ቤተ መጻሕፍት

Description
"መጻሕፍት፡ ለሰው ልጅ መድኀኒት የታዘዘባቸው የማዘዣ ወረቀት መኾናቸዉን ተገንዝባችኊ አንቡቧቸው።"
('ርጢን' ገጽ ፲፫)፧፧፧፧

የ'ቤተ መጻሕፍቱ' ሊንክ
https://t.me/betemetsihaf

ለማንኛውም አስተያየት https://t.me/getnetfekadu
We recommend to visit

Welcome To Amharic films Best Place To find Amharic Movies

አዳዲስ እና የድሮ አማርኛ ፊልሞችን እና አማርኛ ተከታታይ ድራማዎችን ለማግኝት ቻናላችንን Join ይበሉ ።
Share:- @Amharic_Films

ለማስታወቂያ - @Abusheymc & @Alpha6249

Buy ads: https://telega.io/c/Amharic_films

Last updated 1 year, 8 months ago

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @Aymu_xo

Last updated 3 weeks, 1 day ago

╔╦╦═╦╔╦═╦═╦═╗
║ እንኳን ደህና መጡ | |
╚══╩═╩═╩╩╩╩═╝
➟ እንኳን ወደ ትልቁ የሊቨርፑል ( መርሲሳይድ) ቻናል በደህና መጡ ።
◉ ስለ ሊቨርፑል ◉
? ዝውውሮች

? ውጤቶች

? የጨዋታ ፕሮግራሞች

? እንዲሁም የተጨዋቾች ግለ ታሪክ

? ጨዋታዎችን በቀጥታ ወደናንተ የምናደርስ ይሆናል።

Owner:- @hackersolo0⭐️

Last updated 2 months, 2 weeks ago

4 weeks ago

ሰላመ እግዚአብሔር ከኹላችን ጋር ይኹን።

እንኳን ለጾመ ነነዌ አደረሳችኊ፤ አደረሰን።

. ተምሮ ማስተማር ሰንበት ት/ቤት፣
ዕለታተ ጾመ ነነዌን በየዓመቱ እንደሚያሳልፈው፣

. ዘንድሮም፦
👉 በጸሎት/በምሕላ፣
👉 ገድለ ቅዱሳንን በመስማት፣
👉 ትምህርት ቃለ ምእዳን እና ቡራኬ ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በመቀበል፣

✳️  ዕለታቱን እንሳልፍ ዘንድ፣
ሰንበት ት/ቤታችን
ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

እናንተም ኑ፤
ለሌሎችንም ጥሪውን ያስተላልፉ።

ከየካቲት ፫/ 3 ሰኞ እስከ የካቲት ፭/5 ረቡዕ፤

ጠዋት 1፡30 - 11፡00
. 1:30 -6:00=> ክፍል ፩፣፪እና ፫ ጸሎታት ይደረሳል
. 6፡00-8፡00 => ሥርዐተ ቅዳሴ ይገባል
. 8፡30-11፡00 => ገድላት፣ ድርሳናት፣ ተኣምራት፣... በሙሉ ይነበባል

[በአመቾት ሰዓት እና ቀን መሳተፍ ይችላሉ]

በምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም፣
የተምሮ ማስተማር ሰንበት   ት/ቤት።

ሰላመ እግዚአብሔር ከኹላችን ጋር ይኹን።

1 month ago

"ረጅም ሰዓት(ጊዜ)  በጸሎት አሳለፍሁ፣
ቅዱሳት መጻሕፍትንም አነበብኊ፣...
ነገር ግን አንዳች ነገር አላገኘሁም
" አትበል፤

አንድ ነገር እንዳገኘህ ርግጠኛ ኹን፤

#ከእግዚአብሔር ጋር ያለ ማቋረጥ ከመገናኘት የበለጠ፣
እንደ ምን ከፍ ያለ ነገር ሊገኝ ይችላል!?!

[{ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው}]

https://t.me/betemetsihaf

1 month ago

...

