Why Pay for Entertainment? Access Thousands of Free Downloads Now!

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴

Description
✞✞✞ በየቀኑ አዳዲስ መንፈሳዊ ፅሁፎች ለማግኘኘት ከፈለጉ ተቀላቀሉን ✞✞✞
@orthodox1
ሁሉም እንዲያነበው share ያርጉ


ለማንኛውም መረጃዎች ለመጠየቅ @drshaye

ማናገር ይችላሉ

🇪🇹 ✝✝ኦርቶዶክስ ለዘላለም ትኑር 🇪🇹

Join Us Today And Lets learn Together ✝✝✝
@orthodox1
We recommend to visit

★ሰውን በማዝናናት የብቃት ማረጋገጫ ያለው ብቸኛው ቻናል ሁሌም Telegram ላይ በጥበብ ደምቀን እናሸበርቃለን

💌 Contact us, @Modenyazbot

»የተመረጡ እና ማንም ያላያቸው የአማሪኛ ቀልዶች እንዲሁም የሚያስደንቁ ስዕሎችንና ቪዲዮ ያገኛሉ።

° ° [ ሙድ እንያዝ በእኛ የአራዶች መዝናኛ ] ° °

° ° Creator @Teke_Man ° °

Last updated 2 months ago

☕ ስለ ኢትዮጲያ ቡና የሚወጡ ወቅታዊና ትክክለኛ የክለቡ መረጃዎች አዚህ ያገኛሉ!

➪የዝዉዉር ዜና
☞የአሰልጣኞች አስተያየት
➪ጎሎች እና ቪዲዮዎች
☞የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
➪ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት ከየስታድየሙ !

➡መወያያ ግሩፓችን @Ethiopia_coffee_Sc

📩ሀሳብ ወይም አስተያየት ካሎት
በዚህ 👉 @EthiopianCoffeeScBot ✍
BOT ማድረስ ይችላሉ!

Last updated 4 days, 3 hours ago

እንኳን ወደ # ሉሲ የቴሌግራም ቻናል በደህና መጡ
#የሉሲ /LUCY DINKINESH E/ቤተሰብ ሰለሆኑ ደስብሎናል።

መረጃ መስጠት የምትፈልጉ በዚ አድርሱን 👉 @CACA77

# የኢትዬጵያዊነት የአሸናፊነት መገለጫ አርማችን ነው!
ነፃነታችንን 💪በፈርጣማው ጡንቻችን ይረጋገጣል
👉 ኢትዬጵያዊነት አርበኝነት የማንነት አርማች ነው
🙏🙏🙏

Last updated 1 month ago

2 months, 3 weeks ago

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ
  የህንጻ ቤተክርስቲያን ምርቃት ጥሪ
፡፡፡፡፡፡፡፡፡።።።።።።።።።፡፡።።።።።።።።።
ኑ" የእግዚአብሔርንም ሥራ አዩ
                          (መዝ66÷5)
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/በአ/አ/ሀ/ስ/በን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ቤ/ክ/የምስራቀ ፀሐይ ለቡ መርጡለ አርሴማ ገዳም ቀደም ሲል  ክቡር መልአከ ጽዮን  ቆሞስ አባ እስጢፋኖስ ይርጋ ወደዚህ ደብር በዋና አስተዳዳሪነት ተመድበው በመጡበት ሰዓት በሚያደርጉት የጉብኝት ወቅት ቦታው መሀል ከተማ ተቀምጦ እንዴት የቅድስት አርሴማ ጽላት ቆርቆሮ በቆርቆሮ በሆነ መቃኞ ውስጥ ይቀመጣል በማለት መንፈሳዊ ቁጭት አድሮባቸው  የአካባቢው ምዕመናንም ህንጻ ቤ/ክ እንዲሰራ ፍላጎት ስላላቸው  ዋና አስተዳዳሪው ሳይውሉ ሳያድሩ ልዩ ትኩረት በመስጠት ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፈው
እግዚአብሔርን ይዘው የንስሐ ልጆቻቸው የሆኑትን አክሊለ ስማዕትና ወለተ ሐና የተባሉ  እግዚአብሔር የመረጣቸው ባልና ሚስቶች የቅድስት አርሴማን ህንጻ  ቤተክርስቲያን እንዲሰሩ  በማሳመን በራሳቸው ወጪ ብቻ  ውሃ አንኳን ከቤተክርስቲያን ሳይጠቀሙ በገንዘብ እየገዙ ማንም ሳይጨመር  በደብሩ ዋና አስተዳዳሪ ክቡር መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ እስጢፋኖስ ይርጋ የየዕለት ክትትል በ1 ዓመት ከ4 ወር
ህንጻ ቤተክርስቲያኑ በፈቃደ እግዚአብሔር እጀግ  ዘመኑን በዋጀና ባማረ ሁኔታ ተሠርቶ ተጠናቆ የካቲት 9 ቀን2016 ዓ/ም እና የካቲት 10 ቀን 2016 ዓ/ም
.ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ለቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
.ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ጠቅላይ ዋና ስራአስኪያጅ እና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
.ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል የበላይ ጠባቂ
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የየመምሪያ ኃላፊዎች በተገኙበት እጅግ ባማረና በደመቀ ሁኔታ  የህንጻ ቤተክርስቲያኑ ምርቃት ይከናወናል ።
:::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
    በመሆኑም አርስዎም በዕለቱ ተገኝተው የበረከቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ  እና ላልሰሙት ያሰሙ ዘንድ በሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ሰም መንፈሳዊ ጥሪአችንን እናስተላልፋለን ።

የደብሩ ሰ/ጉ/አ/ጽ/ቤት

Mewi Events

Our passion is your perfect event.

For Bookings ☎️ 0979338787
                                 0910611517

2 months, 4 weeks ago

ለበለጠ መረጃ ተከታዮቹን የውጪ ምንጮች ከገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ለተጨማሪ ማስረጃ ያገናዝቡ ( በአስተያየት መስጫው በተቀመጠው አስፈንጣሪ ማውረድ ይችላሉ)

✧ THE ENCOMIUM OE BISHOP ABBA THEODOTUS [THE MARTYRDOM AND MIRACLES OF SAINT GEORGE OF CAPPADOCIA. THE COPTIC TEXTS EDITED WITH AN ENGLISH TRANSLATION
ERNEST A. WALLIS BUDGE, M. A] Pp. 307

✧ The Passion of St. George  Translated by E. A. W Budge Written by Abba Theodotus, Bishop of Ancyra in Glaatia in 431 AD. Pp. 18

በተራራው ላይ ጥር ፲፰ ቀን ስለተደረው ገቢረ ተአምራት ገድሉ በተጨማሪነት ከላይ በርእስነት ያነሳነውን ቃል በሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሕይወት ውሥጥ እያየ እንዲህ ይነግረናል

☞ ወጸውኦ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ለማር ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ በቃሉ አምላካዊ … ወሶቤሐ ተንስአ ከመ መርዓዊ ዘይወጽእ እምጽርሑ እንዘ አልቦ  ሕማም ለግሙራ

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሰማዕቱን ቅዱስ ጊዮርጊስን በአምላካዊ ቃሉ ጠራውና "የመረጥኩህ ወዳጄ ጊዮርጊስ ሆይ አሁን ከእንቅልፍህ ተነሥ አትፍራ፡፡ የማዝህ በመከራህ ሁሉ ከአንተ ጋር ያለሁት አምላክህ እኔ ክርስቶስ ነኝ"  አለው፡፡ ያን ጊዜም #ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ሙሽራ_ከጫጉላው_እንደሚወጣ ምንም ሕማም ሳያገኘው ተነሣ፡፡

#ደብረ_አሱርዮን የክርስቶስ ሙሽራ ሰማዕተ ጽድቅ ቅዱስ ጊዮርጊስን ለመጨረሻው መከራ ለሦስተኛው ሞት የወለደች የሰርግ አዳራሹ ናት። ምንም ሕማም ሳያገኘው በክብር ላይ ክብር እንዲጨመርለት ለበለጠው ተጋድሎ ጥር ፲፰ ሥጋው አጥንቱ ተቃጥሎ አመድ ሆኖ ተዘርቶ ሙሽራ ሲያገባ ተሰበሰበ እንደሚባለው እርሱም የሰርግ አዳራሹ የሙሽርነት እልፍኙ ከተባለችው ከፍ ያለችና ምድረ በዳ ከሆነች/ይድራስ  ተራራ በክብር ተሰብስቦ ተነሳ «#ደብረ_ይድራስ_ጽርሐ_መርዓሁ_ለጊዮርጊስ» 

የቀደሙቱ በፈተና ሲጨነቁ በጸሎታቸው እንዲህ የምትል «አርኬ»  የልብ ለልብ ተማጽኖ ለሰማዕቱ ያደርሳሉ።

«ተማኅጸንኩ በዝርወተ አጽምከ በደብረ ይድራስ በድው
በአምሳለ ጸበል ወሐመድ በእደ ሠገራት እደው
ጊዮርጊስ ኄር ጊዮርጊስ አፈው
ምርሐኒ ለፍቁርከ እምፆታ ፈቃድ ምንትው
በኀበ አስተርአየ ወፈቀደ መለኮት ሕያው»

