Why Pay for Entertainment? Access Thousands of Free Downloads Now!

ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy

Description
"Strong minds discuss ideas, average minds discuss events, weak minds discuss people."
Rinu Ruzvelt
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።

ያግኙን +251913134524

Last updated 1 month ago

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @MKHI7

Last updated 1 month ago

BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot

Last updated 2 weeks ago

1 month ago

አብዘርዲዝም - ካምዩ

ምንጭ ፦ ፍልስፍና ከዘርዓያዕቆብ እስከ ሶቅራጠስ
ምንጭ ፦ ፍሉይ አለም

መጠለያ ባጣህበት ሁኔታ በዝናብ እየተደበደብክ እየተጓዝክ ሳለ፣ መሳቅ ጀምረህ አታውቅም? የሆነ ጉዳይ በእጅጉ ተበላሽቶብህ ከዚህ በላይ ምን ሊመጣ አይነት ስሜት ፈገግ ብለህ አታውቅም? በችግሮችህ ውስጥ ሳለህ እያንዳንዷን ደቂቃ ወደህ አታውቅም? ይህን አልበርት ካምዩ አብሰርዲቲ ይለዋል፡፡

ካምዩ ፈረንሳያዊ የኤግዚስታንሻሊዝም (ህላዌነት) ፈላስፋ ነው፡፡ በቀላል ታሪክም ፍልስፍናውን ይጀምራል፡፡

ሲሲፈስ የተባለ የጥንታዊቷ ግሪክ ንጉስ አማልክቱን የሚያስቆጣ ተግባር ፈጸመ። ሲሲፈስ ሞትን በሰንሰለት አሰረው፡፡ ይህንንም በማድረጉ የሰው ልጅ ዘላለም ኗሪ ሆነ። በመጨረሻም አማልክቱ ሲሲፈስ ያደረገውን አወቁ፤ በርሱ ላይም ዘላለማዊ ቅጣት ፈረዱበት፤ የሞትንም ሰንሰለት በጠሱ፡፡ እናም ሲሲፈስ ለመቀጣጫ እንዲሆነው ዘላለም ድንጋይ ሲያንከባልል እንዲኖር ተፈረደበት። ግዙፍ ቋጥኝ እየገፋ ወደ ተራራ አናት ያደርስዋል፤ ወዲያውም ቋጥኙ ወደ ተራራው ስር ተንከባሎ ይወርዳል፤ ሲሲፈስም እንደገና ከታች ጀምሮ ወደ ላይ ቋጥኙን ይገፋዋል፡፡ ቋጥኙም ተመልሶ ወደ ተራራው ግርጌ ይወርዳል...

ይህ የሲሲፈስ ዘላለማዊ ቅጣቱ ነው። ያንተስ ሕይወት ከርሱ ይለያልን? የሲሲፈስ እልፍ ጊዜ እየተመላለሰ ቋጥኝ ማንከባለሉ ትርጉም አልባ እንደሆነ ይሰማሃል? ሆኖም ያንተ ሕይወት ትርጓሜው ምንድን ነው?

ሕይወትህን ልክ እንደ ሲሲፈስ ትርጉም አልባ ቋጥኞችን ስትገፋ ነው የምታሳልፈው፡፡ የማይሞላ ሆድ አለህ... ሚልዮን ጊዜ መግበኸው ሚልዮን ጊዜ ጎድሎብሃል፤ የማይሞላ ፍላጎት አለ... ሚልዮን ጊዜ ተደስተህ ሚልዮን ጊዜም ተከፍተሃል። በጠዋት ከእንቅልፍህ ትነሳለህ፤ ገንዘብን ፍለጋም ወደ ስራ ትሄዳለህ... ቀኑ ይመሻል ዳግም ይነጋል... በጥዋት ወደ ስራ ትሄዳለህ. ከእለታት በአንዱ ቀንም ራስህን በሞት አልጋ ላይ ታገኘዋለህ፡፡ እናም በሕይወት ዘመንህ የምታደርገው ነገር ሁሉ ልክ እንደ ሲሲፈስ ቋጥኝ መግፋት- ዘበት ነው!

የሰው ልጅ ህልቆ መሳፍርት በሌለው ሁለንተና ላይ ራሱን ሲያገኘው፤ “ለምን?” የሚል ጥያቄን ይጠይቃል። ለምን ተፈጠርኩ? ለምን እኖራለሁ? የሕይወቴ ትርጉምስ ምንድን ነው? ሆኖም እውነታው ይህ ነው... ያንተም የኔም የመኖር ሁኔታ በአጋጣሚዎች የተፈጠረ እንጂ ትርጓሜ ያለው ነገር አይደለም በጸጥታ ውስጥ ባለው በግዙፉ ሁለንተና ውስጥ አንተ ማን ነህና ሕይወትህ ትርጉም ይኖረዋል? ሁለንተናም ስላንተ ግድ የለውም... ለጥያቄህም መልስ የለውም፡፡ ሆኖም ይህ መሆኑን ብናውቅም፤ ሰው ነንና የሕይወታችንን ትርጉም መፈለጋችንን አናቆምም የሞትን ቀን ያበቃለታል። ሞት በሕይወታችን የኖርንላቸውን ተግባራቶች በሙሉ ዋጋ ያሳጣቸዋል፡፡ ይህንን ነው አብሰርዲዝም ወይም የሕይወት ዘበትነት ሲል የሚጠራው፡፡

እና ዘበት በሆነ ዓለም ላይ እንዴት እንኑር?

ታይታኒክ በተባለው ፊልም መጨረሻ ላይ መርከቧ እየሰመጠች ሳለ ሙዚቀኞች ቫዮሊን ሲጫወቱ ይታያል፡፡ እንደሚሞቱ ቢያውቁም፣ ቅጽበታቸውን ብቻ መኖር ጀመሩ፤ የሚወዱትንም ሙዚቃ ከልባቸው ተጫወቱ፡፡

ካምዩ በአንደኛው መጽሐፉ ላይ እንዲህ ይለናል - "የምር የሆነ አንድ የፍልስፍና ጥያቄ ብቻ ነው ያለው፤ ጥያቄውም - ራሴን ላጥፋ ወይስ ቡና ልጠጣ?”

እንደ ካምዩ እሳቤ የሰው ልጅ የሚኖርበት ምክንያት ከሌለው ሶስት ነገሮች ያደርጋል፡

የመጀመሪያው ራሱን ያጠፋል፡፡ ማለቂያ አልባ በሆነው ሁለንተና ውስጥ የምትበራ አንድ ሻማ የርሷ ጭል... ጭል ማለት ትርጉም የለውምና ራሷን እፍ ብላ ታጠፋለች፡፡ ይህን ካምዩ የዓለምን ዘበትነት ማምለጫ ይለዋል።

ሁለተኛው philosophical suicide ይፈጽማል፡፡ ይህም ማለት ሕይወት ትርጉም ባይኖራትም ትርጉም እንዳላት አድርጎ ማሰብ ይጀምራል። ለዚህ ዋነኛ ተጠቃሽ የሚሆኑት ጭፍን አማኞች ናቸው፡፡ በእምነት ውስጥ መመርመር የለም... የምትኖርበት አላማ እንዳለህ እና የምታምንበት ሀይል ለዚህ አላማ እንደፈጠረህ ያለምንም መጠራጠር በጭፍን ትቀበላለህ፡፡ ስለሆነም መኖርህ ዋጋ አልባ ወይም ዘበት እንደሆነ አይሰማህም፡፡

በሶስተኛነት የምናገኘው ካምዩ absurd hero ይለዋል። ይህ ሰው ሕይወቱ ትርጉም እንደሌላት ያውቃል፤ ለሌሎች ሰዎች ትርጉም የማይሰጥ ነገር ግን ለእርሱ ብቻ ዋጋ ያለው ... ለእርሱ ብቻ የሚሰራ የሕይወት ትርጉምንም ይፈጥራል። ይህ የትርጉም ፈጠራ ሂደትም በራሱ ደስተኛ ያደርገዋል። ለሲሲፈስም ድንጋዩን ወደ ተራራ ማንከባለሉ ለእርሱ ትርጓሜ አለው፡፡ ይህ ለስው ልጆች የከፈለው መስዋእትነት ምልክት ነው. ይህ አማልክቱ ለእርሱ የሰጡት ቅጣት ምንም እንዳልሆነ ማሳያ መንገዱ ነው... ፈገግ ብሎም ድንጋዩን ይገፋል... የእርሱ ፈገግታም አማልክቱን እንደሚያስቆጣቸው ያስባል። እናም ድንጋይ ማንከባለሉ ብቻ ልቡን በደስታ ይሞላዋል።

