Dive into the Ultimate Free Library: Your One-Stop Hub for Entertainment!

Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

Description
كناشة ابن منور
Advertising
We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።

ያግኙን +251913134524

Last updated 2 months ago

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @MKHI7

Last updated 2 months ago

BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot

Last updated 1 month, 1 week ago

1 month, 2 weeks ago
ንቃ!

ንቃ!
~
የጠላት አጀንዳ አስፈፃሚ የውስጥ ባንዳ ክፋት ያምሃል? እንግዲያው ይህንን ቀብር አምላኪ አንጃ ስሩን በመንቀል ላይ አጥብቀህ ስራ!
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor

1 month, 3 weeks ago

የሸዋል ስድስት ቀናትን ፆም የሚመለከቱ ነጥቦች
~
1. ከሸዋል ስድስት ቀናትን መፆም ፋይዳው ምንድነው?
መልስ፦ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
مَنْ صَامَ رَمَضَانَ ثُمَّ أَتْبَعَهُ سِتًّا مِنْ شَوَّالٍ كَانَ كَصِيَامِ الدَّهْرِ
“ረመዷንን ፁሞ ከዚያም ከሸዋል ስድስት ያስከተለው አመት እንደመፆም ነው።” [ሙስሊም፡ 1164]
ስለዚህ ስድስት ቀናትን በሸዋል ወር ውስጥ መፆም አጅሩ ከረመዷን ወር ፆም ጋር የሚቆራኝ ነው ማለት ነው።

  1. ከሸዋል ስድስት ቀናትን መፆም የሚጠቁመው ሐዲሥ ሰነዱ አስተማማኝ ነውን?
    መልስ፦ ሐዲሡ ሚዛን በሚደፋ አቋም ለማስረጃነት በቂ ነው። ዝርዝር የፈለገ ይህንን ሊንክ ተከትሎ ይመልከት፦ https://tinyurl.com/mucfx3ny

  2. ከሸዋል ውጭ ባሉ ወራት ውስጥ ስድስት ቀናት ቢፆም የሸዋልን ፆም ይተካልን?
    መልስ፦ ማስረጃ የመጣው ሸዋልን በተመለከተ ብቻ ነው። ከዚህ ውጭ ለማለት የሚያስችል መረጃ የለም።

  3. አከታትሎ ነው ወይስ አፈራርቆ ነው የሚፆሙት?
    መልስ፦ በሸዋል ወር ውስጥ እስከሆነ ድረስ አከታትሎም ይሁን አፈራርቆ፣ ቀጥታ ከዒድ በኋላም ይሁን አዘግይቶ በፈለገው መልኩ መፆም ይችላል።

  4. ፆሙን ከሸዋል አንድ መጀመር ይቻላል?
    መልስ፦ ሸዋል አንድ ዒድ ነው። በዒድ ቀን መፆም ደግሞ አይፈቀድም።

  5. ቀዷእ ያለበት ሰው ሸዋልን መፆም ይችላል?
    መልስ፦ ከፊል ዓሊሞች አይቻልም ይላሉ። የአብዛኞቹ ዓሊሞች አቋም ግን ይቻላል የሚል ነው። ጠንካራውም አቋም ይሄ ነው። ይህንን ከሚጠቁሙ መረጃዎች ውስጥ፦

[ማስረጃ አንድ]፦

እናታችን ዓኢሻህ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዲህ ብላለች፦
كانَ يَكونُ عَلَيَّ الصَّوْمُ مِن رَمَضَانَ ، فَما أسْتَطِيعُ أنْ أقْضِيَ إلَّا في شَعْبَانَ
ከረመዷን (ያልፆምኩት) ፆም ይኖርብኝ ነበር። በሸዕባን እንጂ ቀዷኡን ማውጣት አልችልም ነበር።” [ቡኻሪ፡ 1149] [ሙስሊም፡ 1849]
ልብ በሉ! ሸዕባን በኢስላማዊው አቆጣጠር ከረመዷን በፊት ያለው ወር ነው። የረመዷንን ቀዷእ ሳታወጣ ቀጣዩ ረመዷን ሲቃረብ ነበር የምትፆመው። በዚህ መሃል ላይ ትልልቅ አጅር ያላቸው የዐረፋ ፆም፣ የዐሹራእ ፆም፣... አሉ። ዓኢሻ ይህን ሁሉ አትፆምም ነበር፣ ከአመት እስካመት ሱና ፆም አትፆምም ነበር ብሎ ማሰብ ይከብዳል።
“አይ ለሳቸው ስትል ነበርኮ የረመዷንን ቀዷእ የምታዘገየው” ከተባለ “አዎ። ነብያችን ﷺ ሸዕባንን አብዛኛውን ይፆሙት ስለነበር ሸዕባን ላይ ቀዷእ ለማውጣት ሰፊ ጊዜ ይኖራታል። ግና እሳቸውኮ
ዐረፋና ዐሹራእ ይፆሙ ነበር።
በሌሎችም ወራት “አያፈጥሩም እስከምንል ድረስ ይፆሙ ነበር” ብላለች ዓኢሻ። [ቡኻሪ፡ 1969]
ከየወሩ ሶስት ቀን ይፆሙ ነበር። [አቡ ዳውድ፡ 507]
በየ ሳምንቱም ሰኞና ሐሙስም ይፆሙ ነበር። [ቲርሚዚይ፡ 745]
በተጨማሪም “ከረመዷን ቀጥሎ በላጩ ፆም የሙሐረም ወር ፆም ነው”ብለዋል። [1163]
በየወሩ “አያመል ቢድ” ማለትም 13ኛ፣ 14ኛ እና 15ኛ ቀናትን መፆምንም አዘዋል። [ነሳኢ፡ 7/222] [ቲርሚዚይ፡ 761]
ይህ ሁሉ ከመሆኑ ጋር የረመዷንን ቀዷእ እስከ ሸዕባን ድረስ የምታዘገይበት አንዱ ምክንያት ቀጣይ ረመዷን እስካልገባ ድረስ ማዘግየት ስለሚቻል ነው። እንጂ በዚህ ሁሉ መሃልም መፆም ትችል ነበር።

