Dive into the Ultimate Free Library: Your One-Stop Hub for Entertainment!

🕋ISLAMIC ZONE🕋

Description
"ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራ ሰውን አጅር ያህል ያገኛል" ረሱል (ﷺ)

ሌላኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ @hanif_tube
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።

ያግኙን +251913134524

Last updated 1 месяц назад

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @MKHI7

Last updated 1 месяц назад

BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot

Last updated 2 недели, 1 день назад

1 month ago

አስቸኳይ ማሳሰቢያ

አሽረል-አዋኺር (የረመዷን የመጨረሻ አስር ቀናት) ሲገባ ብዙ ቦታ ላይ በብዙዎች የሚፈፀም ትልቅ ጥፋት አለ እሱም ለተሀጁድ ሶላት ወደ መስጂድ በመምጣት ከሰገዱ በሗላ ሶላቱ ሲጠናቀቅ ብዙ ሰዉ ስኹር ለመመገብ ወደ ቤቱ ይሄዳል ታዲያ ለሱብሒ ሶላት ወደ መስጂድ የሚመለሰዉ ትንሽ ሰዉ ነዉ አብዝሀኛዉ ሰዉ ስሁር በልቶ እዛዉ እቤቱ የሱብሂ ሶላትን ሰግዶ ነዉ የሚተኛዉ ይህ እጅግ በጣም ትልቅ ስህተት ነዉ::

وقد روى الإمام مالك في "الموطأ" (270) عَنْ أَبِي بَكْرِ بْنِ سُلَيْمَانَ بْنِ أَبِي حَثْمَةَ : " أَنَّ عُمَرَ بْنَ الْخَطَّابِ فَقَدَ سُلَيْمَانَ بْنَ أَبِي حَثْمَةَ فِي صَلَاةِ الصُّبْحِ ، وَأَنَّ عُمَرَ بْنَ الْخَطَّابِ غَدَا إِلَى السُّوقِ ، وَمَسْكَنُ سُلَيْمَانَ بَيْنَ السُّوقِ وَالْمَسْجِدِ النَّبَوِيِّ ، فَمَرَّ عَلَى الشِّفَاءِ أُمِّ سُلَيْمَانَ ، فَقَالَ لَهَا : لَمْ أَرَ سُلَيْمَانَ فِي الصُّبْحِ . فَقَالَتْ : إِنَّهُ بَاتَ يُصَلِّي فَغَلَبَتْهُ عَيْنَاهُ ، فَقَالَ عُمَرُ : " لَأَنْ أَشْهَدَ صَلَاةَ الصُّبْحِ فِي الْجَمَاعَةِ أَحَبُّ إِلَيَّ مِنْ أَنْ أَقُومَ لَيْلَةً

كتاب صلاة الجماعة باب ما جاء في العتمة والصبح (حديث رقم: 293 )

አቡበከር  ብን  ሱለይማን  ቢን  አቢ  ሃተምህ  እንዳስተላለፉት፡-  “ዑመር  ቢን  አል-ኸጣብ  (ረዲየላሁ ዐንሁ)  ሱለይማን  ቢን  አቢ  ኸተማን  የሱብሒ  ጀመዓ  ሶላት  ላይ  ኣጡት።  ዑመር  ኢብኑል  ኸጣብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) በጠዋት  ወደ  ገበያው  ሲያመሩ  በሱለይማን  መኖሪያ  ቤት  በኩል  አለፉ። የሱለይማን  ቤት   በነብዩ  መስጂድ  እና  በገበያዉ  መካከል  ስለነበር  የሱለይማን  እናት  ዘንድ  አለፋ  እና  “የሱብሒ ጀመዐ ሰላት ላይ  ሱለይማንን  አላየሁትም”  አላት።  ሌሊቱን  ሲሰግድ  አይኖቹም  ደከሙ  እንቅልፍ  አሽነፈዉ።”  ዑመርም  “- ለሊቱን  ሙሉ እየሰገድኩ  ከማደር  ይልቅ  በጀመዓ  ሱብሒ  መስገድ  ለኔ  በጣም  የተወደደ  ነው።  አሉ

ኢማሙ ማሊክ “አል-ሙወጣእ”
ኪታቡ  ሰላቱል  ጀመዐ  293

አላህ በኛ ላይ ግዴታ ያደረገብን የሱብሒ ሶላትን ነዉ:: ወንድ ልጅ የግዴታ ሶላቶችን በመስጂድ ነዉ መስገድ ያለበት የተሐጁድ ሶላት መስገድህ የሱብሒ ሶላትን በጀመዐ ለመስገድ የሚያዳክምህ እና እንዳትችል የሚያደርግህ ከሆነ የተሐጁድ ሶላቱ ቢቀርብህ ይሻላል!