. ሰዎች ላይቀበሉህ ይችላሉ፤
ወይም ሐሳብኽን ላይረዱህ፣
ቦታ ላይሰጡህ ይችላሉ፤

. በእጅህ ላይ ያለው ሙሉ በሙሉ አመድ ኾኖ ልታገኘው ትችላለህ፤

. ሰዎች፦
ሊጠሉህ፣
ሊያሙህ፣
ወይም
ስም ሊያወጡልህ፣
አልያም ሊስቁብህ/ሊሳለቁብህኽም ይችላሉ፤

. በሕይወትህ ውስጥ ትልቁ ስሕተት፣
ለኹሉም ሰው ትክክለኛ ሆኖ ለመታየት መሞከር ነው።

. መልካም ብትሆን ክፋዎች ይጠሉኻል።

. ዐዋቂ ብትሆን ዐላዋቂዎች፦
ባዶነታቸውን ስለምትገልጥባቸው፣
አብዝተው ይጸየፉኻል።

. ብርሃናዊ ራዕይ ቢኖርህ፣
የጨለምተኞችን ጨለማ ስለምታሳይ፣
መኖርህ ያንገበግባቸዋል።

. ነጻ አውጭ  ብትሆን፣
ጨቋኞች ያሳድዱኻል።

👉 ምናለፋኽ
በዓለም ስትኖር፦
በሙሉ ድምጽ ልትወደደም፣ ልትጠላም አትችልም።

🛐ከምንም በላይ #በእግዚአብሔር_ፊት
ትክክል ኹን!!🛐

😊 አንድ ነገር ልንገርህ፦

. በሕይወትህ ማንንም አትውቀስ፤

ጥሩ ሰዎች፦ ደስታን ይሰጡኻል!!
መጥፎ ሰዎች፦ ልምድ ይሆኑኻል!!
ክፉ ሰዎች፦ ማስጠንቀቂያ ይሆኑኻል!!
ምርጥ ሰዎች፦ ትዝታ ይሆኑኻል!!

. …

3 months, 1 week ago
[#**ኅዳር**](?q=%23%E1%8A%85%E1%8B%B3%E1%88%AD)[**#ጽዮን**](?q=%23%E1%8C%BD%E1%8B%AE%E1%8A%95)

#ኅዳር#ጽዮን

"ጽዮን" ማለት "ጸወን አምባ፣ መጠጊያ" ማለት ነው

ጽዮን የሚለው ስም
. በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራ እና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል
. በትንቢታዊ ምስጢሩ ግን
ድንግል ማርያም
ቤተ ክርስቲያን እና
ዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል

ኅዳር 21 ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በተለየ መልኩ የምናከብርበት ምክንያት፡-

  1. በብሉይ ኪዳን ታቦተ ጽዮን የፈጸመችውን ልዩ ልዩ ገቢረ ተኣምራትን በማሰብ

  2. ቀዳማዊ ምኒልክ ከዐሥራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል የበኲር ልጆች ጋር ሊቀ ካህናቱን አዛርያስን እና ታቦተ ጽዮንን ይዞ አክሱም የደረሰበት ዕለት በመሆኑ

  3. በሦስት መቶ ሠላሳ ዓመተ ምሕረት በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመነ መንግሥት "ክርስትና" የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት #ይሁን ተብሎ ዐዋጅ የታወጀበት

  4. ዘካርያስ በተቅዋመ ወርቅ ምሳሌ ራእይ ያየበት

  5. ነቢዩ ሕዝቅኤል በተቆለፈች ቤተ መቅደስ

  6. ዕዝራ በቅድስት ሀገር ምሳሌ ራእይ ያየበት

  7. አብርሃና አጽብሃ በወርቅ እና በዕንቁ ያሠሩት ባለ ዐሥራ ሁለት ክፍል ቤተመቅደስ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት

  8. በዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዮዲት ጉዲት አብያተ ክርስቲያናትን ስታቃጥል
    ታቦተ ጸዮንን ይዘው ወደ ዝዋይ ሐይቅ ከተሰደዱ በኋላ
    ዘመነ ሰላም ሲጀመር አክሱም በነበሩ ካህናት አስታዋሽነት ከዝዋይ ወደ አክሱም የገባችበት ዕለት በመሆኑ

በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ከፍ ባለ መንፈሳዊ በዓል ይከበራል፡፡

ይኽ ሲባል ግን በዓሉ የሚከበረው
በአክሱም ጽዮን ማርያም ብቻ ነው ማለት ሳይሆን፣
ታቦተ እግዝእትነ ማርያም ባለችበት ቦታ ሁሉ መከበሩን #ልብ ማለት ያስፈልጋል፡፡

ምልጃዋ አይለየን?

3 months, 1 week ago

#ፈሪሃ#እግዚአብሔርን(እግዚአብሔርን መፍራትን) ገንዘብ ስታደርግ

ገንዘብ ካላቸው በላይ ባለጠጋው አንተ ነኽ፤

'እንዴት' ትለኝ ይኾናል፤

እኔም 'እንዲኽ ብዬ' እመልስልኻለው፤

የባለጠጎቹ ገንዘብ ያልቃል፤
ያንተ ግን ብል እና ዝገት አይበላውም፤

ጊዜ አይለውጠውም፤

አያልቅም፤

ወደ ሰማያት፣
ወደ ሰማየ ሰማያት፣
ወደ ምድር፣
ወደ አየራት፣
ወደ እንስሳቱ ዓይነት፣
ብዙ የብዙ ብዙ ወደሚኾኑት ዕፅዋት፣
ወደ ደቂቀ አዳም በጠቅላላው፣
ወደ መላእክት፣
ወደ መላእክት አለቆች፣
ወደ ኃይላት #ተመልከት