በግጥም ወደኛው ስንመልሰው ይኽን ሐሳብ ይዟል

በአጥንቶችህ ተማጽኛለሁ
                   በተራራው የይድራስ አጸድ
በጠባቂዎች እጅ በተበተነው 
                    እንደ ትቢያና እንደ አመድ
ቸር የምትባል ጊዮርጊስ
                     ምግባርህም የሚያውድ
ወዳጅህን አንተው ምራኝ
                ከሥጋ ፈቃድ መንታ መንገድ
በሚገለጥበት ጎዳና
                        ሕያው የመለኮት ፈቃድ

🙏አሜን 🙏
መልካም በዓል
✍️ በቴዎድሮስ በለጠ ጥር ዝርወተ አጽሙ ለቅዱስ ጊዮርጊስ  ፳፻፲፮ ዓ.ም. [📍ከደብረ ወርቅ አትርፎ ቅዱስ ጊዮርጊስ]

2 months, 4 weeks ago

ውእቱሰ ከመ መርዓዊ ዘይወጽእ እምጽርሑ
#አርሱም_ከእልፍኙ_እንደሚወጣ_ሙሽራ_ነው
°°°°°°°°°°[መዝሙር ፲፰(፲፱)፥ ፭ ]°°°°°°°°

ቅዱስ ዳዊት ነገሩን የሚያነሳው "ወውስተ ፀሐይ ሴመ ጽላሎቶ ☞ በፀሐይ ክበብ ውሥጥ ጸዳሉን አደረገ (በእነርሱም ውስጥ የፀሐይን ድንኳን አደረገ)" በማለት ነው።

መልሶም ያ ፀሓይ ከጫጉላ የወጣ ሙሽራን ይመስላል [ውእቱሰ ከመ መርዓዊ ዘይወጽእ እምጽርሑ] በማለት ፀሐዩን በሙሽራ እየመሰለ በማሕጸነ ድንግል የተደረገውን ድንቅ ምሥጢረ ሥጋዌና ነገረ ተዋህዶ ወደእኛ እያቀረበ የበተስፋ ይተነብያ አራቅቆ ይተነትናል።

መተርጉማኑ ምሳሌስ ከተመሰለለት ነገር ቢያንስ እንጂ እንደምን ይበልጥ ብለው (ምሳሌ ዘየሐጽጽ ባለው) መምሰልስ ሙሽራው ነው ፀሐይን የሚመስለው እንጂ እንዴት ፀሐይ ሙሽራን ይመስላል ይላል ? ብለው ወደዘመኑ ተመልሰው ራሱን ዳዊትን ይጠይቁታል! ይመልስላቸዋል እንዲህ ብለው ይታረቁታል «መመሳሰል የጋራ ነው ብሎ እንዲህ አለ» ፤ ከዚህ አለፍ ብለው ደግሞ ሙሽራው ፀሐይን የፈጠረ መርዓዊ ሰማያዊ ክርስቶስ ሆኖ ፀሐይም ራሱ ፀሐየ ጽድቅ አማኑኤል ብለው አንዱን በአንዱ እያወዳጁ ምሥጢሩን በነገረ ምሳሌ ያስማሙታል።

ቅዱሱ ነቢይ የትንቢቱ ማረፊያ የሚያደርገው በፀሐይነቱ ውሳጣዊ ዓይናችን ብሩህ ያደረገልንንና የሕሊናችንን ጨለማ አርቆ ከእርሱ በሚገኝ እውቀት ያከበረንን እውነተኛ ብርሃን ቅዱሳኑን በጸጋ ብርሃናት የሚያሰኛቸውን አምላካችን ክርስቶስን ነው እንደሙሽራ ከጫጉላ ቤቱ ከሰርግ አዳራሹ ከድንግል እናቱ የወጣ ነውና ።

#ክርስቶስ_ፀሐይ
°°°°°°🌞°°°°°°
እርሱ ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስ ምሥራቅና ጽባህ ከተባለች እናቱ ድንግል ሲወጣ ከቆጥ ተሰቅሎ ከማገር ተንጠልጥሎ ያለ ሁሉ እንደሚገለጥ በእርሱም ፊት አንዳች የማይሠወር ፀሐይ [አልቦ ዘይትኀባእ እምላኅቡ] የተባለ፤

እርሱ ፀሐየ ጽድቅ ክርስቶስ በዙፋኑ ከተቀመጠ ንጉሥ አንስቶ በአደባባይ እስከወደቀ ጽኑስ ሁሉ ሊያየው የሚመኝ የሚረባ የሚጠቅም በመንገዱም ለመሮጥ ደስ የሚሰኝ አርበኛ ፀሐይ [ይትፌሳሕ ከመ ይርባሕ ዘይሜርድ ፎኖቶ] የተባለ፤

እርሱ ፀሐየ ዘጽድቅ ክርስቶስ ከባህሪው በሚገኘው ብርሃን የምድርን ጨለማ ያራቀ በጽድቁ ኃጢኣትን በእውቀቱ ድንቁርናን በንጽሕናው ርኩስን ያስወገደ ፀሐይ [ንጹሕ ወይሜይጣ ለነፍስ] የተባለ፤

የከበረች ቤተክርስቲያንን ለራሱ ሙሽሪት ያደረገና እንደሰርግ ቤት (ጫጉላ) የእናቱ ድንግል ማርያምን ማሕጸን ንጽሕት አዳራሽ አድርጎ ሥጋችንን ነስቶ የተዋሐደን የማይጠልቅ ፀሐይ የተባለው ሙሽራው ክርስቶስ በቅዱሳኑ ላይ አድሮባቸው የሚኖርና የዓለም ብርሃን ያደረጋቸው

☀️ #ጊዮርጊስ_ጸሐይ☀️
ፀሐይን የሚገልጥ ፀሐይ ጊዮርጊስ ፀሐየ ልዳ

ፀሐይም ቁምነገር ሁኖ ቅዱሳንን በዚህ መመሰላችን የሚነደው መብዛቱ ያሳዝናል፤ እንኳን በምግባር በሃይማኖት የተገለጠ ቅድስና ብቻውን የሰውነት ተፈጥሮ ከፀሐይ የላቀ ነበር። መጽሐፍ እንዲህ ይላል
"ከፀሐይ የሚነጻ ምን አለ? እርሱስ እንኳ ያልፋል፤ እንዲህ መሆን ሳለ ደማዊና ስጋዊ (ሰው) ክፉ ነገር ያስባል" 【ሲራ ፲፯፥፴፩】

ፀሐይ ይደንቃችኋል? ቅድስናን የባህሪ ገንዘቡ ያደረገ የበጎ ሥጦታና ፍጹም በረከት ምንጭ የተለዩ ፣ የከበሩ ፣ የነጹና የጸኑ ቅዱሳኑን መርጦ በፀጋው ቅድስና ከፍ የሚያደርግ አምላካችን ክርስቶስ ፦ በኑሯቸው እርሱን የመሰሉት እርሱ በእነርሱ ሕይት ቢገለጥ የተገለና አድሮባቸው ቢኖር ቅዱሳንን ክብራቸው ከፀሓይ እጥፍ ድርብ (Resplendently) የሚያበራ እንደሆነ በወንጌል ነግሮናል!
“በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ።” 【ማቴ ፲፫፥፵፫】

ሊያውም በሃይማኖታቸው ጽናትና በምግባራቸው ተጋድሎ የጽድቃቸው መገለጫ የሆነው ብርሃን ጉድለት ሳይኖርበት የሚጨምር እንደሆነ ጠቢቡ ሰሎሞን ይመሰክራል
“የጻድቃን መንገድ ግን እንደ ንጋት ብርሃን ነው፥ ሙሉ ቀን እስኪሆንም ድረስ እየተጨመረ ይበራል።” 【ምሳ ፬፥፲፰】

በልዳ ምሥራቅነነት ለክርስትናው አርበኝነት ሲወጣና ሲያበራ የታየው ቅዱስ ጊዮርጊስ የልዳው ፀሐይ ነው!

🌟 #ጊዮርጊስ_ኮከብ 🌟
ወደ ኮከብ የሚመራ ኮከብ ጊዮርጊስ ኮከበ ፋርስ

መክብበ ሰማዕታት ኮከበ ክብር ወመስተጋድል ቅዱሱ መንፈሳዊ አርበኛ ጊዮርጊስ ጨለማ በነገሠበት ሥቃይና መከራ በሠለጠነበት ምድራችን በሃይማኖቱ ጽናት በተጋድሎውም ትጋት በላይኛው ሰማይ በከበረች ነፍሱ እንደ ኮከብ ብሩህ ነው። "ወለነፍሰ ጻድቃንሰ ከመ ከዋክብት ብሩሃት በመልዕልተ ሰማያት" እንዲል【፩መቃ ፴፮፥፵】

በተለይም ደግሞ በዛሬዋ ኢራን የቀድሞዋ ፋርስ (persia) ለብዙዎች ከስሑታን ፍኖት መመለስና በእውነተኛው ሃይማኖት መጽናት አብነት ሆኖ በማለፉ ኮከበ ፋርስ ተብሏል።
“ብዙ ሰዎችንም ወደ ጽድቅ የሚመልሱ እንደ ከዋክብት ለዘላለም ይደምቃሉ።” ይላልና【ዳንኤል ፲፪፥፫】

