ሀሁ መጻሕፍት /Hahu books

Description
Subscribers

We recommend to visit

Books only!

This channel is created for books sharing To widen your mind and to get books easily We have more than 2000 amharic and english books !

Join and share @Books_worldd

አስተያየት @BooksWorlddd_bot !

@books_worlddd መወያያ ግሩፕ

#share

📚📖 🌟✨እንኳን በደህና መጡ✨🌟📖 📚

➥ እዚህ ቻናል ላይ የተለያዩ የ አማርኛ እና English መፅሀፍትን በ 📙 Pdf እና ትረካዎችን እና ሌሎችም ጠቃሚ ነገሮችን ያገኛሉ።

📖 ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል‼️

መልካም ቆይታ ከ @Ethio_Books ጋር ✌

ለማንኛውም ሀሳብ አስተያየት በ 👉 @Ethio_booksbot ላይ ያድርሱን እናመሰግናለን።

Last updated 11 months ago

Ethiopian Books, Files and Historical Documents.

Use @etbookstorebot to send us any comments or documents.

3 months ago
ሀሁ መጻሕፍት /Hahu books
3 months ago

በረ/ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው (የታሪክ መምሕርና ተመራማሪ) የተሰናዳው ማሕደረ ጀግንነት ወማሕደረ ንዑዳን መጽሐፍ ሊመረቅ ዛሬ ከቀኑ ከ8:00 ሠዓት ጀምሮ በራስ አምባ ሆቴል ይመረቃል።

የአገረሰብ ዕውቀት፣ የሥነ-ልሳን እና የታሪክ ተመራማሪው ጆርጅ ብራይን ሃንቲንግፎርድ ተርጉሞ እና አሰናድቶ ባቀረበየው (Glorious Victories of Amda Seyon: King of Ethiopia) የኢትዮጵያው ንጉስ ዐምደ ጽዮን የጀግንነትና የድል ሐተታ ዜና መዋዕል ስለ ንጉሱ የድል ሚስጥርና የጦር አሰላለፍ በስፋት ተነስቷል። ፀሐፌ-ታሪክ ተክለጻድቅ መኩሪያ ንጉስ ዐምደ ጽዮን የጦር ስልጠና እና አወቃቀር "የኢትዮጵያ ታሪክ: ከዐፄ ይኩኖአምላክ እስከ ዐፄ ልብነድንግል" በተሰኘው የታሪክ መፅሐፍ ቢፅፉትም፣ በዜና መዋዕሉ በተለየ አፅንዖት ተገልጿል።

ሃንቲንግፎርድ ገፅ 81-82 ድረስ፣ ንጉሱ ዐምደ ጽዮን ጃናሞራ፣ ኮረም፣ ጎጃም፣ ሐድያ፣ ተኩላው የተባሉ እጅግ የሰለጠኑ ኢትዮጵያን ጠባቂ እግረኛና ፈረሰኛ ጦር ያደራጁ ቢሆንም፣ ማንኛውንም ጥቃት፣ ኃይል እና ጦር የሚያፍረከርከው፣ በዜና መዋዕሉ፣ "በወርቅና በብር የተጌጡ ጦር፣ ጎራዴና ጋሻ ታጣቂ፣ ሲዋጉ እንደ ንስር አሞራ በጠላት ላይ የሚሽከረከሩ፣ ሲያጠቁ እንደ ሚዳቋ በፍጥነት የሚፈናጠሩ፣ ከገጠሙ ያለ ድል የማይመለሱ፣ ተናዳፊ የሆኑ 'ቀስተ ንኅብ' (Spears of the Bee) የተሰኘው የሸዋውን ጦር ዕዝ አደራጅተው ነበር። ቀስተ ንኅብ በቁጥር ከሌሎች ዕዞች ያነሰ፣ ግን በጦር ስልትና ጀብዱ ከዐምደ ጽዮን ቤተ መንግስት እስከ ቀይ ባሕር እና ግብፅ በረሃ የሚወረወር የኢትዮጵያ ክንድ ነበር ብሎታል።

የእኛ ዘመን ቀስተ ንኅብነት የተመሰከረበት፣ ዳግም ለኢትዮጵያ የተከፈለ ውዱ መስዋዕትነት፣ የወገን ፍቅር፣ በገቢር የተገለጠ ጀግንነት የተሰነደበት ክቡር ማሕደር : ቀስተ ንኅብ።