ካምዩም ሕይወት ትርጉም አልባ እንደሆነች ቢያውቅም እንኳ እንደ ሲሲፈስ ሁን ይልሃል። በዝናብ ውስጥ ደንስ... ትርጉም አልባ በሆነች ዓለም ላይ ለራስህ ብቻ እውነት የሆነ የመኖር ትርጉም ፍጠር፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy

1 month ago

ክቡር ሰው - ካንት

ምንጭ ፦ ፍልስፍና ከዘርዓያዕቆብ እስከ ሶቅራጠስ
ፀሀፊ ፦ ፍሉይ አለም

ከጓደኞችህ ጋር እራት እየበላህ፣ አንዱ ተስተናጋጅ ከመጠን በላይ እያጨበጨበ አስተናባሪውን ይጣራል “እዚህ ጋር አንድ ምግብ፡፡” አንዳንድ ሰውም በሰላም ላደረሰው ሾፌር “እንዴት ነህ፣ ቻው ወይም አመሰግናለሁ” ሳይል ከታክሲ ወርዶ ወደ ጉዳዩ ያቀናል፡፡ ወንጀለኞች ህጻናትን ሰርቀው እንደ እቃ ይሸጣሉ፡፡ መንግስትም አገሩን ከዳ ብሎ ያስበውን ግለሰብ ያስገድላል፡፡ እነዚህ ሁሉ ድርጊቶች በጋራ የያዙት ነገር ምን አለ?

ኢማኑኤል ካንት አስተናጋጁን የሚያመናጭቀው ጓደኛህም፣ ለሾፌሩ ግድ የሌለው ተሳፋሪም፣ ልጆች የሚጠልፉ ወንጀለኞችም፣ አስገዳዩ መንግስትም... ሁሉም የሰውን ልጅ አግባብ ባልሆነ ሁኔታ አስተናግደዋል ይለናል።

ካንት በምክንያታዊነት ላይ ባለው የጸና አቋም በእጅጉ ይታወቃል። ለእርሱ ምክንያታዊነት ከሁሉ የላቀ ንብረታችን እንደሆነ ነው የሚነግረን። ከዚህም በላይ ምክንያታዊነት ምን ልክ ምን ስህተት ምን ኃጢአት ምን ጽድቅ እንደሆነ ይለይልናል፡፡

ካንት የሞራል ህግጋት አይለወጤ እና የጸኑ ናቸው ብሎ ያስባል። የሚደረስባቸውም በምክንያት እና ምክንያታዊነት ብቻ ነው። ይህንንም ምክንያታዊ ግብረገብነትንም ለማስረዳት ካንት ባለ ብዙ ገፅ መጽሐፎችን አሳትሟል።

ካንት ሁሉም ሰው ሊነካ የማይገባው
ክብር አለው ይለናል። እናም የሁላችንም ድርጊቶች ይህን ክብር የጠበቁ ሊሆኑ ይገባል። በሁሉም ሁኔታዎች ውስጥ ብንሆንም የሰውን ክብር መንካት የለብንም፡፡ ሰዎች የምንገለገልባቸው ቁሳዊ መሳሪያዎች አይደሉም፡፡ ሁሉም የራሳቸው ዋጋ አላቸው። ለሁሉም ሰው ግድ ሊኖረን ይገባል።

ሁላችንም እንደ ግለሰብ ዋጋ እንዳለን እናስባለን፡፡ ዓለም የግለሰቦች ጥርቅም ናትና ለራሳችን የምንሰጠውን ዋጋ ለሁሉም ሰው መስጠት የተገባ ነው፡፡ እኛ ምንም አይነት ጥያቄ እና ምክንያት ሳንደረድር፣ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለራሳችን ከፍ ያለ ዋጋን ከሰጠን፣ እንደ ማህበርም ለሌሎች ሰዎች ዋጋ ሊኖረን ይገባል።

አዎ በማህበረሰብ ውስጥ አንደኛው ተገልጋይ፣ ሌላኛው አገልጋይ ሊሆን የተገባ ነው፤ ሆኖም በዚህ ሂደት ውስጥ ሰዎችን እንደ ሰውነታቸው ልናከብራቸው የተገባ ነው፡፡ አስተናጋጁም፣ የታክሲ ሹፌሩም ሆነ ሀገር ከዳተኛው ሰው ናቸው። ሁሉም ለራሳቸው ዋጋን ይሰጣሉ፡፡ ካንት ከእርሱ በኑሮ ደረጃ ዝቅ ያሉትን አገልጋዮቹን በታላቅ ክብር ይመለከታቸው ነበር፡፡

በቀጣይም ሰውን እንዴት ማዋራት እንዳለብህ ስታስብ ይህን “እንደ ሰው እያከበርኳቸው ነው ወይንስ እንደ መሳሪያ እየተጠቀምኩባቸው?” ይህም ቀላል እና ሊተገበር የሚገባው ግብረገባዊ ህግ ነው፡፡

@Zephilosophy
@Zephilosophy

1 month, 2 weeks ago

ማራኪ የዜን ትረካዎች
በግሩም ተበጀ

@Zephilosophy
@Zephilosophy

3 months ago

ወደ መለኮት የሚወስድ መሰላል

ምንጭ ፦ የህይወት ኬሚስትሪ (ሳድጉሩ)
ትርጉም ፦ ሀኒም

“ግንዛቤ” ለተለያዩ ሰዎች የተለያዩ ነገሮች ማለት የሆነና ግልጽ ያልሆነ ቃል ነው። “ግንዛቤ” ስትል ከአእምሮ ንቃት ጋር እንዳታምታታው፡፡ የአእምሮ ንቃት በተሻለ ሁኔታ ለመኖርና የመኖርህን ሂደት በትንሹ ከፍ ባለ መንገድ እንድትመራ ይረዳሀል:: ግንዛቤ አንተ የምታደርገው ነገር አይደለም፤ ሕያውነት ነው፡፡ የአንተ ሕያውነትህ በአንተ ግንዛቤ ምክንያት ብቻ ነው። ሙሉ በሙሉ ግንዛቤ የሌለህ ከሆንክ ህያው መሆንህን አታውቅም፡፡ በሕይወት የምትኖረው ባለህ ግንዛቤ መጠን ብቻ ነው። የግንዛቤህ መጠን የሚለካው ደግሞ፣ አንድ ነገር በተሞክሮህ ውስጥ ባለው መጠን ነው፡፡

“ግንዛቤን መለማመድ የምችለው እንዴት ነው?” ብለህ ትጠይቅ ይሆናል፡፡ ግንዛቤን መለማመድ አትችልም፡፡ ሕይወትንስ እንዴት መለማመድ ትችላለህ? አሁን ለምታስበውና ለሚሰማህ ነገር ትልቅ ቦታ የምትሰጥ ከመሆንህ የተነሳ፣ ለህያውነትህ ብዙ ቦታ አትሰጥም፡፡ የስነ ልቦና ሂደትህም ከሕይወት ሂደትህ የበለጠ አስፈላጊ ሆኗል፡፡ አእምሮህ ጫጫታ ውስጥ ባይሆን፣ ግንዛቤ ተፈጥሯዊ መንገድ ነበር፤ ነገር ግን አእምሮህ ማለቂያ ወደሌለው ሁካታ ውስጥ እንዲገባ ስላደረግክ ግንዛቤ ከባድ የሆነ ይመስላል።

ሰዎች የአስተሳሰባቸውን ሂደት በጣም አስፈላጊ ከማድረጋቸው የተነሳ “አስባለሁ፣ ስለዚህም አለሁ” እስከማለት ደርሰዋል። ግን እውነቱ የትኛው ነው፤ የምታስበው ስላለህ ነው ወይስ ያለኸው ስለምታስብ ነው? ሀሳብ ማፍለቅ የቻልከው ስላለህ ነው፣ አይደል? በየትኛውም መንገድ በስነ ልቦና ሂደትህ መጫወት ትችላለህ፤ ነገር ግን ማሰብ የምትችለው ህያው ስለሆንክ ብቻ ነው፡፡ ህያው መሆን ከማይረባ የአስተሳሰብ ሂደትህ ይልቅ እጅግ ትልቅ ሂደት ነው፡፡

ከፈለግክ ሙሉ በሙሉ መኖር፣ ግን አለማሰብ ትችላለህ። እንዲያውም ብታስተውል በሕይወትህ ውስጥ በጣም ቆንጆዎቹ ጊዜዎች ስለ ምንም ነገር ሳታስብ የቆየህባቸው ጊዜያት ናቸው፡፡ የደስታ ጊዜያት፣ የሀሴት ጊዜያት፣ ፍጹም የሆኑ የሰላም ጊዜያት... ብለህ የምትጠራቸው ጊዜያት ስለ ምንም ነገር ሳታስብ የኖርክባቸው ጊዜያት ናቸው፡፡