ክርስቶስ ያደመቃቸው ከዋክብት ከእርሱ የተገኙ የእርሱ ስለሆኑ መርተው ወደ እርሱ ያደርሳሉ፤ በዚኽች ጥንት ምሥራቃዊት (ጽባሓዊቷ) ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን በኩል ያየነው ይህ ፍጡነ ረድኤት የተባለው ኮከብ እንደ ሰብአ ሰገል ፈጥኖ እየመራ ከቅድስናው አዳራሽ እያስገባን ለአምላካችን እንድንገዛለት ያደርገናል።
"ርኢነ ኮከበ ዚአሁ በምሥራቅ ወመጻእነ ከመ ንስግድ ሎቱ ☞ የእርሱን ኮከብ በምሥራቅ ዐይተን ልንሰግድለት መጥተናል" 【ማቴ. ፪፥፪】

ደብረ ይድራስ ጽርሐ መርዓሁ ለጊዮርጊስ
#ጊዮርጊስ_የክርስቶስ_ሙሽራ #እልፍኙ_የይድራስ_ተራራ
°°°🏔°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°⛰️°°°

#ይድራስ የሚለው ቃል ምድረ በዳ ማለት እንደሆነ የገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሐፊ የእንቆራው ኤጲስ ቆጶስ ቅዱስ ቴዎዶጦስ (Saint Theodotus of Ancyra) ይነግረናል።

☞ ወአዲ አዘዘ ይንሥኡ እምድር ከመ ይጹሩ ሐመደ ሥጋሁ ለቅዱስ ወይሰድዎ በከበሮ ወያዕርግዎ ኀበ #ደብር_ልዑል_ዘስሙ_ይድራስ ዘውእቱ መካነ በድው ብሂል ወይዘርዉ በነፋስ መልዕልተ ደብር ከመ ኢይርከብዎ ክርስቲያን ሐመደ ሥጋሁ ወወዓልትሂ ዘረዉ ሐመደ ሥጋሁ ውስተ ደብር ወተመይጡ

ዳግመኛም የቅዱሱን የሥጋውን አመድ አፍሰው በመውሰድ በቀፎ አድርገው ትርጓሜው #ምድረ_በዳ የሆነ ስሙ ይድራስ ተብሎ ወደ ሚጠራ ታላቅ ተራራ ላይ ክርስቲያኖች የሥጋውን አመድ እዳያገኙት በነፋስ እንዲያዘሩት አዘዘ፤ ጭፍሮቹም የሥጋውን አመድ በተራራ ላይ በትነው ተመለሱ።

የተራራውን ትክክለኛ መጠሪያ ስም በሚመለከት በገላትያ ላለችው እንቆራ ኤጲስ ቆጶስ የነበረው ብፁዕ ቴዎዶጦስ [The blessed Abba Theodotus, Bishop of Ancyra in Galatija] #የእውነት_ፀሐይ #የንጋት_ኮከብ (The sun of the truth☀️, the star of the morning🌟) እያለ ጠርቶ ያከብረውና በዱድያኖስ በኩል ከደረሰበት ጸዋትወ መከራ አንዱ ሥጋውን አቃጥለው አመድ አድርገው ከፍ ወዳለ ተራራ ይዘውት እንደወጡና በዚያም እንደበተኑት አመልክቶ የተራራውንም ስም #ደብረ_አሱርዮን ብሎ አስቀምጧል።

Then Dadianus made them take his ashes up to a high mountain called #Asurion, and they scattered them on the mountain to the winds.

4 months, 2 weeks ago

ነገረ ዘይት/ ወይራ ዛፍ (About Olive Tree)

ከዕለተ ሠሉስ ዕፀው መካከል ዕፀ ዘይት (የወይራ ዛፍ) አንዱ ነው! ቅባት የሚሰጥ ለመብልነት ለመብራትም የሚውል የወይራ ወገን ነው::

በሕገ ልቡና በሰብአ ትካት ለጥፋት ውኃ መወገድ በሰላም አብሣሪዋ ርግብ የመጣ ምልክት ይኼ ወይራ ነው!  "ርግብም በማታ ጊዜ ወደ እርሱ ተመለሰች በአፍዋም እነሆ የለመለመ የወይራ ቅጠል ይዛ ነበር። ኖኅም ከምድር ላይ ውኃ እንደ ቀለለ አወቀ።" 【ዘፍ ፰፥፲፩】

በሕገ ኦሪት ከምድረ ርስት ከነአን ገጸ በረከት አንዱ ይኼ ወይራ ነው! "ስንዴ ገብስም ወይንም በለስም ሮማንም ወይራም ማርም ወደ ሞሉባት ምድር፥..." 【ዘዳ. ፰፥፰ በቤተ መቅደሱ ያሉ ሁለቱ ኪሩቤል የተቀረጸው : የመቅደሱ መግቢያ መቃን  እና የቅድስተ ቅዱሳኑ ደጃፍ አምድ የተሰራው ከዚሁ  ከወይራ ነው! 【፩ ነገሥ. ፮፥፳፫-፴፬】

* በሕገ ወንጌል በመዋዕለ ሥጋዌው ሌሊት ሌሊቱን ጌታችን የመረጣት የጸሎት ሥፍራ ምጽአቱን ያስተማረባትና ዕርገቱን የፈጸመባት ደብር የወይራ ዛፍ የበዛባትን ሥፍራ "ደብረ ዘይትን" ነው! 【ሉቃ. ፳፩፥፴፯】 ዕለት ዕለትም በመቅደስ ያስተምር ነበር፥ ሌሊት ግን ደብረ ዘይት ወደምትባል ተራራ ወጥቶ ያድር ነበር።

በነገረ ሃይማኖት ምሥጢራዊ ምሳሌነቱ

የወይራ ዛፍ የቤተ እግዚአብሔር መብራት ምንጭ ነው! የፈጣሪን ገጸ ምህረት ተወካፌ ጸሎትነት ያሳያል "አንተም መብራቱን ሁል ጊዜ ያበሩት ዘንድ ለመብራት ተወቅጦ የተጠለለ ጥሩ የወይራ ዘይት እንዲያመጡልህ የእስራኤልን ልጆች እዘዛቸው።" 【ዘጸ· ፳፯፥፳】
  የወይራ ዛፍ ክር የሚነድበት ዘይት መገኛ ነው! ለእግራችን መብራት ለመንገዳችን ብርሃን የሆነ ህጉን ለሚያስተምሩ ምግባር ለሚያሰሩ አበው ምሳሌ ነው!  "ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው።"  【መዝ. ፻፲፰፥፻፭】
የወይራ ዛፍ በቤተ እግዚአብሔር ያማረ የተወደደ እንደሆነ እንዲሁ በሥላሴ ፊት ባለሟልነት በምዕመናን ዘንድ መወደድ በአጋንንት ዘንድ መፈራት ያላቸውን አበውን የመስላል!  "ለእስራኤልም እንደ ጠል እሆነዋለሁ... ውበቱም እንደ ወይራ ይሆናል" 【ሆሴ. ፻፬፥፮】
የወይራ ዛፍ ብዙ ፍሬ እንዲያፈራ ባለ ብዙ ጸጋና ክብር የሆኑትን አበውን ይመስላል! " ልጆችህ በማዕድህ ዙሪያ እንደ ወይራ ቡቃያ ናቸው።"  【መዝ. ፻፳፯፥፫】
የወይራ ዛፍ ቀን ከአእዋፍ ሌሊት ከአራዊት በአጥር በቅጥር ተጠብቆ  እንዲኖር በረድኤቱ በቤቱ ጥላ ተጠብቀው የሚኖሩ አበውን ይመስላል! "እኔስ በእግዚአብሔር ቤት እንደ ለመለመ እንደ ወይራ ዛፍ ነኝ፤" 【መዝ· ፶፩፥፰】

ለዚህ ነው የኢያሴንዩና የቶና ልጅ ኤልያስን ባለራእዩ ቅዱስ ዮሐንስ በመጽሐፈ ቀለምሲስ  «ዕፀ ዘይት ወመኃትው በቅድመ እግዚአብሔር » እያለ የሚጠራው። እነዚህ በምድር ጌታ ፊት የሚቆሙ ሁለቱ ወይራዎችና ሁለቱ መቅረዞች ናቸው። ማንምም ሊጐዳቸው ቢወድ እሳት ከአፋቸው ይወጣል ጠላቶቻቸውንም ይበላል፤ ማንም ሊጐዳቸው ቢወድም እንዲሁ ሊገደል ይገባዋል። እነዚህ ትንቢት በሚናገሩበት ወራት ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይን ሊዘጉ ሥልጣን አላቸው፥ ውኃዎችንም ወደ ደም ሊለውጡ በሚፈልጉበትም ጊዜ ሁሉ በመቅሠፍት ሁሉ ምድርን ሊመቱ ሥልጣን አላቸው። በረከታቸው በሁላችን ይደር !