🕋🕌@islamic_zonee🕌🕋

1 month ago

[አላህ ሆይ! አንተ በጣም ይቅር ባይ ነህ፣ይቅርባይነትን ትወዳለህና ይቅር በለኝ

አዒሻ (ረዐ) ባስተላለፉት ሐዲስ መሰረት ‹‹የአላህ መልእክተኛ ሆይ! ለይለቱል ቀድር ቢገጥመኝ ምን ብዬ ዱዓእ ላድርግ? ስላቸው፣

‹አል’ሏሁምመ እን’ነከ ዐፉው’ዉን ቱሕቡል ዐፍወ ፈዕፉ ዐን’ኒ›

(አላህ ሆይ! አንተ በጣም ይቅር ባይ ነህ፣ይቅርባይነትን ትወዳለህና ይቅር በለኝ) በይ አሉኝ፡፡›› [ቲርሚዚ ዘግበውታል]](http://t.me/islamic_zonee)

🕋🕌@islamic_zonee🕌🕋

1 month, 1 week ago

[**ዐሽረል አዋኺር (አሥርቱ ቀናት)

በተባረከው የረመዷን ወር ዉስጥ የሚገኙት አሥሩ የመጨረሻ  ውድ ቀናት መጡ። በነኚህ ቀናት ዉስጥ አምልኮም ሆነ ማንኛዉም መልካም ሥራ የተወደደና ከፍ ያለ ደረጃ ያለው ነው፡፡

ጅማሮ -
አሥርቱ ቀናት የሚጀምሩት በረመዷን 21ኛው ምሽት ላይ ነው፡፡ ወሩ ሙሉ ከሆነ እስከ ረመዷን 30ኛው ቀን ምሽት ይቆያሉ፡፡

ምሽቶቹን ምን ልዩ ያረጋቸዋል?

ለይለቱ ቀድር የምትባል ምሽት ከአሥርቱ ቀናት በአንዱ ዉስጥ አለች፡፡  ይህችን ቀን በነኚህ ቀናቶች ዉስጥ በርትተን እንድንፈልግ ረሱል ሰ.ዐ.ወ. መክረዉናል፡፡

ለይለቱል ቀድር ምንድናት?

ከሺህ ሌሊቶች የምትበልጥ ትልቅ ደረጃ ያላት ምሽት ናት፡፡

ቀኗ በትክክል ይታወቃል?

በትክክል አይታወቅም፤ ነገርግን በተለይም ዋናነት በምሽቶቹ ነጠላ ቀናት ዉስጥ ማለትም በ21፣ በ23፣ በ27፣ በ29 ዉስጥ ፈልጉ ተብሏል፡፡
ለይለቱል ቀድር የሚባል ዱዓ ይኖራል? - እናታችን ዓኢሻ ረ.ዐ አላህ ለይለተል ቀድርን ከወፈቀኝ ምን ልበል? በማለት የአላህን መልዕክተኛ ሰ.ዐ.ወ ጠይቃቸው “ አልሏሁም ኢንነከ ዐፉዉን ቱሒቡል ዐፍው ፈዕፉ ዐንኒ” በይ ብለዋታል፡፡ “አላህ ሆይ አንተ ይቅር ባይ ነህ፤ ይቅር ማለትን ትወዳለህ፤ ይቅር በለኝ፡፡” ማለት ነው ትርጉሙ፡፡

ረሱል ሰ.ዐ.ወ በነኚህ ቀናት ዉስጥ ምን ያደርጉ ነበር?

በነኚህ ቀናት ዉስጥ ነቢዩ ሰ.ዐ.ወ. በአምልኮ ከሌላው ጊዜ በበለጠ በእጅጉ ይበረቱ ነበር፡፡ ቤተሰቦቻቸዉንም ያነቁ ነበር፡፡ ከሌላው ጊዜ በበለጠ ይለግሳሉ፡፡ ሌሊቱን በዚክር እና በዒባዳ ያሳልፋሉ፡፡ ኢዕቲካፍም ይገባሉ፡፡

ኢዕቲካፍ ምንድነው?