ታዲያ ይበልጥ አስፈላጊው የትኛው ነው፤ መኖር ወይስ ማሰብ? ህያው ፍጡር መሆን ትፈልጋለህ ወይስ የምታስብ ፍጡር? መወሰን አለብህ፡፡ አሁን ዘጠና በመቶ የሚሆነውን ጊዜ የምታሳልፈው ስለ ሕይወት በማሰብ እንጂ ሕይወትን በመኖር አይደለም፡፡ እዚህ የመጣኸው ግን ሕይወትን ለመለማመድ እንጂ ስለ ሕይወት ለማሰብ አይደለም፡፡ ሕይወትን መለማመድ ትፈልጋለህ፣ በሃሳብህ ከጠፋህ ግን ሕይወትን መለማመድ አትችልም፡፡ ሕይወትን የምትለማመደው በስሜት ህዋሳትህ እንጂ በማሰብ አይደለም፡፡ ሃሳቦችህ ከእውነታው ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸው በመሆኑ የምታስበው ነገር ምንም ትርጉም የለውም፡፡ ማሰብ ከእውነታው ጋር ግን ምንም ግንኙነት ስለሌለው፣ ሁሉም ሰው በፈለገው መንገድ የራሱን የማይረባ ነገር ማሰብ ይችላል።

የስነ ልቦና ሂደትህ ከሕይወት ሂደት ጋር ሲነጻጸር በጣም ትንሽ ክስተት ነው፡፡ አሁን አንተ ማሰብን በሕይወት ከመኖር በላይ አስፈላጊ እንደሆነ ስለምታስብ፣ ከአንተ ሃሳብ ጋር በጥቂቱም ቢሆን ብጋጭ ለእሱ ስትል ልትሞት እንኳን ፍቃደኛ ነህ። ሰዎች ለሀሳባቸው፣ ለሚያምኑበት ነገር ይሞታሉ፡፡ ሰዎች በሕይወት መኖር ማለት ምን ማለት እንደሆነ ስላላስተዋሉ ማሰብ ከሕይወት ሂደት የበለጠ አስፈላጊ ሆኗል፡፡ ሕይወት በመኖር እንቅስቃሴ ስለተዋጠ፣ ማሰብ ከሕይወት የበለጠ ታላቅ ይመስላል፡፡ ግን እንደዚያ አይደለም። አስተሳሰብ ከሕይወት ሂደት ጋር ሲወዳደር ትንሽ ክስተት ነው፡፡

አርስቶትል የዘመናዊ አመክንዮ አባት ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ የእሱ አመክንዮ በጣም ቀላል እና ቀጥተኛ ነው፤ A መሆን የሚችለው A ብቻ ነው፤ B መሆን የሚችለው B ብቻ ነው፡፡ A፣ B ሊሆን አይችልም፤ Bም A ሊሆን አይችልም፡፡ በዚህ መከራከር ትችላለህ? ምክንያታዊ በሆነ መልኩ ትክክል ይመስላል፡፡ ግን እስቲ ይህን እንይ፡-

እዚህ ወንድ ወይም ሴት ሆነህ ተቀምጠሃል፡፡ ግን እንዴት ወደዚህ መጣህ? ሴት ነሽ እንበል፣ አባትሽ ለአንቺ መምጣት ምንም አላዋጣም ማለት ነው? በአንቺ ውስጥ አለ፣ አይደለም እንዴ? ወንድ ከሆንክም እናትህ ምንም አላዋጣችም ማለት ነው? እናትህ በአንተ ውስጥ የለችም? እውነት ነው አንተ ወንድ ወይም ሴት ነህ፤ ሀቁ ግን ሁለቱንም መሆንህ ነው። እውነት በምክንያታዊነት ሊገለጽ የማይችል ልኬት ነው᎓᎓ እውነት ከአመክንዮ ጋር አይገጥምም፤ ምክንያቱም አመክንዮ ሁልጊዜ የሚከፋፍል ሲሆን፣ እውነት ግን አንድ አድራጊ ነው፡፡ ታዲያ ይህ አመክንዮ ከሕይወት ጋር የሚገጥመው የቱ ጋ ነው?

የአንተን አመክንዮ በሕይወትህ ላይ ከልክ በላይ የምትተገብረው ከሆነ፣ ሁሉም ሕይወት ከውስጥህ ተጨምቆ ይወጣል፡፡ የአእምሮ አመክኗዊ ቁሳዊ እውነቶችን ገጽታ የሚጠቅመው የሕይወት ለመቆጣጠር ብቻ ነው፡፡ በመሰረታዊነት ሕይወትህን ፍፁም በሆነ አመክንዮ የምትመለከት ከሆነ ሕይወት ምንም ትርጉም አይኖረውም፤ ስለዚህ ራስህን በአመክንዮ ለመያዝ የምትሞክር ከሆነ ሙሉ በሙሉ ምስቅልቅል ያልክ ትሆናለህ ማለት ነው፡፡ ነገ በማለዳ ከእንቅልፍህ ስትነቃ የፀሐይ መውጣትን፣ በሰማይ ላይ  የሚበሩ ወፎችን አትመልከት፤ የምትወደውን ሰው፣ የልጅህን ፊት ወይም በአትክልቱ ውስጥ ያሉትን አበቦች አታስብ፤ ዝም ብለህ በፍፁም አመክንዮ አስብ።

አሁን፣ በትክክል ከአልጋ መውጣት አለብህ ያ ትንሽ ስራ አይደለም፡፡ ወደ መጸዳጃ ቤት ትሄዳለህ፣ ጥርሶችህን ትቦርሻለህ፣ ምግብ ትበላለህ፣ ከዚያ አንዳንድ ስራዎችን ትሰራለህ፣ ትበላለህ፣ ትተኛለህ፤ ነገ ጠዋትም ተመሳሳይ ነገር ታደርጋለህ፡፡ ይህን ነገር ለሚቀጥሉት አርባና ሀምሳ አመታት ደጋግመህ ማድረግ አለብህ። የሕይወት ተሞክሮህን ሳትመለከት መቶ በመቶ በምክንያታዊነት አስብ፡- በእርግጥ ጠቃሚ ነው? እባክህ የከፍተኛ አመክንዮ ጊዜያት ራስን የማጥፋት ጊዜዎች መሆናቸውን ተመልከት፡፡ ስለ ሕይወት መቶ በመቶ ምክንያታዊ በሆነ መንገድ የምታስብ ከሆነ፣ ለመኖር ምንም ምክንያት አይኖርም፤ እኔና አንተ እዚህ የምንኖርበት ምንም ምክንያት የለም፡፡ ነገር ግን በሕይወትህ ውስጥ አንድ የሚያምር ቅጽበት ከተመለከትክ፣ በድንገት ሁሉም ነገር ብሩህ ይሆንና መኖር ትፈልጋለህ፡፡ የሕይወትህ አመክንዮአዊ ገጽታና የሕይወት ተሞክሮህ ስፋት አንዳቸው ከሌላኛቸው ጋር ተቃራኒ ናቸው።

ሕይወትን በተሞክሮ አይን የምትመለከት ከሆነ፣ ለመኖር፡የሚያበቃ ምክንያት ይኖርሃል፡፡ ሕይወትን በምክንያታዊነት የምትመለከት ከሆነ ደግሞ ለመኖር ምንም ምክንያት አይኖርም፡፡ ሰዎች በበርካታ ምክንያቶች ራሳቸውን ያጠፋሉ፡፡ በአጠቃላይ ግን ሰው ራሱን የሚያጠፋው የነበረውን ተሞክሮ መልሶ ለማየት ፍቃደኛ ባለመሆኑ ነው፡፡ ለምሳሌ በጤና ምርመራ ሲወድቅ፣ የትዳር አጋር ጥሎት ሲሄድ ወይም ንብረቱን ሲያጣ ራሱን ሊያጠፋ ይችላል፡፡ ለምሳሌ ዛሬ ባልሽ ወይም ሚስትህ ጥሎሽ ወይም ጥላህ ሄደዋል እንበል። በምክንያታዊነት የምታስብ ከሆነ፣ “መላ ሕይወቴ ይህንን ሰው መውደድና ከዚህ ሰው ጋር መሆን ነበር፤ አሁን ይህ ሰው ትቶኝ ሄዷል። የምኖርበት ምክንያት ምንድነው?” ብለህ ታስብና ራስህን ታጠፋለህ። ነገር ግን ባልሽ ወይም ሚስትህ ትተው ከሄዱ ምናልባት በሕይወትህ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ አዲስ እድል ሊሆን ይችላል፡፡ ነፃ ስለሆንክ ብቻ ከአንድ የሕይወት ገጽታ ምናልባትም ያልገመትካቸው ነገሮች ያጋጥሙህ ይሆናል።
@Zephilosophy