🍁 [ኦ ኤልያስ] ; ብፁዓን ፡ እለ ፡ የአምሩከ ፤ ወእለ ፡ ስርግዋን ፡ በፍቅርከ ፤ ወንሕነሂ ፡ ሕይወተ ፡ ነሐዩ ፡ (በእንቲአከ) ።

🍁 [ኤልያስ ሆይ] ; የሚያውቁህና በፍቅርህ ያጌጡ ሰዎች ብፁዓን ናቸው፣ እኛም ስለአንተ በሕይወት እንኖራለን።

🍁 [Oh Elijah] ; Blessed are they that saw thee, and slept in love; for we shall surely live.
【ሲራ ፵፰፥፲፩, Sirach 48:11】

መጽሐፍ እጅግ ማግነናችንን ከአምላክ ማስተካከላችን እንዳልሆነ ሲነግረን እንዲህ ይላል  ⇨ አኮ ዘናስተአርዮ ምስለ ፈጣሪሁ አላ ናስተማስሎ በኵሉ ግብር ምስለ አምላኩ።  ⇨  ከፈጣሪው ጋር የምናስተካክለው አይደለም በሥራዎቹ ሁሉ ከአምላኩ ጋር እናመሳስለዋለን እንጂ ⇨ We do not equate Him with the Creator, but we view him as an example of God in all his works.
አልያስ ፍጥረቱ እንደኛው መሆኑን  “ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥” 【ያዕ፭፥፲፯】 ነገር ግን ከመጠን ይልቅ ማክበራችን ታዘንና ተለምነን መሆኑን ልብ ይሏል  “ወንድሞች ሆይ፥ በመካከላችሁ የሚደክሙትን በጌታም የሚገዙአችሁን የሚገሥጹአችሁንም ታውቁ ዘንድ፥ ስለ ሥራቸውም በፍቅር ከመጠን ይልቅ ታከብሩአቸው ዘንድ እንለምናችኋለን። ”【፩ኛ ተሰ ፭፥፲፪】

አንድ #ማስተካከያ በማመልከት መልእክታችንን እንቋጫለን።

ኤልያስ የተወለደው በምን ቀን ነው? 
መጽሐፈ ስንክሳራችን ታኅሳስ ፩ ቀን "የተገለጠበት ቀን” የሚለውን ይዘው ናቡቴ ባረፈበት ቀን ተወልዷል የሚሉ መምህራንና አድባራት ጭምር ይታያሉ፤ መገለጡ በጾመ ነቢያት  በነቢይነቱ በ’ነ አክአብ ፊት ፣ በሐሳውያን ነቢያትና በካህናተ ጣኦት ዘንድ፣ በእስራኤላውያን መካከል… መሆኑን ለመግለጥ እንጂ መወለዱን የሚገልጥ እንዳልሆነ መጽሐፍ ያብራራል።
ታዲያ ልደቱ መቼ ነው ያሉ እንደሆነ «መልኩ» በዚሕ መልክ አስቀምጦታል

"…ኤልያስ እምከ ካልዕተ ሣራ ጠባብ
ልደትከ አመ እሥራ ወአመ ሰኑዩ ለአብ
እንዘ ኩለንታከ በእሳት ግልቡብ …"

ከዚህ ውሥጥ «ልደትከ አመ እሥራ ወአመ ሰኑዩ ለአብ»
አብ የተባለው ወርኅ የቱ ነው ብለን የአይሁድን ዜና መዝገብ ብንፈትሽ ታሪክ ጸሐፊው ዮሴፍ (Flavius Josephus ⇝Yoseph Ben Mattithyahu) እንዲህ በማለት የወሩን ቁጥር ጭምር ያመለክትልናል
"ወርኃ ኃምስ ወውእቱ ወርኅ ወርኃ አብ ⇨ አምስተኛው ወር እርሱም አብ የሚባለው ወር ነው"【መጽሐፈ ዮሴፍ ኮርዮን ፶፫፥፭】

ይህ በዕብራውያኑ አብ የተባለው ለሚያዝያ ፭ኛው ወር በእኛ ደግሞ ወርኃ ነሐሴ ነው፤ ስለዚህ የኤልያስ ልደቱ "አመ እሥራ ወአመ ሰኑዩ ለአብ" ባለው መነሻ ነሐሴ ፳፪ ይውላል ማለት ነው።

“እነሆ፥ ታላቁና የሚያስፈራው የእግዚአብሔር ቀን ሳይመጣ ነቢዩን ኤልያስን እልክላችኋለሁ።”【ሚል ፬፥፭ 】

የቅዱስ ኤልያስ በረከቱን አምላካችን ለሁላችን ይላክልን 🙏

✍️ ከቴዎድሮስ በለጠ ታኅሳስ ፩/፳፻፲፮  ዓ.ም. ( Edited & Яερ๑šтεd ƒr๑๓ ጥር ግዝረት ፳፻፲፭  ከእንጦጦ ርእሰ አድባራት ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል አልያስ ወኤልሳዕ)

4 months, 2 weeks ago

“ነቢይ ዘከመ እሳት ⇨ እሳታዊ ነቢይ”
✥ °°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°° ✥

"ወተንስአ ኤልያስ ነቢይ ዘከመ እሳት ወቃሉኒ ከመ ነድ ያውኢ ⇨ እሳታዊው ነቢይ ኤልያስ ተነሣ ቃሉም እንደ እሳት ያቃጥል ነበር" 【ሲራ. ፵፰፥፩】

መነሻችን የሚሆነው ጥያቄ ነው?
☞ [መኑ ውእቱ] ዘዐርገ በነደ እሳት በሰረገላት ወበአፍራስ ዘእሳት ?
በእሳት ሰረገላና በእሳት ፈረስ ወደሰማይ የወጣ ማነው?
ይህን ጥያቄ የሚያነሳው ሲራክ ብለን የምንጠራው ኢያሱ ወልደ ሲራክ ወይም ኢያሱ ወልደ አልዓዛር በመጽሐፉ ፵፰ኛ ምዕራፍ ቁጥር ፱ ላይ ነው።

በመጽሐፈ ሲራክ መቅድም ሊቃውንቱ ይኽን ነግረውናል
ሲራክ፦ ፀሐፊ ማለት ነው፤ ፀሐፊው ኢያሱ ወልደ አልዓዛር ወልደ ሲራክ ይባላል።
፶፩ ምዕራፎች ፦ በአቀራረቡ ከሰሎሞን መጽሐፈ ምሳሌ ጋር ተመሳሳይነት አለው።
ይዘት ፦ ለመንፈሳዊና ሥጋዊ ሕይወታችን ጥበብና ምክር የሚሰጥ ነው።

ሲራክ ስለእሳታዊ ነቢይ ይጠይቃል፤
ማነው? በእሳት ተጠቅልሎ የተወለደ ፣ በእግዚአብሔር ቃል ሦስት ጊዜ ከሰማይ እሳት ያወረደ ፣ በእሳት ሠረገላና በእሳት ፈረስ ተጭኖ ወደሰማይ የነጎደ ማነው?
በዘይቤ መንፈሳዊ ትምህርትነትና ምክር በስፋት የያዘው ይኽ መጽሐፈ ሲራክ የእሳትን አስተማሪ ምሳሌነ አጉልቶ በብዙ መንገድ ይነግረናል ለአብነት
☞ ወርቅን ወርቅ ለመሆኑ የሚፈትኑት በእሳት እንደሆነው ሁሉ ጻድቅም ችግር በሚያመጣ መከራ ተፈትኖ የሚያልፍ ነው 【፪፥፭】
☞ የሚነድ’ እሳት የሚጠፋው በውኃ እንደሆነው ኃጢዓት የሚሰረየው በምጽዋት ነው 【፫፥፳፰】
☞ ከተናጋሪ ሰው ጋር መከራከር በእሳት ላይ እንጨት እንደመከመር ነው 【፰፥፫】
☞ መልከ መልካምና ደምግባት ያላት ሴት ፍቅር የሚነድ’ እሳት ነው 【፱፥፰】
☞ በነጻ ፈቃድ እንዲመርጥ ለሰው እግዚአብሔር ያቀረበው የጽድቅና የኃጢዓት መንገድ እንደ እሳትና ውኃ ነው 【፲፭፥፲፮】
☞ ሰው በልቡ ሐሳብ መፈተኑ ሸክላ በእሳት እንደሚፈተነው ነው 【፳፯፥፭】
☞ የእግዚአብሔር ፍርድና ቁጣው እሳት ነው 【፳፰፥፳፪】…

እሳት በጠባዩ ይቡስ (ደረቅ) ፣ ውዑይ (የሚያቃጥል) እና ብሩህ (የሚበራ) ነው። በፍጥረትነቱም ከዐራቱ አሥራው ፍጥረታትና ባሕርያት አንዱ ሆኖ በሁሉ የሚገኝ በይብስቱ ከነፋስ በውዕየቱ ከመሬት በብርሃኑ ከውሃ የሚስማማ ፍጥረት ነው።

ሲራክ ምዕራፉን የሚጀምረው የነቢዩን ማንነት እንዲህ ሲል ነግሮን ነው! "ወተንስአ ኤልያስ ነቢይ ዘከመ እሳት ወቃሉኒ ከመ ነድ ያውኢ ⇨ እሳታዊው ነቢይ ኤልያስ ተነሣ ቃሉም እንደ እሳት ያቃጥል ነበር" 【ሲራ. ፵፰፥፩】

አልያስ ማለት ቀናዒ
መደንግጸ አብዳን፡ ሕገ መነኮሳት ሠራዒ
ኤልያስ ማለት ድንግል
ብእሴ ሰላም ፡ መምህረ እስራኤል
ኤልያስ ማለት ቅብዓ ፍሥሐ
ለቤተክርስቲያን ፡ አንቀጸ ጽርሐ
ኤልያስ ማለት ካህነ ኦሪት
ምዑዘ ምግባር ፡ መዝገበ ሃይማኖት
ኤልያስ ማለት ጸዋሚ
ለእግዚአብሔር ቊልኤሁ ፡ ዝጉሐዊ ተሐራሚ

ኤልያስ ማለት…

ኤልያስ ቴስብያዊ ፣ ኤልያስ ቀርሜሎሳዊ ፣ ኤልያስ ታቦራዊ ፣ ኤልያስ ዘሰራጵታ፣ ኤልያስ ነቢየ ፋፃ … በኩረ ሐዋርያት ፣ ቢጸ ነቢያት ፣ ነቢየ ክርስቶስ ፣ ነቢየ ልዑል ባለብዙ ግብር ባለብዙ ስም …

የዚኽ እሳታዊ ነቢይ ስሙ እንዲህ የበዛው ሥራው ስለበዛ ነው "በአምጣነ ዕፁ ለእሳት የዐቢ ነዱ ⇨ በእንጨቱ ብዛት የእሳቱ ነዲዱ ይበዛል" እንዲል【ሲራ. ፳፰፥፲】

ወሬዛ በኃይሉ አረጋዊ በመዋዕሉ ተብሎ የተገለጠ ጸሐፌ ትዕዛዝ ቅዱስ ኤልያስ ጥር ፮ በእሳት ሠረገላና በእሳት ፈረስ ተጭኖ ወደሰማይ ያረገበት ቀን ፣ ታኅሳስ ፩ በአክአብ ፊት በኃይል ለዘለፋ የተገለጠበት(የናቡቴ ዕረፍት) ፣ «ነሐሴ ፳፪ ቀን ደግሞ ልደቱ» ነው፤ በእነዚኽ ቀናት ልንዘክረውና ልናከብረው ይገባል!