እነዚህ ኹሉ የአምላክኽ ፍጥረት ናቸው፤

የእነዚኽ #አምላክ እና #መጋቢ
ባርያ መኾን
"ድሃ መኾን" አይደለምና፥
'ድሃ አይደለኽም' ብዬ እነግርኻለው።

[{ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ}]

3 months, 2 weeks ago

#የነቢያት#ጾም

. ከልደት በዓል አስቀድሞ የሚጾም ሲሆን፣ #ከኅዳር ፲፭/15/ ቀን ጀምሮ ለ፵፫/43 ቀናት ተጹሞ፣ የሚፈሰከው በልደት በዓል ነው፤

. ይኽ ጾም በዘመነ ብሉይ እና በዘመነ ሐዲስ ብዙ ቅዱሳን ጾመውታል፤

. ዛሬም እኛ ምእመናን፣
እንደ ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን መሠረት፣
የአባቶችን ፈለግ ተከትለን፣
ከፈጣሪ ጋር ለማግኘት እንጾመዋለን
መጾምም ይገባናልም፡፡

በመሆኑም በጌታችን ልደት፣
ትንቢተ ነቢያት ስለተፈጸመበት፣
ይህ ጾም የነቢያት ጾም ይባላል፤

. የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መኾን ያስተማሩበት ስለሆነም ጾመ ስብከትም ይባላል፡፡

. ምንም እንኳን ትንቢቱ የተፈጸመ ቢሆንም፦
በረከት ለማግኘት
የነቢያትን ፈለግ ተከትለን
በየዓመቱ እንደ ዐዲስ ደስ ብሎን

ክብር ይግባውና ጌታችን ለፍርድ መጥቶ፣ መንግሥቱን ከሚያወርሳቸው ቅዱሳኑ ጋር እንዲደምረን

"የነቢያትና የሐዋርያት፣ የጻድቃን እና የሰማዕታት አምላክ ተለመነን" እያልን #እንማጸንበታልን#እንጾመዋለን፡፡

6 months, 2 weeks ago

አንድ ወንድም አንድን አረጋዊ
"ልቤ ደንድኖብኛል፤ እግዚአብሔርንም አልፈራውምና ምን ላድርግ" ብሎ ጠየቀው።

አረጋዊውም
"እግዚአብሔርን ከሚፈራ ደግ ሰው ጋር ኑር[ዋል]"
አለው።

[ከበረሐውያን ሕይወት እና አንደበት ፤ በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ፤ ገጽ ፻፰/108፤ ፳፻፫/2003 ዓ.ም.]

6 months, 2 weeks ago

ፍቅር ከሌበት ልቡና ፥ ፈሪሃ እግዚአብሔር ሊመነጭ አይችልም፤

ፈሪሃ እግዚአብሔር የሌላው ልቡናም፥ የንስሓ መሰናክል ነው።

6 months, 2 weeks ago

በብዙ ወንዶች መፈለግ ጽድቅ አይደልም፤

ጥያቄው የተፈላጊነትሽ መደብ የቱ ነው የሚለው ነው፤

ለዝሙት ከኾነ የፈለጉሽ፦
ላቷን ገልጣ ከምትሄድው ፍየል ለይተው አላዩሽም ማለት ነው፤

መታየት እኮ አያመጻድቅም

ምስጢር መስማት የምትወጂውን ያኽል ነው ምስጢር መኾን ያለብሽ አራት ነጥብ

...

© ...

9 months, 1 week ago
We recommend to visit

Welcome To Amharic films Best Place To find Amharic Movies

አዳዲስ እና የድሮ አማርኛ ፊልሞችን እና አማርኛ ተከታታይ ድራማዎችን ለማግኝት ቻናላችንን Join ይበሉ ።
Share:- @Amharic_Films

ለማስታወቂያ - @Abusheymc & @Alpha6249

Buy ads: https://telega.io/c/Amharic_films

Last updated 1 year, 8 months ago

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @Aymu_xo

Last updated 3 weeks, 1 day ago

╔╦╦═╦╔╦═╦═╦═╗
║ እንኳን ደህና መጡ | |
╚══╩═╩═╩╩╩╩═╝
➟ እንኳን ወደ ትልቁ የሊቨርፑል ( መርሲሳይድ) ቻናል በደህና መጡ ።
◉ ስለ ሊቨርፑል ◉
? ዝውውሮች

? ውጤቶች

? የጨዋታ ፕሮግራሞች

? እንዲሁም የተጨዋቾች ግለ ታሪክ

? ጨዋታዎችን በቀጥታ ወደናንተ የምናደርስ ይሆናል።

Owner:- @hackersolo0⭐️

Last updated 2 months, 2 weeks ago