክፉ ደዌ ላይ እንደ ወደቅኽ ተገንዘብ፤
'ሰዎች'
የሞትን ፍሬ የሚቀጥፉበት፥
መጀመሪያው ይኽ ነውና።"
[ ('ከበረሃውያን አበው') ]
'ሰይጣን'
በልብህ ውስጥ 'ክርስቶስ' መኖሩን እና አለመኖሩን ዐያውቅም፤
.ስትቆጣ፣ ስትበሳጭ ባየህ ጊዜ፣
ስትጮህ፣
ስትምል፣
በቊጣ ስትናገር፣
ዋዛ ፈዛዛ ስትናገር፣ ... ሌላም ሌላም ሲያይብህ፥
. አጅሬ ሰይጣን፦
'እግዚአብሔር' በአንተ ዘንድ እንደሌለ ያውቃል።
. ያን ጊዜም የውጭውን እና
የውስጡን ሰውነትኽን ይገዛል።
. በልብኽ ውስጥም ክፉ ያሳስብኻል፤
. መብራት እንደሌለው ቤት ያደርግኻል፤
. በውስጥኽ ያለውን በርብሮ ይወስድብኻል።
[ የከበረ አባ ቢልስ ]
ከክፉ ሰዎች እና ከሰይጣን ወጥመድ የምናመልጥበት መፍትሔ [መንገድ]፦
👉 ጸሎት፣
👉 ትሕትና፣
👉 ንስሓ ናቸው።
"የስድብ መንፈስ ነቅዑ [ምንጩ፣ መነሻው]፣
በሌሎች ላይ መፍረድ ነው"
ቅዱስ ኒፎን
"ጸሎት"ን የማታፈቅር ሰው ከሆንክ፥
ምንም ዓይነት በጎ ነገር በውስጥኽ እንደማይኖር ዕወቅ፤
ወደ እግዚአብሔር የማትጸልይ ከሆነ፣
በመንፈሳዊነትኽ ሞተኻል፣ ...
የውስጥ ሰላምም አይኖርኽም፣
የክፉ ሰዎች እና የአጋንንት መጫወጫም ትኾናለህ፣...
ሕይወትም የለኽም፣...
{[ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ]}
ድርሳነ ኤልያስ ነቢይ
ተርጓሚ፦ መ/ር ተስፋ ሚካኤል ታከለ
፳፻፭/2015 ዓ.ም.
🙏 እግዚአብሔርን ማምለክ አያሳፍርም፤ አንገት አያስደፋም፤
. ታላላቅ በተባሉ ምድራዊ መድረኮች ላይ ስሙን መጥራት አያሸማቅቅም፤
. የሠረቁ እና የዘረፉ፣ የገደሉ እና ያስገደሉ፤ በግፍ እና በበደል ተግባራቸው የገዘፈ የወንጀል ታሪክ ያላቸው እና የንጽሐንን ደም ያፈሰሱ ሰዎች በአደባባይ ከእኛ በላይ ላሳር ብለው በሚንደላቀቁበት ምድር፣
. የእግዚአብሔርን ስም እየጠሩ፣ ራሳቸውን፣
ሀጋራቸውን እና ሕዝባቸውን እንዲባርክላቸው፣ እንዲቀድስላቸው እየተማጸኑ መኖር፣
ክብርን ለመውረስ ያበቃ እንደ ኾነ እንጂ፣ ክብርን አያስነጥቅም።
. እግዚአብሔርን ማምለክ እንጂ ማታለል አይቻልም፤ ማሞኘትም መሸንገልም አይታሰብም።
[ የዘለዓለም ሕይወት እምነት ሥነ ምግባራዊ ፋይዳ ፤ በደበበ ጤናው ፤ ገጽ 24/29 ፤ 2013 ዓ.ም.]
🌝 አንተ በየዕለቱ ጠዋት ጠዋት ከእንቀልፍ ስትነቃ የምትጨነቀው ስለ ምንድር ነው!?!
🤧 የምትጨነቀው ፊትኽን መታጠብኽ!?
☕️ ቁርስኽን መብላትኽ!?
👖👞👜 ልብስኽን መልበስኽ እና ለመሔድ መዘጋጀት!?!
🌓 የቀን ተቀን ሕይወትኽ ነውን!??
ወይስ የመጀመሪያ ጒዳይኽ፦
🛐 ዕለቱን በጸሎት፣ በንባብ እና በተመስጦ፣ ከእግዚአብሔር ጋር መጀመር ነውን 🤔...
👉 እንደዚኽ ዓይነቱ ጒዳይ ላይ አንዳንዶች 'ለመጸለይ ጊዜ የለኝም'🕑 ይላሉ።
😏 እኔ ግን፣ እውነተኛ ምክንያት ነው ብዬ አላስብም።
👍 አንተ ግን ጸሎትኽን እና ተመስጦኽን ከአስቀደምክ፣ ያ አጣኊት የምትለው ጊዜኽን ታገኘዋለኽ።
. ሞክረው እስኪ
😊 ስለ ኾነም፦ በኹሉም ነገር ላይ ለእግዚአብሔር ቅድሚያ ስጥ።
ኦ ፡ ድንግል ፡ ለውሳጥያትየ ፡ ሀቢ ፡ አዕይንተ ፡ ጠበብ ፡ ወአእምሮ፤
እምገነተ ፡ መጽሐፍ ፡ ፍሬ ፡ አኮቴትኪ ፡ ለተገብሮ(ለአረሮ)፤
ተመሲልየ ፡ ንህበ ፡ ክንፈ ፡ ኅሊናየ ፡ በአሰርሮ፤
ጽጌ ፡ ውዳሴኪ ፡ እቅሥም ፡ ወአስተጋብእ ፡ ማእረሮ፤
ዘያስተፌሥሖ ፡ ለልብኪ ፡ ወለ ኅሊናኪ ፡ ዘያሠምሮ።
"ድንግል፡ ሆይ!
. ከ 'አትክልት፡ መጽሐፍ' የሚገኝ፡ የምስጋናሽን፡ ፍሬ፣
. 'መዓር' ለመሥራት፡ እንደ፡ ንብ፣
ክንፈ፡ ልቡናዬን፣
ክንፈ፡ ኅሊናዬን፡ በመዘርጋት፣
. ፈጽሞ፡ ልቡናሽን፡ የሚስደስተዉን፡ የምስጋናሽን፡ አበባ፡ እቀስም፡ ዘንድ፣
. መዓዛ፡ ምስጢሩንም፡ እሰበስብ፡ ዘንድ፣
. ለውሳጣዊ ልቡናዬ፣ የጥበብ፡ እና፡ የዕውቀት፡ ዓይኖችን፡ ስጭ።"
፧፧፧ እንዚራ ስብሐት፤አባ ጊዮርጊስ ዘኢትዮጵያ(ዘጋሥጫ) ፧፧፧
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።
ያግኙን +251913134524
Last updated 1 month, 2 weeks ago
ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም
- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት
ለማስታወቂያ ስራ --> @MKHI7
Last updated 1 month, 2 weeks ago
BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot
Last updated 3 weeks, 5 days ago