እንኳን እሳት ያወረደውን ቀርቶ የወረደውን እሳት ማክበር ተገቢ ነው ፤ አበው እንዴት መያዝ እንደሚገባው ሲነግሩን «እሳትን በገል ውሃን በቅል» ብለዋል።
ሙሴ አንደበቱ ትብ የሆነው እሳት በልቶ ፣ መጻጉዕ እጁ የተኮማተረው እሳት ጸፍቶ መሆኑን እናውቃለን።

ሊቁ እንዲህ ተቀኝቷል
"መጻጉዕ ሕፃን ኢያእማሬ ነፍስ ዓዲ
አኮኑ ፈነወ እዴሁ መንገለ እሳት ነዳዲ

【 መጻጉዕ ሕጻን ነው ነፍስ ማወቅ መች ጀመረ ?
ቢበስልማ ኖሮ ወደሚነደው እሳት እጁን ባልጨመረ 】

ኤልያስ ማለት በእብራይስጡ (ኤል אֵל) እና (ያስ/ ያህ יָהּ)ከሚሉ ሁለት የፈጣሪያችን ስሞች የተገኘ ጥምረት ሆኖ "እግዚአብሔር ጌታዬ ነው" የሚለውን ፍቺ ይሠጣል። በቅዱሱ መጽሐፍም ከታላቁ ነቢይ ውጪ ሌሎች ሁለት እስራኤላውያን በዚህ የከበረ ታላቅ ስም ተጠርተዋል።

በግሪኩ ደግሞ ኤሊያ ἐλαία (አላህያህ) ማለት ወይራ ማለት ነው። ይህን ያዞ ጌታችን የወይራ ዛፍ በበዛበት ተራራ በደብረ ዘይት ሲጸልይበት የነበረውን ዋሻ የኤልዮን ዋሻ እያለ ይጠራዋል

“ወመዐልትሰ ይሜህር በምኵራብ ወሌሊተ ይወፅእ ወይበይት ውስተ ደብር ዘስሙ ኤሌዎን ⇛ዕለት ዕለትም በመቅደስ (በምኩራብ) ያስተምር ነበር፥ ሌሊት ግን [ኤሌዎን በሚባል] ደብረ ዘይት ተራራ ወጥቶ ያድር ነበር ” 【ሉቃስ ፳፩፥፴፯】

መጽሐፍም ኤልያስ ማለት ወይራ ማለት ነው የሚለውን ልሳነ ጽርእ ይዞ የወይራን ተክል ፍሬና ዘይትን ኤልያስ እያለ ይገልጣል (The tree , the fruit or the oil ☞ ዕፀ ዘይት ፣ ፍሬ ዘይት ፣ ቅብዐ ዘይት)

【ኩፋ ፲፯፥፲】 "ወነሥአቶ እሙ ወሐራዊ ወገደፈቶ ታሕተ አሐቲ ኤልያስ ወሖረት ወነበረት አንጻሮ መጠነ አሐቲ ምንጻፍ እስመ ትቤ ኢይርአይ ሞት ለሕጻንየ ወነቢራ በከየት ⇨እናቱ አነሳችውና ሔዳ በአንዲት የወይራ/ዘይት እንጨት ሥር አኖረችው የልጁን ሞት አላይም ብላለችና በዚያ ተቀምጣ አለቀሰች" (13፥31)

【ሔኖ ፫፥፳፬】 "ወአሕቲ መስፈርተ ኤልያስ ትገብር ዐሠርተ ምክያደ ዘይት ⇨አንዲቱም መስፈሪያ ዘይት አስር የዘይት አውድማንበትመላለች "

የእኛ ሊቃውንት ስሙን በዘይቤና በምሥጢር እያራቀቁ «ዕፀ ዘይት ማኅቶት በቅድመ እግዚአብሔር ፣ ሥዩም ላዕለ ምድር ወሥሉጥ ላዕለ ሰማይ ወላዕለ ማይ » በማለት ገልጠውልናል። በ«መልኩ» መነሻ ላይም
ሰላም ለትርጓሜ ስምከ ዘተብህለ ዘይተ
… በጸውኦ ስምከ ኤልሳዕ ዮርዳኖስ አዕተተ" ይላል

የቅዱስ ዮሐንስ ራእይ ቃልም ለእርሱ መነገሩን በምሥጢር አስማምተው ይተረጉማሉ።

"ዕፀ ዘይት ወመኃትው በቅድመ እግዚአብሔር "【ራዕ ፲፩፥፬】
አቡቀለምሲስ በዚህ የራእዩ ክፍል በአምላካቸው ፊት ወይራና መቅረዝ እያለ አክብሮ የጠራው ሔኖክና ኤልያስን ነው።
✧ ወክልኤ ዕፀ ዘይት እለ ቅድመ እግዚአብሔር
(በእግዚአብሔር ፊት ያሉ የእግዚአብሔር ባለሟሎች የሚሆኑ ሁለቱ የወይራ ዛፎች) መባላቸው
☞ ሄኖክ ማለት ተሐድሶ(አዲስ መሆን) ማለት ነው።
ተሐድሶ በዘይት ነውና
☞ ኤልያስም ማለት ከላይ እንዳየነው ዘይት ማለት ነው።

✧ ወክልኤ መኃትው እለ ቅድመ እግዚአብሔር
(በእግዚአብሔር ፊት ያሉ የእግዚአብሔር ባለሟሎች የሚሆኑ ሁለቱ መብራቶች) መባላቸው
☞ በትምህርታቸው የሰውን ልቡና ብሩህ ያደርጋሉና

5 months, 2 weeks ago

እሾኹ ተነቅሏል፡፡

አዳም "እሾኽና አሜከላ ይብቀልብህ" ተብሎ ተረግሞ ነበር፡፡

በዚኽም ምክንያት ይህ እሾኽ የአዳምን እግሮች ሲወጋ ኖረ፡፡ ዛሬ ግን እሾኹ እግር እንዲወጋ ኾኖ አልተሠራም፤
አክሊል ኾኖ በመድኃኔዓለም ራስ ላይ ተደፋ እንጂ፡፡ በእሾኽ ምክንያት መቁሰል ከአዳም እግሮች ጀመረ፤ በመድኅን ክርስቶስ ራስ ላይ ተፈመ፡፡
አዳምን "ይብቀልብህ" ያለውን እሾኽ በራሱ ላይ 'እንዲበቅል' አደረገ፡፡

በዚህ እሾኽ አምሳል፥ ፍዳ መርገም፣ ኀጢኣት…ተነቅሏል:: ከኀሳር ወደክብር ተሸጋግረናል፡፡ መርገሙ ተሽሯል፡፡

6 months ago

የትምህርት ዕድል ያመለጠህ መስሎህ ነው? ገና ሺህ የትምህርት ዕድሎች አሉህ:: ዕድሜህ ያመለጠህ መስሎህ ነው? ነገ የሚጠብቁህ ብሩሕ ዘመናት እኮ ቁጭ ብለው አሉ? የሚረዳኝ ሰው የሚያስብልኝ ሰው አጥቼያለሁ? ብለህ ከሆነም ካልሰሙህ ጥቂቶች በላይ ልንሰማህ የምንሻ "ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ"

መከራ ጸናብኝ ኑሮ ጨለመብኝ የሀገሪቱ ሁኔታ ተስፋ አሳጣኝ ብለህ ይሆን? እኛስ አብረንህ አይደልንም? አብረን ከገባንበት ችግር አብረን ብንወጣ አይሻልም? ከአንተ በባሰ ሁኔታ የታሰርንና የተገረፍን ጳውሎሶችና ሲላሶች "ሁላችን በዚህ አለንና በራስህ ክፉ አታድርግ" ስንልህ ስማን::

ይልቅ አንተም እንደ ወኅኒው ጠባቂ "እድን ዘንድ ምን ላድርግ ብለህ?"ነፍስህን የምታድንበትን መንገድ ወደ መቅደሱ ቀርበህ ጠይቅ::

ወዳጄ ይህንን ጽሑፍ ያነበብኸውም በሕይወት ስላለህ ነው:: የአንተን ዓይን የሚጠብቁ ብዙ ጽሑፎች ፣ የአንተን ጆሮ የሚፈልጉ ብዙ ድምፆች ፣ የአንተን መሐረብ የሚፈልጉ ብዙ ዕንባዎች ፣ የአንተን ሳቅ የሚፈልጉ ብዙ ቀልዶች ... ገና ብዙ ብዙ አሉ::