ኢዕቲካፍ ማለት አምልኮና ወደ አላህ መቃረብን በማሰብ ራስን ከዓለማዊ ጉዳዮች አርቆ ለተወሰነ ጊዜ፣ ሰዓታት፣ ቀን ወይም ሌሊት መስጂድ ዉስጥ መቆየት ነው፡፡ ኢዕቲካፍ ነቢያዊ መንገድ ነው፡፡ በአሥርቱ ቀናት ዉስጥ እስከሚሞቱ ድረስ ኢዕቲካፍን አልተዉም ነበር ብላለች እናታችን ዓኢሻ፡፡

የኢዕቲካፍ ጥቅሙ ምንድነው?

ኢዕቲካፍ ከዓለማዊ ጉዳዮች ያርቃል፣ ሙሉ በሙሉ ቀልብን ወደ አላህ በመመለስ ከአላህ ጋር መገለልን ያስገኛል፡፡ ነፍስን ያጠራል፣ መንፈስን ያድሳል፣ ቀልብን ያንፃል፡፡ ራሣችን እንድንፈትሽና እንድንገመግም ዕድል ይሠጠናል፡፡

በኢዕቲካፍ ጊዜ ምን ይወደዳል?

በኢዕቲካፍም ሆነ በአሥርቱ ቀናት ዉስጥ ሶላት ማብዛት፣ ኢስቲግፋር (አላህን ምህረትን መለመን) ማብዛት፣ ቁርኣን መቅራት፣ ዚክር ማድረግ፣ ሶደቃ መስጠት፣ ዱዓ ማድረግ፣ መልካም ሥራዎችን ማብዛት ይወደዳል፡፡ በአጠቃላይ ማንኛዉንም መልካም ነገር ሁሉ ሳይሠለቹ አብዝቶ መሥራት ይወደዳል፡፡

አላህ ሆይ ከሚጠቀሙበት አድርገን ለይለተል ቀድርንም ወፍቀን ያ ረብ!!!**](http://t.me/islamic_zonee)

🕋🕌@islamic_zonee🕌🕋

3 months ago

*⭕️አንዳንዴ ሶደቃ (ምፀዋት) ባለቤቷ ትላልቅ ወንጀሎች ያሉበት ከሆነ ሳት ውስጥ ከመግባት ታድነዋለች⭕️*

🔸 መልክተኛው ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም እንደህ ብለዋል:-
"اتقوا النار ولو بشق تمرة"
❝በተምር ግማሽ እንኳን ቢሆን ሳትን ራቁ❞
በኻሪይ እና ሌሎችም ዘግበውታል።
📌ማለትም ግማሽ ተምርን እንኳ ሶደቃ በመስጠት የጀሀነምን ሳት ራቁ ማለት ነው።

🔸ከአቢ ሁረይራህ እንደተዘገበው ነቢዩ ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፡

"ﺇﻥّ ﺍﻣﺮﺃﺓً ﺑﻐِﻴّﺎ ﺭﺃَﺕ ﻛَﻠﺒًﺎ ﻓﻲ ﻳﻮﻡٍ ﺣَﺎﺭّ ﻳَﻄِﻴﻒ ﺑﺒِﺌﺮ ﻗَﺪ ﺃﺩْﻟَﻊ ﻟِﺴَﺎﻧﻪ ﻣﻦَ ﺍﻟﻌَﻄﺶ ﻓﻨَﺰﻋَﺖ ﻟﻪُ ﺑﻤُﻮﻗﻬﺎ ﻓﻐﻔﺮَ ﻟﻬﺎ"

🔸❝አንድ ዝሙት የምትሰራ ሴት ልጅ ሙቀት በበዛበት ጊዜ አንድን ውሻ ከመጠማቱ የተነሳ ምላሱን አውጥቶ በጉድጎዱ ሲዞር አየች ከዛም በጫማዋ (ውሃን አውጥታ አጠጣችው) አሏህም (ወንጀሏን) ማረላት❞
ቡኻሪይ እና ሙስሊም ዘግበውታል።**

3 months, 1 week ago

ከትንሳዔ መከራ ለመዳን…

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿مَنْ سَرَّهُ أَنْ يُنْجِيَهُ اللَّهُ مِنْ كُرَبِ يَوْمِ الْقِيَامَةِ فَلْيُنَفِّسْ عَنْ مُعْسِرٍ، أَوْ يَضَعْ عَنْهُ﴾

“ከትንሳኤ መከራ አላህ ነፃ እንዲያወጣው የወደደ ሰው ያበደረውን ሰው እዳ ያቅልለት ወይም ሙሉ ለሙሉ ያንሳለት።”

📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1563

3 months, 1 week ago

◈ሶብር የሚያደርግ ሰው ታላላቅ ደረጃዎችን ይጎናጸፋል።
◈ ሶብር የድልና የስኬት ቁልፍ 🔑 ነው!