4 months, 3 weeks ago

ደስተኛ አለመሆንን ለምን እንመርጣለን?
...የቀጠለ

ሰዎች ደስተኛ ከሆኑ በገንዘብ ልትደልሏቸው አትችሉም፤ መላ ህይወታቸውን ገንዘብ በማከማቸት አያጠፉምና፡፡ ለእነሱ ጠቅላላ ህይወትን ገንዘብ ለማከማቸት ሲባል ማባከን እብደት ነው፡፡ ሰውየው ሲሞትኮ ገንዘብ አብሮት አይሞትም።ይህ ፍፁም እብደት ነው። ደስተኛ ካልሆናችሁ በስተቀር ይህ እብደት አይታያችሁም።

ሰዎች ደስተኛ ከሆኑ የህብረተሰብ ጠቅላላ ቅርፅም ይቀየራል።  ይህ ህብረተሰብ በስቃይ ነው የሚኖረው። ለዚህ ህበረተሰብ ስቃይ ትልቅ ኢንቨስትመንት ነው።ልጆቻችንን ስናሳድግ ከመጀመሪያው ጀምሮ  ወደ ስቃይ እንዲያደሉ እናደርጋቸዋለን፡፡ ስለዚህ ሁልጊዜ የስቃይን መንገድ ይመርጣሉ፡፡

ሁለም ሰው ማለዳ ከዕንቅልፉ ሲነሳ ምርጫ አለው። ንጋት ላይ ብቻ አይደለም በእያንዳንዱ ቅፅበት የስቃይን ወይም የደስታን መንገድ የመምረጡ እድል አለ፡፡ ይሁንና ዋጋ ሰላለው ሁልጊዜ የስቃይን መንገድ ትመርጣላችሁ:: ልምዳችሁ  የዘውትር ተግባራችሁ ሆኗልና ሁልጊዜ ስቃይን ትመርጣላችሁ። በመሰቃየት ብቁ ሆናችኋል፤ መንገዳችሁ ሆኗል፡፡ አዕምሮአችሁ የመምረጥን እድል ሲያገኝ ወዲያውኑ ወደ ስቃዩ መንገድ ያደላል::

ስቃይ ቁልቁለት፤ ደስታ ደግሞ ዳገት ይመስላሉ። ደስታ የማይደረስበት ተራራ ቢመስልም ግን እውነት አይደለም:: እውነታው ከዚህ ተቃራኒ ነው። ደስታህ ቁልቁለት ነው ፤ ስቃይ ደግሞ ዳገት ነው። ስቃይ የማይደረስበት አስቸጋሪ ነገር ቢሆንም እናንተ ደርሳችሁበታል፤ የማይቻለውን ችላችኋል፤ ምክንያቱም ስቃይ ኢ -ተፈጥሯዊ ነውና፡፡ ሁሉም ሰው ስቃይን ባያፈልግም ሁለም ሰው እየተሰቃየ ነው::

ህብረተሰቡ በዚህ ረገድ ትልቅ ስራ ሰርቷል:: ትምህርት ፣ ባህል፣ የባህል ተቋማት ፣ ወላጆች፣ መምህራን. . . ሁሉም ትልቅ ስራ ሰርተዋል፡፡ ከደስታ ፈጣሪዎች፣ የሚሰቃዩ ፍጥረታትን አስገኝተዋል፡፡ ሁለም ሰው ሲወለድ ደስተኛ ሆኖ ነው፤ ሁሉም ህፃን ሲወለድ አምላክ ሆኖ ነው:: ሁሉም ሰው ሲሞት ደግሞ እብድ ሆኖ ነው:: ህፃንነትን መልሶ ማግኘት፣ መልሶ መያዝ የእናንተ ሃላፊነት ነው:: በድጋሚ ህፃን መሆን ከታደሉ ስቃያ ይጠፋል፡፡

ከአንድ ነገር ጋር ስትዋሃዱ ደስተኛ ትሆናላችሁ፡፡ ራሳችሁን እንድ ነገሩ: ስትነጥሉ (ከደስታ ቢሆን እንኳን) ትሰቃያላችሁ::ስለዚህ ቁልፉ ይህ ነው:: የራስ ኩራትን (ለራስ የሚሰጥ ከፍተኛ ግምትን) ይዞ መነጠል የሁሉም ስቃይ መነሻ ነው::

ህይወት ከምታመጣው ነገር ጋር አንድ ሆናችሁ ፣ ራሳችሁን በመተው የምትፈስሱ፣ ከሚመጣው ነገር ጋር የምትዋሃዱ ከሆነ ግን ሁሉም ነገር አስደሳች ይሆናል፡፡

ምርጫው እለ፡፡ እናንተ ግን ምርጫ መኖሩን አላስተዋላችሁም:: የተሳሳተውን መንገድ መምረጥን ልማዳችሁ አድርጋችሁታል፡፡ የቀረ ምርጫ መኖሩን አታስተውሉም::

ንቁ ሁኑ:: የስቃይን መንገድ በመረጣችሁ ጊዜ ሁሉ ምርጫውን የመረጣችሁት እናንተ መሆናችሁን አትዘንጉ:: ‹‹ምርጫውን የመረጥኩት እኔ ነኝ፣ ሃላፊነቱም የእኔ ነው፣ ይህ ሁሉ የእኔ ስራ ነው።"ብላችሁ ማሰባችሁ በራሱ ጠቀሜታው ላቅ ያለ ነው:: ይህን ስታደርጉ ወዳያወኑ ልዩነቱ ይገለፅላችኃል:: የአዕምሮአችሁ ባህርይ ይለወጣል። ወደ ደስታ የሚወስደው መንገድ ቀላል ይሆንላችኋል፡፡

አንዴ ምርጫችሁ ይህ እንደሆነ ካወቃችሁ ሁሉም ነገር ጨዋታ ይሆናል:: ስለዚህ መሰቃየት ከፈለጋችሁ ተሰቃዩ፡: ያን ምርጫ የራሳችሁ መሆኑን በመገንዘብ ምንም ወቀሳ አታቅርቡ። ሀላፊነቱ የሌላ የማንም አይደለም ፤ ይህ የራሳችሁ ድራማ ነው:: ያንን የስጋት መንገድ ከመረጣችሁ፣ በዚህ የስቃይ ህይወት ውስጥ ማለፍ ከፈለጋችሁ
ምርጫው ፣ ጨዋታችሁ የራሳችሁ ነው ማለት ነው:: የምትጫወቱት እናንተ ናችሁ፡፡ እናም በደንብ ተጫወቱት ከዚህች ቅፅበት ጀምሮ ግን ደስተኛና በሀሴት የተሞላ ለመሆን ደጋግማችሁ ጣሩ::

ደራሲ ኦሾ
ምንጭ አካለ አእምሮ
@Zephilosophy
@Zephilosophy

4 months, 3 weeks ago

ደስተኛ አለመሆንን ለምን እንመርጣለን?