ስለዚህ ሰይጣንን አሳፍረው:: እንዲህ በለው :-

"ጠላቴ ሆይ፥ ብወድቅ እነሣለሁና፥ በጨለማም ብቀመጥ እግዚአብሔር ብርሃን ይሆንልኛልና በእኔ ላይ ደስ አይበልሽ" ሚክ. 7:8

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥቅምት 2016 ዓ.ም.
ሜልበርን አውስትራሊያ

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን አጥብቃችሁ ስለ እኔ ጸልዩልኝ!
በኮሜንት መስጫው ሥር "ለሚሰሙት ጸጋን ይሰጥ ዘንድ፥ እንደሚያስፈልግ ለማነጽ የሚጠቅም ማናቸውም በጎ ቃል እንጂ [ዋጋን በምድር የሚያስቀር ውዳሴም ሆነ ሌላ] ክፉ ቃል ከአፋችሁ ከቶ አይውጣ" (ኤፌ 4:29)

6 months ago
  • በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ +

ይድረስ ለተከፋኸው ወንድሜ
መኖር ለደከመህ ፣ ሕይወት ለታከተህ ፣ የሚሰማህ ላጣኸው ፣ የሚረዳህ ሰው ላላገኘኸው መከረኛው ወዳጄ!

ከሞት ውጪ ሌላ መፍትሔ አልታይ ካለህ የአንተ ቢጤ መከረኞቹ ጳውሎስና ሲላስ እስር ቤት ውስጥ ሆነው እንዲህ ይሉሃል::

"በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ" ሐዋ. 16:28

አውቃለሁ ዙሪያው ገደል ሆኖብሃል:: ምነው ባልተፈጠርሁ እስክትል ድረስ ተጨንቀሃል::
ግን ይህ ስሜት በአንተ አልተጀመረም:: ሰው ሆኖ ተፈጥሮ ኑሮ ያልመረረው ማን አለ? መሞት ያልተመኘስ ማን አለ?

ሞት ያማረህ አንተን ብቻ መሰለህ?

" ስለ ምን ከማኅፀን አወጣኸኝ? ዓይን ሳያየኝ ምነው በሞትሁ" ያለውን ጻድቅ ኢዮብ አልሰማህም? (ኢዮ. 10:18)

"ከአባቶቼ አልበልጥምና ነፍሴን ውሰድ" ብሎ እንዲሞት የለመነውን ኤልያስን አላየኸውም? 1ነገሥ. 19:4

ዮናስንስ "አሁንም፥ አቤቱ፥ ከሕይወት ሞት ይሻለኛልና እባክህ፥ ነፍሴን ከእኔ ውሰድ፡ አለው" ሲል አልሰማኸውም? (ዮናስ 4:3)

ወንድሜ እመነኝ ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን መኖር ያላስጠላው ሰው በታሪክ ፈልገህ አታገኝም::

ሞት ሞት የሸተተው ልቡ የተሰበረ ብዙ ነው:: አንተ ላይ ብቻ የደረሰ ልዩ ፈተና የለም:: "ለሰው ሁሉ ከሚሆነው በቀር ምንም ፈተና አልደረሰባችሁም፤ ነገር ግን ከሚቻላችሁ መጠን ይልቅ ትፈተኑ ዘንድ የማይፈቅድ እግዚአብሔር የታመነ ነው፥ ትታገሡም ዘንድ እንድትችሉ ከፈተናው ጋር መውጫውን ደግሞ ያደርግላችኋል" ይላል መጽሐፍ:: 1ኛ ቆሮ. 10:13

ምናልባት የልብህን መሰበር የኀዘንህን ጥልቀት አይቶ ምቹ ጊዜ አገኘሁ ብሎ ራስህን እንድትጎዳ ሰይጣን ሊገፋፋህ ይችላል:: እንዴት እንዲህ ዓይነት ሃሳብ በልቤ ሊመጣ ቻለ ብለህ አትረበሽ:: ሰይጣን ይህንን ክፉ ሃሳብ ላንተ ብቻ ሳይሆን ለክርስቶስም አቅርቦለታል::

"የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር" ብሎ ክርስቶስን እንኳን [ማንነቱን ሳያውቅ] ራሱን እንዲወረውር ሊገፋፋው የሞከረ ደፋር ነው:: የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሰው ግን ራሱን አይጎዳም:: "ጌታ አምላክህን አትፈታተነው" "ሒድ አንተ ሰይጣን" ብለህ ሰይጣንን ገሠፀው::

ሰይጣን ክርስቶስን "ከሕንፃ ጫፍ በመወርወር የእግዚአብሔር ልጅ መሆንህን አሳይ" ሲለው ክርስቶስ ሰይጣንን ሒድልኝ ብሎ በመገሠጹ በክብር ወደ ሰማይ ዐርጎ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ::
ወንድሜ ሆይ አንተም ሰይጣንን አትስማው ሃሳቡ ራስህን ጎድተህ ከፈጣሪህ እንድትጣላ ሊያደርግህ ነው:: ሰይጣንን ከገሠጽከው በእግዚአብሔር ቀኝ ከበጎቹ ጋር ትቆማለህ::

አሁን ያለህበት ችግር ያልፋል:: የሚሰማህ ክፉ ስሜት መቼም የማይለወጥ አይምሰልህ:: ኀዘኑም ፣ ብቸኝነቱም ፣ ተስፋ ቢስነቱም ያልፋል:: ጨለማው ይነጋል:: የተዘጋው በር ይከፈታል:: ችግሩ ሲፈታ አንተ ከሌለህ ግን ትርጉም የለውም::

ስለዚህ ለሚፈታ ችግር የማይቀለበስ ውሳኔ አትወስን:: ራስን ማጥፋት ከጊዜያዊ ችግር ለመሸሽ ሲሉ ዘላቂ ችግር ውስጥ መግባት ነው:: ጊዜያዊ ሕመምን ለማስታገስ የዘላለም ሕመምን ለምን ትመርጣለህ? "የሞተ ተገላገለ" ሲሉ ሰምተህ እንዳትታለል ሞት ዕረፍት የሚሆነው ራሱ እግዚአብሔር ሲጠራህ ብቻ ነው::
"እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ወደ እኔ ኑ እኔም አሳርፋችኋለሁ" ያለው ጌታ ሳይጠራህ ራስን ማጥፋት የዘላለም ስቃይ ያመጣል::

ወዳጄ "በራስህ አንዳች ክፉ አታድርግ"

የሕይወትህን ዋጋ ታውቅ ይሆን? አንተ እኮ የእግዚአብሔር ልጅ ለአንተ ሲል የሞተልህ ነህ:: ሊፈውስህ የቆሰለ ፣ ሊያከብርህ የተዋረደ ፣ ሊያረካህ የተጠማ ፣ ሊያለብስህ የተራቆተ ለአንተ እኮ ነው::
ክርስቶስ ስለ አንተ ሞቶአል:: አንተን ግን የጠየቀህ እንድትሞትለት ሳይሆን እንድትኖርለት ነው::
ለሞተልህ አምላክ እንዴት መኖር ያቅትሃል?

ወዳጄ ሆይ ሰውነትህ በአምላክ ደም የተገዛ ክቡር ሰውነት ነው:: አካልህ "አንተ" እንጂ "ያንተ" አይደለም:: "በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ" ይላል

ስለዚህ በከበረ የእግዚአብሔር ልጅ ደም የተገዛ ሰውነትህን ለሰይጣን በርካሽ አትሽጠው:: አትግደል የሚለው ሕግ ራስህንም ይጨምራል:: ቤተ መቅደስ የሆነ ሰውነትህን ለማፍረስ አታስብ::
"ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ" 1ኛ ቆሮ. 3:17

ሰዎች አስቀይመውህ ይሆን?

"አሳያቸዋለሁ ፤ ስሞት የእኔን ነገር ይገባቸዋል" ብለህ በሰዎች ተቀይመህ ራስህን አትጉዳ:: እመነኝ ብትሞት ሰዎች ከሳምንት በላይ አያስታውሱህም:: ለሕይወትህ ዋጋ ያልሠጡ ሰዎች ለሞትህ ዋጋ አይሠጡም:: ፈጥነውም ይረሱሃል:: ለሚረሱህ ሰዎች ብለህ የማይረሳህን አምላክ አታሳዝን:: ሰው ስለ አንተ ግድ የለውም እግዚአብሔር ግን የራስህን ቁጥር ሳይቀር በቁጥር ያውቀዋል :: እንኳንስ ራስህን ልትጎዳ አንዲት ጸጉር እንኳን ከአንተ እንድትወድቅ አይፈልግም::

እግዚአብሔርን በኃጢአት ብታሳዝነው እንኳን ኖረህ ንስሓ እንድትገባ እንጂ እንድትሞት አይፈልግም:: አባትህ ነውና ከእርሱ ጋር ባትሆንም እንድትኖር ይፈልጋል:: በምሳሌ ልንገርህ :-

ሁለት ሴቶች አንድን ሕፃን "የኔ ልጄ ነው" ብለው እየተከራከሩ ጠቢቡ ሰሎሞን ፊት ቀረቡ:: ጠቢቡ ሰሎሞን ሰይፍ አመጣና "ልጁን ቆርጬ ለሁለት ላካፍላችሁ" አላቸው:: አንደኛዋ ሴት "እሺ እንካፈል" ስትል እውነተኛዋ እናት ግን "ልጄ ከሚሞት እርስዋ ትውሰደው" አለች:: እናት መሆንዋም በዚህ ታወቀ::