አሏሁ በሁሉም ነገር ላይ ሷቢሮች ያድርገን🤲

3 months, 1 week ago

የ125 ብር ካርድ ሊለቀቅ ነው 9 ደቂቃ ብቻ ነው የቀራው። ቶሎ ከስር JOIN ሚለውን ነክታቹ JOIN REQUEST ላኩ 🏃‍♀️🏃‍♂️

3 months, 1 week ago

[🎧🎵የማንን ሙዚቃ ማዳመጥ ይፈልጋሉ👇

👤 Mikaya Behailu

👤 Minyeshu Kifle

👤 Muluken Melesse

👤 Neway Debebe

👤 Nati Haile

👤 Nhatty Man

👤 Sami Dan

👤 Sayat Demissie

👤 Seleshe Demissie

👤 Shewandagne Hailu

👤 Tamrat Desta

👤 Teddy Afro

👤Aster Awoke

👤Abnet Agonafr

👤Geremew Asefa

🌐 All Ethiopian Music🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶](https://t.me/+OEwmYncg87c5YjFk)

3 months, 1 week ago

*☑️ የበደልከውን ሰው እምባ ፍራ
〰️*〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️

◾️‏قال الرافعي رحمه الله :
ራፍእይ አላህ ይዘንለትና እንዲህ ብሏል።

【دموع المظلومين هي في أعينهم دموعٌ، ولكنّها في يد الله صواعق ، يضرب بها الظالم】
📍 የተበዳዮች እምባ በአይናቸው ሲታይ ፈሳሽ ውሃ ነው። ነገር ግን ይህች እምባ አላህ ዘንድ በዳዩን አካል ድምጥማጡን የምታጠፋ እንደ መብረቅ ነች።
📚وحي القلم-(١ /٤٤٩**)

3 months, 2 weeks ago

وَمَا تَنقِمُ مِنَّا إِلَّا أَنْ آمَنَّا بِآيَاتِ رَبِّنَا لَمَّا جَاءَتْنَا ۚ رَبَّنَا أَفْرِغْ عَلَيْنَا صَبْرًا وَتَوَفَّنَا مُسْلِمِينَ

«የጌታችንም ተዓምራቶች በመጡልን ጊዜ ከማመናችን በቀር ከእኛ አትጠላም፡፡ ጌታችን ሆይ! በእኛ ላይ ትዕግስትን አፍስስ፡፡ ሙስሊሞች ኾነን ግደለን፡፡»(አዕራፍ 126)

ከሚያምረው የትዕግስታችን መገለጫ ውስጥ አንደኛው ሰዎች ሲመለከቱን እኛ ህይወት ላይ ምንም ዐይነት ሙሲባ እየደረሰ እንዳልሆነ እንዲያስቡ ስናደርግ እና ለሌሎች ምን ዐይነት ፈተና ውስጥ እያለፍን እንደሆነ ግን ወደን እንደተቀበልን እና ችለነው እየኖርን እንደሆነ ለማስረዳት አለመሞከራችን ነው። ምክንያቱም እንደ ረሱል ዐለይሂ ሰላቱ ወሰላም ከሁሉም በላይ ሀሳብ እና ጭንቀት ኖሮበት እንደእርሳቸው ትዕግስት አድርጎ ፈገግታን ፊቱ ላይ እሚያሳይ ሰው አለመኖሩ እንዲሁም እኛ ደግሞ በእርሳቸው ያማረ ጎዳና ላይ መሆናችን ነውና።

❤️❤️❤️اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد صلى الله عليه وآله وصحبه أجمعين ❤️❤️❤️
በሰብር፣ በካህፍ፣ በዱዓ በሰለዋት ያሰብነው የሚሳካበት ያማረ እና የፈካ ጁምዓ ይሁንልን!!!

የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉhttps://t.me/islamic_zonee ለወዳጅ ዘመዶው ያጋሩ ባረከላሁፊኩም

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።

ያግኙን +251913134524

Last updated 1 месяц назад

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @MKHI7

Last updated 1 месяц назад

BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot

Last updated 2 недели, 1 день назад