የሰው ልጅ ከተጋፈጣቸው ውስብስብ ችግሮች መሃል እንዱ ይህ ነው፡፡ በንድፈ - ሃሳብ ደረጃ ሳይሆን በጥልቀት መመርመር አለበት። ይህ ጉዳይ እናንተንም የሚመለከት ነው:: ሁሉም ሰው ወደ ሃዘን፣ ድብርት፣ ስቃይ የሚወስደውን የተሳሳተ መንገድ ይመርጣል፡፡ ለዚህም ቀድመው የታወቁ ምክንያቶች አሉ።

የመጀመሪያው በጣም አስፈላጊ የሆነ ሚና የሚጫወተው የሰው ልጆች አስተዳደግ ነው:: «ደስተኛ ካልሆናችሁ አንድ ነገር ታገኛላችሁ፡፡ ደስተኛ ከሆናችሁ፤ ሁልጊዜ አንድ ነገር ታጣላችሁ» የሚል አስተዳደግ፡፡

አንድ ህፃን ይህን ልዩነት የሚገነዘበው ከመጀመሪያው ጀምሮ ነው:: ደስተኛ ባልሆነ ጊዜ ሰው ያዝንለታል ፤ ስለዚህ ርህራሄን ያገኛል፡፡ ሁሉም ሰው ሊወደው ይጥራል፤ ስለዚህም ፍቅርን ያገኛል፡፡ ከዚህ ያበልጥ ደግሞ ትኩረታቸውን በእሱ ላይ ያደርጋሉ፤ ስለዚህም ትኩረትን ያገኛል። ትኩረት ልክ እንደ አልኮል የሚያነቃቃ የራስ ኩራት ምግብ ነው:: ሃይል ይሰጣችኋል፤ እንድ የሆነ ሰው የሆናችሁ ያህል ይሰማችኋል፤ ስለዚህም ትኩረት ማግኘት በእጅጉ ትፈልጋላችሁ::

አንድ ሰው ሲመለከታችሁ አስፈላጊ የሆናችሁ ያህል ይሰማችኋል፡፡ ማንም ስው ዞር ብሎ የማይመለከታችሁ ከሆነ ግን እዚያ የሌላችሁ ያህል፣ ምንም እንዳልሆናችሁ ይሰማችኋል፡፡ ሰዎች ሲመለከቷችሁ፣ ሲጠነቀቁላችሁ በሃያል ትሞላላችሁ! ትነቃቃላችሁ፡፡
በማንኛወም ግንኙነት ውስጥ ለራስ የሚሰጥ ግምት (የራስ ኩራት) አለ:: ሰዎች ትኩረት በሰጧችሁ ልክ የራስ ኩራታችሁ ይጨምራል፡፡ ማንም የማያተኩርባችሁ ከሆነ የራስ ኩራታችሁ ይጠፋል:: ሁሉም ሰው ሙሉ በሙሉ የረሳችሁ ከሆነ እንዴት የራስ ኩራት ሊኖር ይችላል? እናንተ የገዛ ራሳችሁ እንደሆናችሁ እንዴት ሊሰማችሁ ይችላል።

ስለዚህም የማህበረሰቦች፣ የማህበራት፣ የክለቦች አስፈላጊነት ይመጣል፡፡ በመላው ዓለም ብዙ ክለባት አለ፣የክለባቱና የማህበራቱ ቀጥር በሚሊዮን የሚቆጠር ነው::  እነዚህ ማህበራትና ክለባት የተፈጠሩት በየትኛውም መንገድ ትኩረት ለማያገኙ ሰዎች ትኩረት ለመስጠት ነው::
አንድ ህፃን ከመነሻው ጀምሮ ይህን ፖለቲካ ሊማር ነው የሚያድገው:: «የተሰቃየህ ከመሰለህ ይሄን ጊዜ ይታዘንልሃል፧ ሁሉም ሰው ትኩረቱን ወዳንተ ያዞራል» የማለት ፖለቲካ:: የታመምክ ምሰል - ይሄኔ እስፈላጊ ሰው ትሆናለህ:: አንድ ህመምተኛ ህፃን አምባገነን ይሆናል ፤ መላው ቤተሰብም ትዕዛዙን ያከብራል - እሱ ያለው ሁሉ ደንብ ነው::

ደስተኛ ሲሆን ግን የሚያደምጠው የለም።በእጅ የለም ፤ ጤናማ ሲሆን የሚልጨነቅለት አይኖርም፤  ፍፁም ሲሆን ማንንም ትኩረቱን አይሰጠውም፡፡ በዚህም ከመጀመሪያ ጀምሮ የህይወትን፣የሀዘንን የስቃይ፣ የጨለመ መንገድ መምረጥ እንጀምራለን:: ይሄ አንድ እውነታ ነው።

ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ከዚሁ ጋር የሚያያዝ ነው:: ደስተኛ ስትሆን የመፈንደቅ፣ የሃሴት ስሜት ሲሰማችሁ ሁሉም ሰው ይቀናባችኋል፡፡ ቅናት ማለት ሁሉም ሰው የወዳጅነት ሳይሆን በተቃራኒ ስሜት ይመለከታችኋል ማለት ነው:: ሁለም ሰው ጠላታችሁ ይሆናል፡፡ ስለዚህም በሰው ዘንድ ጥላቻን ላለማትረፍ ደስተኛ አለመሆንን፣ አለመሳቅን ትመርጣላችሁ::

ሰዎችን ሲስቁ ተመልከቷቸው:: በተጠና ሁኔታ ነው የሚስቁት፡፡ ሳቃቸው ከሆዳቸው፣ ከማንነታቸው ጥልቀት የሚወጣ አይደለም:: በመጀመሪያ ይመለከቱዋችኋል ! ከዚያም ያመዛዝናሉ. . . ቀጥሎ ይስቃሉ፡፡ ሲስቁም እስከተወሰነ ደረጃ ነው . ሰዎች መታገስ እስከሚችሉበት፣ እስከማያገለዋቸው፣ የቅናት ስሜት እስከማይፈጥሩበት መጠን ድረስ፡፡

ፈገግታዎቻችን ሳይቀሩ የተመጠኑ ናቸው፡፡ ሳቅ ጠፍቷል! ሃሴት በፍፁም የማይታወቅ ሆኗል፤ መፈንደቅ አያፈቀድም፡፡ እየተሰቃያችሁ ከሆነ ማንም ሰው አብደዋል ብሎ እያስብም፡፡ መፈንደቅ፣መደነስ ሲያምራችሁ ግን ሁሉም ሰው እብድ እንደሆናችሁ ያስባል፡፡

ዳንስ የተወገዘ ነዉ ! ዘፈን ተቀባይነት የለውም፡፡ ደስተኛ ሰው ስናይ አንድ የሆነ ችግር እንዳለበት እናስባለን፡፡ የምንኖረው በምን አይነት ህብረተሰብ ውስጥ ነው? ሰው ሲሰቃይ ሁሉም ነገር መልካም እንደሆነ ይታሰባል፡፡ ህብረተሰቡ በመላ ከሞላ ጎደል በስቃይ ውስጥ ያለ ነውና የሚሰቃየው ሰው ከህብረተሰቡ ጋር ይጣጣማል ፤ እንዱ የህብረተሰቡ አባልም ይሆናል፡፡ አንድ ሰው ሲፈነድቅ ስናይ እብድ እንደሆነ እናስባለን፤ የእኛ ወገን እንዳልሆነ እናስባለን ፤ እንደዚያም ሆኖ የቅናት ስሜት ይሰማናል፡፡

ስለምንቀና እንቃወመዋለን፡፡ ስለምንቀና በተቻለን አቅም ወደ ቀድሞ ሁኔታ - እንዲመለስ እንጥራለን፡፡ የቀድሞ ሁኔታው ትክክለኛ እንደነበር እናስባለን:: የስነ እዕምሮ ተመራማሪዎችና ሃኪሞችም ያ ሰው ወደ ትክክለኛ ሁኔታ እንዲመለስ ይረዱታል፡፡

ህብረተሰቡ ደስታን አይፈቅድም:: ፍንደቃ ታላቁ እብዮት ነው፡፡ እደግመዋለሁ ፤ ፍንደቃ ታላቁ አብዮት ነው:: ሰዎች ደስተኛ እንዲሆኑ መላው ህብረተሰብ መለወጥ አለበት፤ ምክንያቱም ይህ ማህበረሰብ በስቃይ ውስጥ ያለ ነውና::

ሰዎች ደስተኛ ከሆኑ ለጦርነት ወደ ቪየትናም ወይም ወደ ግብፅ ወይም ወደ እስራኤል ልትወስዷቸው አትችሉም:: በፍጹም! ይህን ሃሳብ ስታቀርቡሏቸው የማይረባ ሃሳብ ነው!» ብለው ይስቁና ያጣጥሉዋቸኋል፡፡

ይቀጥላል..

ደራሲ ኦሾ
ምንጭ አካለ አእምሮ

@Zephilosophy
@Zephilosophy

5 months ago

ነገረ መለኮት ከሌላ ማዕዘን...