የሀሁ መጽሐፍት መደብር አድራሻ፦

አድራሻ ቁ. 1 ሜክሲኮ ደብረ ወርቅ ሕንጻ
2 ስታዲየም ናሽናል ታዎር
ስ.ቁ 0911006705
0924408461

3 months, 2 weeks ago

ልዑል ዶ/ር አስፋወሰን አሥራተ ካሣ እንዳተቱት አባቶቻችን የሠራሯት፣ ያበጃጇት፣ የኖሩባትና ታሪካቸውን የጻፉባት የታላቋ ሀገር የኢትዮጵያ ጥንታዊ ማንነትና ምንነት በዚህ ጥልቅ የታሪክ ፍሰት ማሳያ መጽሐፍ ግልጽ ሆኖ ቀርቦልናል። የታሪክ ተመራማሪና ደራሲ ባንተአምላክ አያሌው በተባ ብዕሩ ተሰውሮብን የነበረውን ኢትዮጵያ ለዘመናት ያለፈችበትን ያልተገለጠ እውነት መጋረጃውን ገፎ፣ አቧራዋራውን አራግፎ “የታላቋ ኢትዮጵያ ዝክረ ታሪክ” በሚል ታላቅ ርእስ እንደ ስሙ ታላቅ የሆነ መጽሐፍ እነሆ ለንባብ አብቅቶልናል።
መጽሐፉ በዘመናት ሂደት፣ በሕዝቦች ዑደት የኢትዮጵያ በሮች ሲጠቡና ሲሰፉ፣ ሲላሉና ሲጠብቁ መዛግብቶቿን እየከፋፈተ ያሳያል፤ ከሀገር ውስጥና ከውጪ ድርሳናት እያመሳከረ፤ በየዘመናቱ የሆነውን የዓለመ ሰብእን ክዋኔ እየመረመረ እነሆ ማንነታችሁ ራሳችሁን ተመልከቱ ይለናል። የሀገራችንን የታላቅነቷን ምሥጢሮችም አንድ በአንድ እየዘረዘረ ወደ ቀደመው ታላቅነታችን ይጠራናል። ሃገራችን በሐሰት የትርክት ታሪክ እየተናጠች በምትገኝበትና ትክክለኛው ታሪካዊ እውነታ እየደበዘዘ ባለበት በዚህ ወቅት ነባራዊውን ሃቅ ብሔራዊና ዓለም አቀፋዊ መዛግብትን በመመርመር በማስረጃ አስደግፎ የኢትዮጵያን ጥንታዊና የመካከለኛው ዘመን ታሪክ እንዲህ ገሃድ አውጥቶ የሚያስረዳና ለተመራማሪዎችም ትልቅ ዋቢ በመሆን የሚያገለግል ይህን የመሰለ ድርጁ የምርምር መጽሐፍ ማግኘት ትልቅ ገጸ በረከት ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባው ነው።
ዋና አከፋፋይ፦ ሀሁ መጻሕፍት መደብር
አድራሻ፦ቁ.1 ሜክሲኮ ደብረ ወርቅ ህንፃ.
ቁ.2 አ.አ ስታድየም ናሽናል ታዎር
ስ.ቁ.2519 11 00 67 05

10 months, 3 weeks ago
ሀሁ መጻሕፍት /Hahu books
10 months, 3 weeks ago

የዓለማየሁ ገላጋይ አዲስ መፅሐፍ በታላቅ ቅናሽ ሽያጭ ላይ ነኝ ።
ሀሁ መጻሕፍት
አድራሻ ፦ ቁ.1 አ.አ ስታዲየም ናሽናል ታወር
ቁ.2 ሜክሲኮ ደብረ ወርቅ ህንፃ
ስ.ቁ.0911006705

11 months, 3 weeks ago
ሀሁ መጻሕፍት /Hahu books
11 months, 3 weeks ago

ገበያ ላይ ጠፍተው የነበሩ መጽሐፍት ወደ መደብራችን ጎራ ብለዋል።

ሀሁ መጽሐፍት መደብር

አድራሻ ቁ. 1 ስታድየም ናሽናል ታወር ግራውንድ ፍሎር
2 ሜክሲኮ ደብረ ወርቅ ሕንጻ

ስ.ቁ 0911006705

1 year ago
ሀሁ መጻሕፍት /Hahu books
1 year ago

ይህ ወቅት ድንቅ ነው። የተማከሩ ይመስል በርካታ ጸሐፊያንና ሊቃውንት የመጻሕፍት አበርክቶአቸውን በተመሳሳይ ጊዜ የዘከሩበት ነው። በእርግጥ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በቤተክርስቲያናችን የንባብም የመፃፍም ልማድ የተነቃቃበት ጊዜ ነው ማለት ይቻላል። ይህ መነቃቃት ግን የቅርቡን መቶዎች ዓመታትን የጽሕፈትና፣ የምዕመናንን የንባብ ባሕል ያነጻጸረ እንደሆነ ግንዛቤ ውስጥ አስገብቶ መረዳት ያስፈልጋል። ይህ መነቃቃት በወግ ከተያዘና በአገባብ ከተመራ ፍሬው የሚንዠረገግበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም።

እኔም በአቅሜ ወቅታዊ መስሎ በተሰማኝ አንድ ርዕስ ላይ ጥቂት ነገር ለመጫር መረጃዎች ሰብስቤ፣ አቀናጅቼና አብረው ሊቀርቡ የሚችሉ ሌሎች ጽሑፎችን አጠናቅሬ አፈፃፀሙ ላይ ሳተኩር የተለያዩ የመጻሕፍት ጅረቶች ከልዩ ልዩ አፍላጋት በዙሪያዬ ይጎርፉ ጀመር። የደብተራ በአማን "ተኀሥሦ"፣ የዲያቆን ሄኖክ "የብርሃን እናት"፣ የመጋቤ ብሉይ ወ ሐዲስ አባ ገብረ ኪዳን "መጽሐፈ ምዕዳን" በተለያዩ ኅብረ ቀለማት ሚዲያውን ሲያጥለቀልቁት ከመደነቅ በተሻገረ ጉጉት እየተናጥሁ ተመለከትሁ።