ወዳጄ ያንተም ኑሮህ ከእግዚአብሔር ጋር ላይሆን ይችላል:: ዓለም የራስዋ አድርጋህም ይሆናል:: በሱስ ውስጥ ትዘፍቀህ ፣ እንደ ሶምሶን በደሊላ እቅፍ ፣ እንደ ዴማስ በተሰሎንቄ ውበት ተማርከህ ይሆናል:: እግዚአብሔር ግን አባትህ ነውና ሞትህን አይፈልግም::

"ልጄ ከሚሞት እርስዋ ትውሰደው" እንዳለችው እናት ፈጣሪህ ከነኃጢአትህም ቢሆን እንድትሞት አይፈልግም:: ከእርሱ ጋር ባትኖርም መኖርህን ይፈልጋል:: "የሟቹን ሞት አልፈቅድምና፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ስለዚህ ተመለሱና በሕይወት ኑሩ" ሕዝ. 18:32

የይሁዳ ኃጢአቱ ጌታውን መሸጡ አልነበረም:: ራሱን መግደሉ ነው:: እግዚአብሔር የሚያዝነው ከበደልህ በላይ በእርሱ ተስፋ ቆርጠህ ራስህን ስትጎዳ ነው::

ወዳጄ የአንተን መኖር የሚፈልጉ ብዙ ናቸው:: ፈጣሪ ወደዚህች ዓለም ያለ ምክንያት አላመጣህም:: በአንተ አለመኖርም የሚጎድል ነገር አለ:: አንተን የሚመስል ሌላ ሰው አልፈጠረምና ለዚህ ዓለም አንተን የሚተካ የለም:: በክብር ወደዚህ ዓለም ያመጣህ አምላክ በክብር ወደራሱ እስኪወስድህ ድረስ "በራስህ ላይ ክፉ ነገር አታድርግ"

"የወኅኒውም ጠባቂ ከእንቅልፉ ነቅቶ የወኅኒው ደጆች ተከፍተው ባየ ጊዜ፥ እስረኞቹ ያመለጡ መስሎት ራሱን ይገድል ዘንድ አስቦ ሰይፉን መዘዘ።
ጳውሎስ ግን በታላቅ ድምፅ፦ ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ፡ ብሎ ጮኸ" ሐዋ. 16:27-28

ይህ ሰው እስረኛ ያመለጠ መስሎት ራሱን ሊያጠፋ ሲል ጳውሎስ "ሁላችን ከዚህ አለንና በራስህ ክፉ ነገር አታድርግ" አለው::

ወዳጄ አንተስ ተስፋ የቆረጥኸው ምን ያመለጠ መስሎህ ነው?

7 months, 2 weeks ago

‹‹አዲስ ዓመት መልካሙን የምንሰራበት ይሁንልን!››

:
☞ዘመናትን የሚያቀያይርና አዲስ ዓመትን የሚሰጠን እርሱ
ፈጣሪ ነው።
:
ይህንን የፈጣሪን ምህረትና ቸርነት የምናስብ ስንቶቻችን
ነን?
:
ሰው ደግሞ ተጨማሪ አዲስ ዓመትና እድሜ ካልተሰጠው
ምንም ማድረግ አይችልም፡፡
:
ፈጣሪ እንድንኖር ካልፈቀደልን አዲሱን ዓመት ካልሰጠን
ምንም ነገር ማድረግ አንችልም፡፡
:
# ሌላው ቀርቶ፦

➊.ወጥተን→የምንገባው፣
:
➋.ተቀምጠን→የምንነሣው፣
:
➌.ተምረን ለውጤት→የምንበቃው፣
:
➍.ሠርተን→የምናገኘው፣
:
➎.ነግደን→የምናተርፈው፣
:
➏.ወልደን→የምንስመው፣
:
➐.ለመጪው ዓመት ብለን እቅድ→የምናቅደው ፈጣሪ እንደ
ቸርነቱ ወደ አዲሱ ዓመት እንድንሸጋገር ሲፈቅድልን ነው፡፡
:
√ብዙ ሰዎች ግን የፈጣሪን ቸርነት ረስተዋል፡፡
:
√አዲስ ዘመን ሲሰጠን ዋጋ የሚከፈልበት ቢሆን ኖሮ ዋጋውን
ማን ይችለው ነበር?
:
√ግን ፈጣሪ አዲስ ዓመት የሰጠን ያለዋጋ በነፃ ነው።

√ለምንኖርበት ዕድሜ ለሰጠን ተጨማሪ ዓመት የጠየቀን ዋጋ
የለም፡፡
:
√ታዲያ ጊዜ የሰጠን ፈጣሪ ደግሞ ጊዜ እንድንሰጠው
እንድናመሰግነው ይፈልጋል።
:
❀︵♡︵♔︵♡︵♔︵♡︵♔︵♡︵❀
:
# አዎን ወዳጆቼ፥

☞አንዳንድ ሰዎች እንዲኖሩ፣ እንዲወጡና እንዲወርዱ አዲስ
ዓመትና ጊዜ ፈጣሪ ሰጥቷቸው ሳለ አዲስ ዓመት ለሰጣቸው
ለፈጣሪ ግን ጊዜ መስጠትና ማመስገን ተስኗቸው
ይስተዋላሉ፡፡
:
♡ይህቺን ቀን አስበው እዚህች ቀን ላይ፣ ለዚህች ዓዲስ
ዓመት ያልደረሱ ብዙ ሰዎች አሉ።

♡አንተ እኔ ሁላችንም ግን ደርሰናልና እንደ ቸርነቱና ምህረቱ
ለዚህ ላደረሰን አምላካችን እንዲህ እያልን እንፀልይ፦

➊.አምላካችን ሆይ፥ አዲሱን ዓመት ስለሰጠኸን
እናመሰግናሀለን።
:
➋.አምላካችን ሆይ፥ ከዚህ በኋላ የሚኖረን ቀሪ እድሜ
በፊትህ ያማረ ይሁንልን፡፡
:
➌.አምላካችን ሆይ፥ እድሜና ዘመናችን በቤትህ ይለቅ፡፡
:
ማለዳ ማለዳ በአዲስ ምስጋና፣
:
በአዲስ ዝማሬ፣
:
በአዲስ ሽብሸባ፣
:
በአዲስ ቅኔ፣
:
በአዲስ እልልታ ይህ በረከት የሆነው እድሜና ዘመናችን
በቤትህ ይለቅ፡፡

➍.አምላካችን ሆይ፥ ሳናመሰግንህ ላለፉት የምህረት
አመታት ሁሉ ዛሬ ይቅር በለን፡፡
:
➎.አምላካችን ሆይ፥ የሚከፋፍለን የሚያለያዬንን የጥል፤
የክርክር፤ የዘረኝነት ግድግዳ አንተ አፍርስልን።
:
➏.አምላካችን ሆይ፥ በአዲሱ ዓመት ፍቅርና አንድነትን
ስጠን።
:
➐.አምላካችን ሆይ፥ ሐገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ባርክ።
:
➑.አምላካችን ሆይ፥ በሰጠኸንም እንደ ቸርነትህ
በጨመርክልን አዲስ ዓመት መልካሙን እንድንሰራበት አንተ
ይርዳን! # ለዘላለሙ አሜን!
:
♡እስኪ ተመስገን በሉት። ተመስገንንንንንንንንንንንንንንንን
:
❀︵♡︵♔︵♡︵♔︵♡︵♔︵♡︵❀
:
# መጪው አዲስ ዓመት፦

➊.ሀጥያትን→በጽድቅ፣

➋.አለመጸለይን→በመጸለይ፣

➌.ስጋዊነትን→በመንፈሳዊነት፣

➍.አለማገልገልን→በማገልገል፣

➎.ድህነትን→በመስራት፣
:
➏.አለማንበብን→በማንበብ፣
:
➐.አለማወቅን→በመማር፣
:
➑.ጥላቻን→በፍቅር፣
:
➒.ክፉን→በመልካም፣
:
➓.ንፉግነትን→ በመስጠት፣ የምንከርመበትና ፍቅር የበዛበት
ብሩህ ዘመን ይሁንልን!
:
[☞መልካም አዲስ ዓመት☜]
:
«ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያካፍሉ»
:
"ሰላማችሁ ይብዛ"
:

8 months, 1 week ago

እንኳን በአምላክ መጾር «በጳጳስ መንበር ቄስ ፣ በንጉሥ ዙፋን ራስ» ደፍሮ እንደማይቀመጥበት የእርሱንም ምዕራፈ ክብር ማንም አይጋራውም።

"ወይከውን ዘዚአሁ ምዕራፈ ክብር … ማረፊያውም የተከበረ ይሆናል።” [ኢሳ ፲፩፥፲]

የተመረጠው ፃድቅ ዮሴፍ ተከታይ ሞግዚቷ መንፈሳዊ አባቷ እየሆነ ፦ አማናዊት መቅደስ እናቱን ፣ ቅድስተ ቅዱሳን ትስብእቱን ሐዲስ ካህን ሆኖ ያገለገለ አረጋዊ ነው! እርሱ ምንም እንኳ በመጀመርያዋ መጽሐፍ (ብእሲቱ) በኩል ልጆች ማንበብ የሚያውቅ ቢሆንም የታተመችውን መጽሐፍ (እመ አምላክ ድንግልን) ግን በግብር አልደረሰባትምና ከመጠበቅ ውጪ እርሷን ማንበብ አይቻለኝም አለ!