እኔ እንደ በርትራንድ ረስል ‹‹ሐይማኖት የፍርሃት ውጤት ነው›› አልልም፡፡ ይልቁንስ ምንነቱን እና ከየትነቱን የማያውቁት በቅጡ ያልተደመጠ፣ ምላሽ ያልተሰጠው ናፍቆት ወደ ማመን እንደሚመራን አስባለሁ፡፡ በእርግጥ የሕይወት፣ የአምልኮ ነገር ሲጀመር አደራረጉ እንደሞኝነት መሆን አለበት፡፡

አጀማመሩ ልክ ከፏፏቴ እንማውጋት፣ ለጨቅላ እንደማንጎራጎር፤ ምናልባት ለነፋስ እንደማፏጨት ስሜት የማይሰጥ ከሚመስል መዳዳት ሳይሆን አይቀርም፡፡ ነገርግን መሰረታዊው ሰው የመሆን ቅጥም የተሰራው በዚህ የገርነት ቅኝት መሆን አለበት፡፡ ሰው የፍጥረት የበላይ (superior) የመሆኑን ቀቢጽ የሚሰብኩት ከራሱ መካከል ተከስተው ሙሉ በሙሉ ከተፈጥሮ ቅኝት እስኪነጥሉት ድረስ የንጽህና ልጅ ነበር፡፡

ለምሳሌ የላቲን አሜሪካ ቅዱስ ሕዝቦች ኮጊዎች (Kogi) የክርስቶስን አዳኝነት፣ የነብዩ መሐመድን መልዕከተኝነትን ለመስማት ለአንድ ሺህ ስድስት መቶ ዓመታት የቅኝ ገዥዎችን መምጣት መጠበቅ ነበረባቸው፡፡ ነገርግን ሰው መሆን አልጠፋባቸውም፡፡ እንኳን ለመሰላቸው ለመላው ግዑዝ ለሆነው ስነፍጥረት ሁሉ ይራራሉ፡፡ ለሺህ ዘመናት አማኞች ነበሩ፡፡ ለዚያውም የተፈጥሮን ሥሪት የተከሉ... ዛሬም ድረስ የጥንታዊ አያቶቻቸውን የአምልኮ እና አስተሳሰብ ዘይቤዎችን እያስቀጠሉ ዘመናዊውን የሰው ልጅ ሽሽት በኮሎምቢያ አይደፈሬ የተራራ ሰንሰለቶች ይኖራሉ፡፡

እነዚህ ሕዝቦች ለተፈጥሮ ካላቸው ጥንቁቅነት የተነሳ መንገድ ስንኳ ለመስራት አንዲትም ድንጋይ ከቦታዋ አያፈናቅሉም፤ አንዲትም ሀረግ አይነቅሉም፡፡ ሁሉንም ነገር የሚከውኑት የተፈጥሮን የልብ ምት በተከተለ መልኩ ነው፡፡ ሰሚ ባያገኙም ቅሉ ስህተተኛው ታናሽ ወንድማችን ለሚሉት ዘመናዊው የሰው ልጅ ተፈጥሮን ስለመጠበቅ አስፈላጊነት በተከታታይ መልዕክቶችን ይልካሉ፡፡
እንዲህ የንጽህና ልጅ በነበረ ጊዜ ሰው ጨካኝ በሚመስለው ነገር ግን ፍትህና ርትዕ ሚዛኑ በሆነው ስሙር የተፈጥሮ ሰሌዳ ላይ ጊዜያዊያነቱን፣ አላፊ ጠፊነቱን በጸጥታ የተቀበለ ስኩን ፍጥረት ነበር፡፡ ተፈጥሮን ለመግዛት ለመግራት በበላይነት ስሜት ከመቋመጥ ይልቅ ተፈጥሮን መልበስ፣ መዋረስ ሰው የመሆን ደመነፍስን ያሰለጥን የለምን?

ሁሉም ነገር ሲጀመር የሰው ልጅ የመሆንን ነገረ ውል ለመካን ሙዝን ልጦ የመበላት ጥበብ ማወቅ ብቻ ይበቃው ነበር፡፡ ሲፈጠርም ጀምሮ ስሪቱ የተፈጥሮ ነው፡፡ በእርግጥም ያኔ የሰው ልጅ ደመነፍስ እንደመላዕክት፣ እንደመለኮቱ ጉልህ ‹እኔነቱ በስግብግብ ምሪት ያልደበዘዘ ገር (simplistic) ነበር፡፡

ሊዮ ቶልስቶይ የጻፈው በብዙዎች ዘንድ ሊታወቅ የሚችል አንድ አስገራሚ ተረት አለ፡፡ አሳጥሬ ልተርከው..

በአንድ ደሴት በብህትውና የሚኖሩ ሦስት ጻድቃን ነበሩ፡፡ አኗኗራቸው ተርታ ነው፡፡ ቀስ በቀስ ስለቅድስናቸው በአጎራባቿ ከተማና በመላው ሀገሪቱ ዝነኞች ሆኑ፡፡ ሰዎች ወደ እነርሱ ይጎርፉ ጀመር፡፡

ይህ ያላስደሰተው የአጎራባቿ ከተማ የቤተክህነት አስተዳዳሪ አንድ ቀን ሊገበኛቸው በጀልባ ሄደ፡
እንደደረሰም ጠየቃቸው..

‹‹ዝናችሁ በከተማውና በሀገሪቱ ናኝቷል፡፡ ለመሆኑ ለቅድስና ያበቃችሁ የተለዬ የምትጠቀሙት ጸሎት አለን?

‹‹እውነቱን መናዘዝ ይኖርብናል፡፡ በሥላሶች፣ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ከማመናችን የተለየ ምንም የምናውቀው ፀሎት የለም፡፡ ይልቁንስ የምንፈልገው መናገር ነው።ይፈጸምልናልም፡፡››

እንግዳው የቤተክህነት ሰው ሳቀ፡፡ ያለ ጸሎት የሚሆን ነገር እንደሌለ አስረድቶ ፀሎቱን አስጠናቸው፡፡

‹‹እባክህ እኛ የተማርን ሰዎች ባለመሆናችን ጸሎትህ ረጅም ከመሆኑ የተነሳ ልናስታውሰው አልቻልንምና ድገምልን፡፡›› ባሉት ጊዜ እንደገና አስጠናቸው፡፡ ጸሎቱን ለሦስተኛ ጊዜ እንዲያጠኑት ረዳቸው፡፡

በአሸናፊነት ስሜት ወደ እናት ከተማው መመለስ ጀምሮ የሀይቁ መሀል ላይ ሲደርስ ግን ለማመን የሚከብድ ነገር ሆነ፡፡ ሦስቱ መናኒያን በውኃው ላይ በፍጥነት እየተራመዱ ተጠጉት...

‹‹እባክህ ያስጠናኸን ጸሎት ረጅም ስለሆነ እኛም የተማርን ባለመሆናችን ተረስቶናል እና ብትደግምልን፡፡›› ተማጸኑት፡፡

በውኃ ላይ እንደቀላል መራመድ በሚያስችል ቅድስናቸው የተደነቀው እንግዳው ጎብኚ ግን በውኃ ላይ እስከመራመድ የሚያስችል የመብቃታቸውን ተዓምር ከተመለከተ በኋላ ...
«በፍጹም!   ትክክለኛው ጸሎት የእናንተው ስለሆነ በዚሁ ቀጥሉ ብሎ አሰናበታቸው፡፡››

የሰው ልጅ የንጽህና ልጅ በነበረ ጊዜ እንደነዚህ ሦስት ጻድቃን ነበረ፡፡ በዘመን ሂደት ቀስ በቀስ ሰው መሆንን ረስቶ አውሬነትን ተለማመደ፡፡ ሰው የመሆን ውሉ ሲደናገረው በመጽሐፍ ቅዱስ ‹‹ሰሎሞንስ ስንኳ በዚያ ሁሉ ክብሩ እንደነሱ አልለበሰም›› የተባለላቸው የሜዳ አበቦች ግን አበባ መሆን እንግዳ አልሆነባቸውም፡፡ አበባ ለመሆን ብዙ ምርምር፣ ላቦራቶሪ አላስፈለጋቸውም፡፡ የጽጌ ጌጥነታቸውን ለመቀዳጀት የንጽህና ልጆች መሆን ብቻ ይበቃቸዋል፡፡

የሰውን ልጅ ግን እናውቅልሃለን በሚሉ በራሱ በሰው ልጆች የመላው ፍጥረት የበላይ መሆኑን እየተጋተ ልጅነቱን ካደ፡፡ በሚያምነው ፊት ምንምን፣ ጊዜንም ቢሆን የማይፈራ የነበረውን ፍጥረት በሂደት ድንጉጥ አደረጉት፡፡ ድንጋጤው ጭካኔን ወለደ፡፡

ለራሱ ለመላው ስነፍጥረት ሁሉ ጭካኔን የሚነዛ አረመኔ ሆነ፡፡ ከጊዜና ከቦታ ጽንፍ፣ ከራስ መዳዳት በላይ አልፎ ማሰብ የማይችል ድኩማን...