ጉጉቴ ይዘታቸውን ምንጫቸው እንደሚወስነው ስለተረዳሁ ይመስለኛል። ጥቂት ቀደም ብለው ለንባብ የበቁት እንደ "የልቡና ችሎት"፣ "ሳብራ"፣ "ኦርቶዶክሳዊ አዕምሮ"፣ "መንገደ ብርሃን" "ሚተራሊዮን" ... መጣሁ መጣሁ የሚሉት የመምሕር ፋንታሁን ዋቄ "ኦርቶዶክሳዊነትና የሠይጣን መንግሥት" እና "ሥዝም ሰብአዊነት" የኢዮብ ቱሉ "ንጥቂያ" ... መካከል አንድ አነስ ያለች ሥራ ይዤ መቀላቀሌ መሰለኝ። ነገሩን ያየሁት ለአንድ ታላቅ በዓል ዝግጅት ከአንድ ታላቅ ገበያ ዶሮ ገዝቼ የበግ ጠቦትና የፍየል ሙክት፣ ወይፈንና ሰንጋ ከሚነዱ ሰዎች መካከል ኩስ ኩስ እያልኩ እንደሆነ ነው። ያም ሆኖ ከንባብ የሚያጎድል የለምና ምንም ታናሽ ብትሆን ይህችን መጽሐፍ ለአንባቢያን አበርክቻለሁ።

በመጽሐፏ ውስጥ የታሪክ ምሑራንን ያህል ጥልቅ ባይሆንም በአንድ ታሪካዊ ሙግት ላይ መከራከሪያዬን አቅርቤያለሁ። ጥቂት ስብከታዊ ጽሑፎችና ምልከታዎችም ተካተዋል። የእቅበተ እምነት ጽሑፎችም አሉበት። ለማዋዛት ያህል ውስን ገጠመኞቼንም የመጽሐፌ አካል አድርጌያቸዋለሁ። ይህች "ጩጬ" መጽሐፍ በማንኩሳ ማተሚያ ቤት ስትዋብና ስትኳል ከርማ በነገው ዕለት ወደ ብርሃን ትወጣለች። ከነገ በስቲያም ጀምሮ በዋና አከፋፋዩ ሀሁ መጻሕፍት ቤት አማካኝነት ወደየመጻሕፍቱ መደብርና ወደ አንባቢዎቿ እጅ ትደርሳለች።

መጽሐፏ ውስጥ በተጠቀሰ አድራሻ አስተያየታችሁን እንደምታኖሩ ተሥፋ አደርጋለሁ። እርማት፣ ምክር፣ ትችት፣ ተግሳፅና ነቀፋ.. ሁሉንም ዓይነት አስተያየት እቀበላለሁ። የልብና የአንደበት ቅድስናችሁን እንዳያጎድፍ እሠጋለሁ እንጂ የፈለገ ሰው ሊሰድበኝና ሊረግመኝም ይችላል። ሁሉን በአኮቴት እቀበላለሁ። የትኛውም አስተያየት አንዳች ነገር ያመላክተኛል። ጌታ ቢፈቅድ በቀጣይ ለሚኖረኝ ዳጎስና ጠብሰቅ ላለ ሥራዬ ከአቀራረብ እስከ ይዘት ሁለንተናዊ ግብዐት ይሆነኛልና ስለ ሁሉም አመስጋኝ ነኝ።

ክብረት ይስጥልኝ...!
© ማርያማዊት ገብረ መድን
ዋና አከፋፋይ ሀሁ መጻሕፍት
አድራሻ፦ ቁ.1 አ.አ ስታድየም ናሽናል ታዎር
ቁ.2 ሜክሲኮ ደብረ ወርቅ ህንፃ
ስ.ቁ. 0911006705

1 year ago
ሀሁ መጻሕፍት /Hahu books

We recommend to visit

Books only!

This channel is created for books sharing To widen your mind and to get books easily We have more than 2000 amharic and english books !

Join and share @Books_worldd

አስተያየት @BooksWorlddd_bot !

@books_worlddd መወያያ ግሩፕ

#share

📚📖 🌟✨እንኳን በደህና መጡ✨🌟📖 📚

➥ እዚህ ቻናል ላይ የተለያዩ የ አማርኛ እና English መፅሀፍትን በ 📙 Pdf እና ትረካዎችን እና ሌሎችም ጠቃሚ ነገሮችን ያገኛሉ።

📖 ማንበብ ሙሉ ሰው ያደርጋል‼️

መልካም ቆይታ ከ @Ethio_Books ጋር ✌

ለማንኛውም ሀሳብ አስተያየት በ 👉 @Ethio_booksbot ላይ ያድርሱን እናመሰግናለን።

Last updated 11 months ago

Ethiopian Books, Files and Historical Documents.

Use @etbookstorebot to send us any comments or documents.