Unlock a World of Free Content: Books, Music, Videos & More Await!

ሱና

Description
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።

ያግኙን +251913134524

Last updated 1 month, 2 weeks ago

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @MKHI7

Last updated 1 month, 2 weeks ago

BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot

Last updated 3 weeks, 6 days ago

2 years ago
ሀሰን ሼክ መሃመድ 10ኛው የሶማሊያ ፕሬዝዳንት …

ሀሰን ሼክ መሃመድ 10ኛው የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ

ለሁለት ዓመታት የተራዘመው የሶማሊያ ምርጫ በዛሬው እለት ተካሂዷል።

በምርጫውም ሀሰን ሼክ መሃመድ አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት በመሆን ተመርጠዋል።

ሀሰን ሼክ መሃመድ የሶማሊያ ፓርላማ በ3 ዙር ባደረገው ምርጫ በስልጣን ላይ ያሉትን መሃመድ አብዱላሂ ፋርማጆን በመርታት ነው 10ኛው የሶማሊያ ፕሬዝዳንት በመሆን የተመረጡት።

ተመራጩ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃመድ ከዚህ ከቀም በፈረንጆቹ ከ2012 እስከ 2017 ሶማሊያን በፕሬዝዳንትነት መርተው እንደነበረ ይተወዋል።

t.me/AlGhaziMedia

2 years ago
ሱና
2 years ago
የሼክ ኸሊፋ ቢን ዛይድ ስርዓተ ቀብር …

የሼክ ኸሊፋ ቢን ዛይድ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

ስርዓተ ቀብሩ ትናንት አርብ ነው በትውልድ ሃገራቸው አቡ ዳቢ የተፈጸመው

ከስርዓተ ቀብሩ በፊት የአቡ ዳቢው ልዑል አልጋወራሽ ወንድማቸው ሼክ መሃመድ ቢን ዛይድ አል ናህያን እና ሌሎች የቤተሰብ አባላቶቻቸውና የቅርብ ዘመዶቻቸው በተገኙበት የጸሎትና ስንብት መርሐ ግብር ተከናውኗል፡፡

እ.ኤ.አ በ1948 የተወለዱትና ዩኤኢን ከ2004 ጀምሮ በፕሬዝዳንትነት የመሩት ሼክ ኸሊፋ ትናንት አርብ በ73 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው መገለጹ ይታወሳል፡፡
የዩኤኢ መስራች የሼክ ዛይድ የበኩር ልጅ የሆኑት ኸሊፋ የአቡ ዳቢ 16ኛው ገዢ ነበሩ፡፡

http://t.me/AlGhaziMedia

2 years ago
ሱና
2 years ago
ሱና
2 years ago
ሱና
2 years ago

ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ፦

" . . . ልክ ወደ መጨረሻው ፕሮግራም ላይ ልንገባ ስንል ነው ድንገት ድምፅ ሰማን፤ እየተረበሸ እንደሆነ ተነገረን።

ምንድነው ? ብዬ የሚመለከተው የመንግስት የስራ ኃላፊ ከፀጥታ መዋቅር ውስጥ አንዱ አመራር ጋር ደውዬ ስጠይቅ ያለው ነገር ' ሀያት ሬጀንሲ አካባቢ ጭስ ነው ' ይረጋጉ አሉኝ።

ሰው ይረጋጋ ብዬ ለመድረክ አስተባባሪው ነገርኳቸው ፤ ሰውን አረጋጋነው ፤ መልሶ ግን ቀጠለ ረብሻው ፣ ድምፁም የሚረብሽ ስለነበር ትንሽ ጥሩ አልነበረምና ምንድነው በሚል ጉዳዮችን ለመከታተል ሞከርን።

መልሼ ስጠይቅ ፤ ' አይ አስለቃሽ ጋዝ ከአንድ ፖሊስ በአጋጣሚ አምልጦት ፤ ድንገት ባርቆበት ' ተባለ ፤ ይህንን የሰማሁት ከፀጥታ መዋቅሩ ነው።