“ ማንበብንም ለሚያውቅ፦ ይህን አንብብ ብለው በሰጡት ጊዜ እርሱ፦ ታትሞአልና አልችልም ይላቸዋል፤” [ኢሳ ፳፱፥፲፩]

ወደዓለም የመጣውን በኩር በሥጋ ያሳየች የበኩር እናት ተሰኘች እርሱም የበኩር ልጇ ተብሎ ተከታይ እንዳይኖረው ወልዳ ዘበኩር ተብሎ ተጠርቷል!

ይኽን ካልን ወደ ማሕፀኗ መውጣቱን ፣ በሥጋ እናቱ በምትሆን አርያም ዙፋን ማደሩን በተዋሕዶ አንድነት ምሥጢራዊ ዕርገት ይዘን ወደሰማይ ማረግ ካልነው ኋላ በአርባኛው ቀን በመርቀቅ ሳይሆን በመራቅ ከቅዱሳን ሐዋርያቱ ተለይቶ ወደላይ ሲወጣ ተመለከትንና ይኽንን (በረቀቀው ጽንሰት ስለተከወነ ዕርገት) በትህትና ያንን (በክብር ማረግ በተዋህዶ አካል ወደ ላይ መውጣቱን ) በልዕልና አልነው።
ሐዋርያው ያን በልዕልና የተፈፀመ ከትህትናው ሲለይ "ወአርገ በስብሐት ⇝ በክብር ያረገ ” (፩ኛ ጢሞ ፫፥፲፮) ሲለው ፤ ዳዊት ሁለቱን ሰማይ አካቶ ይኽን ሰማይ ያንን ከሰማያት በላይ ያለ ሰማይ ብሎ "ዘዓርገ ውስተ ሰማየ ሰማይ ዘመንገለ ጽባሕ " በማለት ገለጠው፤
↳ “በምሥራቅ በኩል ወደ ሰማየ ሰማያት ለወጣ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፤ ” (መዝ. ፷፰፥፴፫)

በቅዱስ ኤጲፋንዮስ ቅዳሴ "በይእቲ ሥጋ ምስለ ኃይለ መለኮት ውስተ ሰማያት ዐርገ ኀበ ዘትካት ህላዌሁ ⇝ ከእናቱ በነሳው በዚኽ ሥጋ ከመለኮቱ ኃይል ጋር ወደ ቀደመ መኖርያው ወደ ሰማይ ዐረገ" እንዲል፤

————————————————————
ታቦተ መንፈስ ቅዱስ እመቤታችንን ስለምን ቀድሞ አስነሳት? ————————————————————

በፍለሰታው ሱባዕያት በሊቃውንቱ ቅዳሴ ማርያም ሲተረጎምልን እንደምንሰማው "ትምክሕቶሙ ለወራዙት ወደናግል ወመነኮሳት እለ ይተግሁ ውስተ አናቅጺሃ መዓልተ ወሌሊተ … በእርስዋ ደጃፍ (በራፍ) ሌሊትና ቀን ደጅ ለሚጠኑ ወጣቶች ደናግላንና መነኮሳት ትምክሕት ናት" ይላል ሊቁ አባ ሕርያቆስ።

በደጃፎችዋ በሚለው በሕዋሳቶቿ ለሚማጸኑ ትምክሕት ናት ይላል፤ ሕዋሳቶችዋን በሚያነሳ የሰውነት አባላቶቿን በሚያወሳ የመልክ ሰላምታ ለሚያወድሳት ትምክሕት ናት! ለምን? ለእርሱ ማደርያነት የተገቡ ናቸውና ለዘልዓለም ከብረው የሚኖሩ፤ ከፍጥረት ኹሉ ቀድመው ፈጣሪን በከዊን ያወቁና ፈጣሪን በግዘፍ ለፍጥረት ያሳወቁ ደጆች ፦ የተሸከመውን ማሕፀን፣ የጠባውን አጥባት፣ ያዘለውን ዘባን፣ ያቀፈውን እራኅ፣ በፈጣሪ የተሳመ መልታሕት… ከሌሎች ፍጡራን የአካል አባላት እና የሰውነት ሕዋሳት አብልጦ ይወዳቸዋል።

ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት መዓዛ መለኮቱ የማይለያትን የሽቱ ሙዳይ “ያበድሮን እግዚአብሔር ለአናቅጸ ጽዮን ⇝ እግዚአብሔር የጽዮንን ደጆች አብልጦ ይወድዳቸዋል።” እንዳለ [መዝ ፹፮ (፹፯)፥፪] አብልጦ ይወዳቸዋልና እንደፍጡሩ ለመፍረስ ለመበስበስ አሳልፎ አልሰጠውም!

በእንዚናዙኑ ሊቅ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ቅዳሴ ላይ "ለብሰ ሥጋ ዘይማስን ወረሰዮ ዘኢይማስን" እንደተባለ፤ ከሚፈርሰው ከእኛ ሰውነት የማይፈርሰውን ሕያው አምላክ ለማስገኘት የተመረጠችው የአብ መርዓት፣ የወልድ ወላዲት የመንፈስ ቅዱስ ታቦት የደጆችዋ መቆለፊያ በመቃብር መጥፋት በእሳትም መቃጠል ሳያገኛቸው ጸንተው ኖረዋል፤

“ጽዮንም ሆይ፥ ለአምላክሽ እልል በዪ፤ የደጆችሽን መወርወሪያ አጽንቶአልና " እንዲል [መዝ ፻፵፯፥፲፫]

ፀሐይን ያሠረቀች ዳግሚት ሰማይ፣ እግዚአብሔርን የወለደች እመ አዶናይ ፣ በሥጋና በኅሊና ዘልዓለም ድንግል የሆነች እግዝእትነ ማርያም፦
† በእነታውፋንያ ቁጣ የመጡ አይሁድ ሥጋዋን ለማቃጠል ያሰቡበት ምክር ስለምን ፈረሰ?
† በእሳት ያልጠፋውን ሥጋ "ወኢይገድፍ ምዕቅብናየ ⇝ አደራዬንማ አልተዋትም" ሲል ቅዱስ ዮሐንስ በንጽሕና በእጸ ሕይወት ሥር ሲያገለግላት መቆየቱ ለምነው?
ቀድሞ እሳት ያላቃጠለው ፣ ኋላም አፈር ያልበላውማ ስለሥጋዋ ክብር ነው እንጂ! ተረድተነውማ ቢሆን «ተቀብራ አልተነሳችም» ማለት "ወኢአማሰነ በልደቱ" እንዲል በልደቱ ያልለወጠውን የማደርያውን ክብር በሞት መፍረስና በመቃብር መበስበስ አግኝቶታል፤ አፈር ለውጦ አጥፍቶታል ወደማለት ያደርሳል! ላቲ ይደሉ ክብር ወስብሀት ወለወልዳ አምልኮ ወስግደት።

"ወይከውን ዘዚአሁ ምዕራፈ ክብር … ማረፊያውም የተከበረ ይሆናል።” [ኢሳ ፲፩፥፲]

————————————————————
☞ በቴዎድሮስ በለጠ ◆ ከአርባምንጭ ዚጊቲ አቦ ("#ዝግሕት_ይእቲ") ⇨ [ ነሐሴ ኪዳነ ምሕረት ፳፻፲፩ ዓ.ም ]
————————————————————

We recommend to visit

★ሰውን በማዝናናት የብቃት ማረጋገጫ ያለው ብቸኛው ቻናል ሁሌም Telegram ላይ በጥበብ ደምቀን እናሸበርቃለን

💌 Contact us, @Modenyazbot

»የተመረጡ እና ማንም ያላያቸው የአማሪኛ ቀልዶች እንዲሁም የሚያስደንቁ ስዕሎችንና ቪዲዮ ያገኛሉ።

° ° [ ሙድ እንያዝ በእኛ የአራዶች መዝናኛ ] ° °

° ° Creator @Teke_Man ° °

Last updated 2 months ago

☕ ስለ ኢትዮጲያ ቡና የሚወጡ ወቅታዊና ትክክለኛ የክለቡ መረጃዎች አዚህ ያገኛሉ!

➪የዝዉዉር ዜና
☞የአሰልጣኞች አስተያየት
➪ጎሎች እና ቪዲዮዎች
☞የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
➪ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት ከየስታድየሙ !

➡መወያያ ግሩፓችን @Ethiopia_coffee_Sc

📩ሀሳብ ወይም አስተያየት ካሎት
በዚህ 👉 @EthiopianCoffeeScBot ✍
BOT ማድረስ ይችላሉ!

Last updated 4 days, 3 hours ago

እንኳን ወደ # ሉሲ የቴሌግራም ቻናል በደህና መጡ
#የሉሲ /LUCY DINKINESH E/ቤተሰብ ሰለሆኑ ደስብሎናል።

መረጃ መስጠት የምትፈልጉ በዚ አድርሱን 👉 @CACA77

# የኢትዬጵያዊነት የአሸናፊነት መገለጫ አርማችን ነው!
ነፃነታችንን 💪በፈርጣማው ጡንቻችን ይረጋገጣል
👉 ኢትዬጵያዊነት አርበኝነት የማንነት አርማች ነው
🙏🙏🙏

Last updated 1 month ago