በፍም እሳት ማቃመስ
ያዕቆብ ብርሀኑ

@Zephilosophy

5 months, 1 week ago

ከሃሳብ በታች እና ከሃሳብ በላይ መዋል

በጣም ሲደክምህ፣ ከመደበኛው ጊዜ አንፃር የተሻለ ሰላምና ዘና የማለት ስሜት ሊሰማህ ይችላል የዚህ ምክንያቱ፣ ሃሳብ ስለሚያሸልብና አዕምሮ ፈጠሩ ችግር የሞላበት ማንነትህን ስለማታስታውስ ነው። ወደ እንቅልፍ እያዘገምክ ነው።

አልኮል ስትጠጣ ወይም ሌላ አይነት ዕፅ ስትወስድ (እነዚህ አካለ-ስቃይህን የማይቆሰቁሱ ከሆኑ) ዘና የማለት፣ ግዴለሽነትና ምናልባትም ለተወሰነ ጊዜ የሚቆይ ህያውነት ይሰማሃል። ከጥንት ጊዜ ጀምሮ የህይወት ሃሴት ሲገለጥባቸው እንደኖረው፣ አንተም መዝፈንና መደነስ ትጀምራለህ። የአዕምሮህ ሸክም ቀለል ስላለልህ፣ የህላዌን ሃሴት በጨረፍታ ትቀምሳለህ። ምናልባትም አልኮል “ስፒሪት (spirit)” እየተባለ የሚጠራው ለዚህ ይሆናል፤ ነገር ግን የሚያስከፍልህ ከባድ ዋጋ አለ - እርሱም ማስተዋል የለሽነት ነው፡፡ ከሃሳብ በላይ ከመውጣት ይልቅ ከሃሳብ በታች ትወድቃለህ። ልክ ትንሽ መጠጥ እንደጨመርክ፣ወደ እፅዋት ዓለም የኃሊት ትመለሳለህ።

የስፔስ- አስተውሎ “እራስህን ከመሳት” ጋር ብዙም የሚያገናኘው ነገር የለም። በርግጥ ሁለቱም ሁኔታዎች ከሃሳብ ውጪ ናቸው። የሚያመሳስላቸው ይሄው ነው:: መሰረታዊ ልዩነታቸው ግን፣ በመጀመሪያው ከሃሳብ  በላይ የምትሆን ሲሆን፣ በኋለኛው ግን ከሃሳብ በታች ትወድቃለህ፡፡ አንደኛው በሠዎች ጥልቅ ተፈጥሮ ማበብ ውስጥ ቀጣዩ እርምጃ ሲሆን፣ ሌላኛው ግን ከረዥም ዘመን በፊት ትተነው ያለፍነው የዝቅጠት ቦታ ነው።

ኤካሀርት ቶሌ
@Zephilosophy

5 months, 2 weeks ago

የጠፋውን የሰው ልጅ ፍለጋ (Search for the lost human soul)

ዘመኑ 1950ዎቹ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ... ከሁለቱ የዓለም ጦርነቶች ስካር የባነነው ዓለም ለሌላ ዓይነት ባርነት ራሱን ሲያዘጋጅ ተገኘ፡፡ ሥልጣኔውም አገዘው፡፡ የሥልጣኔ ቀዳሚው ተልዕኮ የሰውን ልጅ እንሰሳዊ ደመነፍስ ማላመድ (taming human animalistic aggresion) ቢመስልም ውጤቱ ግን የተገላቢጦሽ ሆነ፡፡ ለኤሮፓዊ ፋውስታዊ የዛገ መዳዳቱ ስምረት ቴከኖሎጂው ረዳት ሆነለት፡፡

ዘመኑ ሰው ወደ አሻንጉሊትነት የሚያደርገውን የመምዘግዘግ ጉዞ አሀዱ ያለበት ሆነ፡፡ በአዲሱ ፈጠራ ቴሌቪዥን በመታገዝ "ፖፕ ከልቸር" ሰለጠነ፡፡ ሁሉም አብረቅራቂው ዘመን አመጣሽ ሳጥን ጋር ፍቅር ወድቆ ለአዲሱ ጊዜ ባርነት ራሱን አዘጋጀ፡፡ ዓመታት ተቆጠሩ፡፡ ቴክኖሎጂው በቀኝም በግራም እኩል ይመነደጋል፡፡ ቫይረሱ እና አንቲቫይረሱ፣ ሚሳኤሉና ጸረሚሳኤሉ እኩል ይበለጽጋሉ፡፡

ዛሬ ከሰባ ዓመታት በኋላ በዓለምአቀፍ ደረጃ ወደ ሁለት ቢሊዮን የሚጠጉ የቴሌቪዥኖች ዝግጅቶች ፣ ከ5 ቢሊዮን በላይ የሞባይል ስልኮች በሰው ልጆች እጆች ላይ ይገኛሉ። በአንጻሩ በሰው ልጆች የንባብ አትሮኖሶች ላይ እንደተዘረጉ የሚገመቱት መጻሕፍት ዓይነት ከ150 ሚሊዮን አይበልጥም፡፡

እነሆ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ሞታችን ረክሶ ‹ላይቭ ስናየው ስንኳ ማስደንገጡ ቀንሷል፡፡ እንበላለን፤ ግን አናጣጥምም፡፡ እንዋሰባለን፤ ግን ፍቅርን ረስተናል፡፡ አብረን ሆነን ለብቻችንን ነን፡፡ አብረን እየኖረን አንዳችን ለሌላችን በዓድ፣ ሩቅ ነን፡፡ ወዳጅነት፣ ሣቅ፣ ፈገግታ፣ መታመን፣ ፍቅር፣ ፍትወት... ሸቀጥ ሆነው በገበያ ዋጋ ይቸበቸባሉ፡፡

ሰብዓዊት የማይቀለበስበት አስፈሪ ውጥንቅጥ ውስጥ ገብቷል፡፡ አንዳንዶች ይህ አረዳድ ጭፍንነት ሊመስላቸው ይችላል፡፡ አንዳንዶች ሀዘኑ ቤታቸው እስኪገባ ድረስ የመቃብር ደወሉ በየዕለቱ ለእነርሱ እንደሚደወል ይረሱታል፡፡

እናስ ኤሪክ ፍሮም እንዳስጠነቀቀው የሚቀጥለው ዘመን ሮቦቶች ለመሆን ምን ያክል ይቀረናል? በዚያ ዘመን (በ195oዎቹ አጋማሽ) የተነሱት እንደ ኤሪክ ፍሮም ዓይነት የሰው ልጅ ዕጣ ያስጨነቃቸው አሰላሳዮች ሰው ስለመዳረሻው እንዲጠነቀቅ አብዝተው ቢወተውቱም ሁሉም ከአጥበርባሪ ሳጥኗ ጋር ሲወዛወዝ ሰሚ አልነበራቸውም፡፡ ኤሪክ ፈሮም በ1955 እ.ኤአ በታተመ The Sane Society› በተሰኘ መጽሐፉ ላይ እንዲህ አለ፡፡

‹የ19ኛው ክፍለዘመን ጥያቄ፣ ትርክት ‹‹እግዚአብሔር ሞቷል›› ነበር፡፡ የሀያኛው ክፍለዘመን ፈተና ግን የሰው ልጅ ሞቷል› ሆነ፡፡ በ19ኛው ክፍለዘመን ኢ-ሰብዓዊነት ማለት ጭካኔ ነበር፡፡ በ20ኛው ክፍለዘመን ግን ኢሰብዓዊነት ማለት መደንዘዝ፣ ስሜት ማጣትና መነጠል ሆነ፡፡ የትናንት ስጋታችን የሰውን ልጅ ወደ ባርነት እንዳይገባ ነበር፡፡ የነገ ስጋታችን ግን የሰውን ልጅ ከሮቦትነት የመታደግ ሆኗል፡፡››

‹‹ሁላችንም በዘመናዊው የምዕራብ ዓለም የምንኖር ሰዎች እብደት ውስጥ ነን፡፡ ራሳችን እያታለልን ላለመሆናችን ምን ዋስትና አለን?››

ዓለም መልክ የሌለው መገማሸር ውስጥ ገብታለች፡፡ ልክ አንደ ሁልጊዜው!... በዚህ ሂደት ሰው የመሆናችን ቀለም አጥተናል፡፡ ሰው የመሆናችን ውሉ በምን ይረጋገጥ? ከቅድመ አያቶቻችን የሚያስተሳስረን ፈትለነገር ከተቋረጠ ሺህ ዘመናት አልፈዋል፡፡ በሕንጻ ሰንሰለቶች መካከል እየተመላለስን ስንኳ ሕልማችን የተራራ፣ የሸንተረር፣ የአደን፣ የለቀማ ነው፤ እንደ ግዞተኛ ነን፤ ፊሊፒናዊ፣ ቼካዊ፣ ቱርካዊ... መሆናችን፣ የመጽሐፍ ቅዱስ፣ የቅዱስ ቁርዓን፣ ወይም የማናቸውም ቅኝት ሥሪት መሆናችን እውነታውን አይቀይረውም፡፡

እኔ ግን የዓይኑ ቀለም ያላማራቸውን በጅምላ ኮንነው ሰልፊ እየተነሱ ዘቅዝቀው የሚሰቅሉ ሕዝቦች ሀገር ዜጋ ነኝ፡፡ ያ ሁሉ የሺህ ዘመናት ወንጌል፣ ሥነምግባር፣ ሀፊዝ፣ ሥርዓት፣ ትምህርት፣ ግብረገብነት በቅፅበት ውኃ በልቶት መቅላት፣ እስከነፍስ ማቃጠል፣ መደፍጠጥ፣ ማሳደድ... ሁሉም በሚያስደነግጥ ፍጥነት ሲከናወን አቅመቢስ ስዱድ፣ ዲዳ ሆኘ ተመልከቻለሁ፡፡ ታምሜያለሁ፡፡ ብዙ ኢፍትሃዊነት ባለበት ምንም ማድረግ ካለመቻል በላይ የሚያም ምንስ ነገር ይኖራል?