...በጣም ደስ የሚል እና ያማረ ፣ በጣም በጥሩ ሁኔታ ያሳለፍንበት ኢድ ነበር ነገር ግን ይሄ ክስተት መጥቶ ትንሽ ነገሮችን ረባበሻቸው።

በትክክል ለማጣራት ሞክሪያለሁ አንድ የፀጥታ ኃላፊ ከሚመለከታቸው ኮሚሽነር ጋር ተነጋግሬ የነገሩኝ ' ፌዴራል ፖሊሱ ባርቆበት ነው ' አሉ።

ከዛም ደግሞ በትክክል አካባቢው ላይ የመደብናቸው የእኛ አስተናጋጆች በአጋጣሚ ሴቶች ያሉበትና የሚሰግዱበት ቦታ ነበር።

የ 'ሰማዕታት ሀውልት' አካባቢ ላይ ነው፤ ሚኒስትሮች ሳይቀሩ የመንግስት ሙስሊም ሴት ሚኒስትሮች ቦታው ላይ የነበሩ አግኝቻቸው ያዩትን ክፍተት ነግረውኛል።

ከአንድ የ 'ፌዴራል ፖሊስ' ነው ተወርውሯል የሚሉት ምክንያቱም ፤ የሚባርቅ ነገር ዝም ብሎ የሚወድቅ አይደለም ፤ ተፈቶ መለቀቅ አለበት አስለቃሽ ጭሱ ፤ ተፈቶ ነው የተለቀቀው ወደ ሰው ነው የተጣለው።

ሴቶችና ህፃናቶች ወዳሉበት ቦታ ነው የተወረወረው።

ሰው በዛ ሰዓት ወደ መራባበሽ ስሜት ውስጥ ገባ ፤ ሴቶችም በድንጋጤ መሮጥ፤ መነሳት ያፍናል አይነት ሁኔታ ተፈጠረ።

በዚህ ሂደት ላይ እያሉ ሰውን አትውጣ ወደዛ አትሂድ የሚለው ግፊት መጣ ፤ በዚህ መካከል ሰውየውንም ይዘውት ነበር ፤ የእኛ አስተባባሪዎች ከያዙት በኃላ ሌሎች ፌዴራል ፖሊሶች ልቀቁት ብለው ያስለቀቁት፤ እሱም ይቅርታ ጠይቋል ' እኔ ባርቆብኝ ነው፤ ሳላስብ ነው ' ብሎ ደንግጦ የተናገረበት ሂደት ነበር የነበረው።

ያ ሁኔታ ተከሰተ ሰው ስሜት ውስጥ ገባ ፤ እንደገና መገፋት ፣ ወደዛ አትሄድም ወደዚህ አትመጣም ፣ ሶላት አልሰገደም በዚህ አይነት ነገር ውስጥ ሲገባ ተኩስ ተጀመረ ወደ አየር ፤ አስለቃሽ ጭሶች መሰል ነገራቶች እየተደረጉ ሲሄዱ አቅጣጫ ስተው ረብሻዎች ደስ የማይል ነገር ተከስቷል።

እስካሁን ባለኝ መረጃ የሞተ ሰው የለም። የተጎዱ ሰዎች አሉ።

የተለያዩ ሆስፒታሎች ውስጥ የገቡ አይናቸው አካባቢ ተመተው...በተለያየ ነገር የተመቱ ሰዎች ሆስፒታል የገቡ አሉ። ይሄ ነው ክስተቱ።

መጣራት አለበት ለምን ?፤ ማን ?፤ እንዴት ? የሚሉት ነገሮች መታየት አለባቸው። ይሄ በጣም ትልቅ የሆነ ታሪካዊ የሆነ፣ እንደ አትዮጵያ ያለ ሙስሊም የውጭ እንግዳ ጠርተን ፣ በልዩ ሁኔታ ያከበርነው ኢድ ስለነበር እነዚህ ነገሮች ከባድ ናቸው። "

©: Tikvah

@WorabeTimes

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።

ያግኙን +251913134524

Last updated 1 month, 2 weeks ago

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @MKHI7

Last updated 1 month, 2 weeks ago

BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot

Last updated 3 weeks, 6 days ago