ለነገሩ በየትኛውም የዓለም ክፍል በሰብዓዊነት፣ በአጠቃላይ በስነፍጥረት ላይ የሚቃጣ በደል ካላመመኝ የስካሩ አካል ሆኛለሁ ማለትም አይደል? አንዳንዶች ለዚህ መድኃኒቱ ዜግነትን ማስረጽ፣ ሕገመንግስት መቀየር... ዓይነት _ ጨዋ ሐሳቦችን ሲሰነዝሩ እሰማለሁ፡፡ ምንኛ የዋሆች ሆነዋል ጃል! የታመመው በአጠቃላይ የሰው ልጅ (ሰብዓዊነት) መሆኑን ማየትስ እንዴት ይሳናቸዋል? ይህ የሰብዓዊነት ማሽቆልቆል፣ ስርዓት በመቀየር፣ ደንደሳም ዴሞክራሲ በማስረጽ፣ በአዋጅ በማስነገር፣ ኢትዮጵያን እንደ አሜሪካ በማበልጸግ ብቻ ሊሻሻል አይችልም፡፡ እንዲውም ሁላችንም ከጫፍ እስከ ጫፍ እንደ ሰው ካላሰብን አንተርፍም፡፡

ዘመናዊው የሰው ልጅ ከቅድመ አያቶቻችን አንጻር የሁሉም ነገር ውስጥ መትረፍረፍ ውስጥ ነው፡፡ ዛሬ የአንድ አሜሪካዊ ቤተሰብ አማካይ የመገልገያ ቁሳቁሶች ብዛት እስከ 300,000 ይገመታል፡፡ ከመቶ ዓመታት በፊት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር 5000% እጥፍ ተመንድጓል፡፡ ዘመኑ በሁሉም ነገር የመትረፍረፍ (Abundance) ቅዠት ውስጥ የሚዳክር ይመስላል፡፡ ነገርግን መትረፍረፍ መቅሰፍት ሆኖብን ምኞታችን፣ እውነታችን፣ የሕይወት ትርጉማችን አሳክሮብናል፡፡ ምንም የማይፈይድልን የመረጃ ናዳ ያጥለቀልቀናል፡፡ በተሳከረ የመረጃ ቱማታ ተዋክበን እውነታችን ራሱ ዋጋ አጥቷል፡፡

ዘመኑ እንደየትኛውም ግልብ ዘመን ነበርና ኤሪክ ፍሮምና መሰሎቻቸው አድማጭ አላገኙም፡፡ እንደየትኛውም ዘመን... ዛሬ ለስሙ እንሰዋለን የሚሉ ቢሊዮናት ተከታዮች ያሉት መሲሁ በቁርጡ ቀን ከመስቀሉ ፊት ለፊት ለብቻው እንደነበረበት ዘመን፡፡ የሚያሳዝነው ዘመን ልብ መግዛት ሲጀምር ዕድሎች ቁጭት ሆነው ከተፍ ማለታቸው እኮ ነው፡፡

የሰው ልጅ የለየለት ዕብደት ውስጥ ገብቷል፡፡ ነጠል ብሎ ለሚታዘብ ተመልካች የሚታየው የሚሰማው  ሁሉ  አጃኢብ ነው፡፡ ሥልጣኔው ሁሉ በየዕለቱ የሚያስመዘግበው መካን፣ መራቀቅ የአውዳሚነት መሆኑ ተስፋ ያስቆርጣል፡፡ ከጦር መሣሪያ ጋር ያልተነካካው ቴክኖሎጂያዊ ፈጠራ ስንኳ በየዕለቱ ሰብዓዊነትን የሚያኮሰምን የመሆኑ ነገር ያስደነግጣል፡፡

ተመራማሪዎች በቅርቡ ሰው በማይደርስባቸው አስፈሪ የአርክቲክ አካባቢዎች ሳይቀር ብዙ ሺህ ቶን የሚመዝን የማይበሰብስ ቆሻሻ አግኝተዋል፡፡ የሰው ልጅ አሁን በተያያዘው ግዴለሽ ጎዳና ከቀጠለ ሩቅ በማይባል ዘመን ሕይወት ከውቅያኖሶችና ባህራት ተጠቃልሎ ሊጠፋ ይችላል፡፡

በፍም እሳት መቃመስ
ያዕቆብ ብርሀኑ

ይቀጥላል
@Zephilosophy

5 months, 3 weeks ago

4-ምስጋና

አራተኛው ነገር ምስጋና ነው።ምስጋና መንፈሳዊ ልምምድ ነው።በዚህ ዘመን የጠፋው ነገር ምስጋና ነው። የተሰጣችሁ ትንሽ አካል ምን ያህል አስደናቂ እንደሆነ ልብ ብላችሁ ታውቃላችሁን? ይህ አካል ምድር ላይ ካሉት ታላቅ ታዓምራት አንዱ አይደለምን? ጥቂት ምግብን ትመገባላችሁ እናም ይህ ትንሽ ሆዳችሁ ምግቡን ይፈጫል -ከዛም ሰውነታችሁን ይሆናል ይህ ታላቅ ታዓምር ነው።

ሳይንስ በከፍተኛ ሁኔታ ተሻሽሽሏል ግን አንድ ትልቅ ፋብሪካ አቋቁመን በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን በሥራው ብናሣትፍ አንድ ዳቦን ፈጭተን ወደ ደም መቀየር አንችልም፡፡ አንድን ዳቦ ፈጭቶ ወደ ደም መቀየር እስካሁንም ለሣይንስ በጣም አስቸጋሪ ነው፡፡ እናም ይህ አካላችሁ - ይህ ትንሽ አካል፣ ጥቂት ከአጥንቶች፣ ጥቂት ስጋ --ለሃያ አራት ሰዓታት ታዓምርን ይስራል። ሰውነታችሁ ታዓምር ነው ግን እናንተ ለዚህ ምስጋና አታቀርቡም!

ከዚህ ምስጋና ውጪ ሃይማኖተኞች መሆን አትችሉም፡፡ እንዴት ነው አንድ ምስጋና-ቢስ ሰው ሃማኖተኛ ሊሆን የሚችለው? ይህንን ምስጋና ቀጣይነት ባለው መንገድ መስማት ከጀመራችሁ በጣም የምትገረሙ ይሆናል። . ይህ ምስጋና በብዙ ሰላም ፣ በብዙ
ሚስጢር የሚሞላችሁ ይሆናል። ከዚያ በኋላም አንድ ነገር የምትገነዘቡ ይሆናል፡፡ የተሰጧችሁ ነገሮች በሙሉ የማይገባችሁ መሆኑን የምትረዱ ይሆናል። ግን እነዚህ ሁሉ ነገሮች ስላሏችሁ በምስጋና የምትሞሉ ይሆናል።
የተቀበላችሁት ነገር የእርካታ ስሜትን ስለሚሰጣችሁም በምስጋና የምትሞሉም ይሆናል። ምስጋናችሁን ግለጹ። ምስጋናችሁን የምታበለጽጉባቸውን መንገዶች ፈልጉ። በምስጋና ውስጥም መንፈሳዊነታችሁ ያድጋል። መላው ህይወታችሁም በታላቅ ሁኔታ የሚቀየር ይሆናል፡፡

@Zephilosophy

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።

ያግኙን +251913134524

Last updated 1 month ago

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @MKHI7

Last updated 1 month ago

BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot

Last updated 2 weeks ago