[ማስረጃ ሁለት]፦

የረመዷንን ቀዷእ ወሩ እንዳለቀ ወዲያውኑ አከታትሎ መፆም ግዴታ አይደለም። ይሄ የብዙሃን ዑለማእ አቋም ነው። ቀጣይ ረመዷን እስካልገባ ድረስ ማዘግየት ይቻላል። ወዲያውና አከታትሎ መፈፀም ግዴታ ካልሆነ ደግሞ መሃል ግዴታ ያልሆኑ ፆሞችን መፈፀም የተከለከለ አይሆንም። ይህ እንግዲህ ቀዷእ ላለበት ሰው በላጩ አፈፃፀም ቀድሞ ቀዷኡን መፆም፣ ከዚያም የሸዋልን ስድስት ማስከተል ከመሆኑ ጋር ነው።
ነገር ግን በወር አበባ ወይም በሌላ ምክንያት በርከት ያለ ቀዷእ ያለ ከሆነ ሸዋልን ለመፆም በቂ ጊዜ ላይኖር ይችላል። ወይም የፆሙ ጊዜ በመደራረቡ ሊከብድ ይችላል። በዚህና መሰል ሁኔታ ላይ ላለ አካል ሸዋልን የመፆም አጅር እንዳያልፈው ቢያስቀድምና ቀዷኡን አረፍ ብሎ ቆይቶ ቢፆም የሚከለክለው ግልፅ ማስረጃ የለም።

ብዥታዎች፦
-
የግዴታ ፆምን ቀዷእ ሳይፆሙ ሱና ፆም መፆም አይቻልም የሚሉ ዓሊሞች እንዳሉ ገልጫለሁ። ከሚጠቅሷቸው ማስረጃዎች ውስጥ፦

[አንዱ]

መግቢያዬ ላይ የጠቀስኩትን “ረመዷንን ፁሞ ከዚያም ከሸዋል ስድስት ያስከተለው አመት እንደመፆም ነው” የሚለውን ሐዲሥ ነው። ማስረጃ የሚያደርጉበት አግባብ የተጠቀሰው አጅር ሙሉ ረመዷንን ፁሞ ከዚያም ከሸዋል ስድስት ያስከተለን ነው የሚል ነው።
ይሄ ግን አብዛኛው ሙስሊም ረመዷንን ሙሉውን ስለሚፆም በዚህ መልኩ ተገለፀ እንጂ በተጨባጭ ሸሪዐዊ ምክንያት ሙሉውን ያልፆመ ሰው ከተጠቀሰው አጅር ውጭ ይሆናል ማለት አይደለም። ለምሳሌ ያክል ነብያችን ﷺ “ረመዷንን አምኖና አጅሩን አስቦ የፆመ ሰው ያለፈው ወንጀሉ ይማርለታል” ብለዋል። ይህ ማለት ግን በወር አበባ ምክንያት ሙሉውን ያልፆመች ሴት ይህንን አጅር አታገኝም ማለት አይደለም።

[ሁለተኛ] ማስረጃ የሚያደርጉት ተከታዩን ሐዲሥ ነው፦
من أدركَ رمضانَ وعليهِ من رمضانَ شيءٌ لم يقضهِ، لم يتقبَّل منهُ ومن صامَ تطوُّعًا وعليهِ من رمضانَ شيءٌ لم يقضهِ، فإنَّهُ لا يتقبَّلُ منهُ حتَّى يصومَهُ
“በሱ ላይ ቀዷእ ያላወጣው የረመዷን ፆም እያለበት ረመዷን የደረሰበት ሰው አላህ አይቀበለውም። በሱ ላይ ቀዷእ ያላወጣው የረመዷን ፆም እያለበት ግዴታ ያልሆነ ፆም የፆመ ሰው ቀዷኡን እስከሚፆም ድረስ ተቀባይነት አይቀበለውም።” [ሙስነድ አሕመድ፡ 8606]

መልስ፦ ዶዒፍ ነው። [አልዒለል፣ ኢብኑ አቢ ሓቲም፡ 768]

[ሶስተኛ] የሚጠቀሰው እንዲህ የሚል ነው፦
አንድ ሰው፡ “የረመዷን ቀዷእ አለብኝ። ከመሆኑም ጋር አስሩን ትርፍ ፆም ልፆም ፈልጌ ነበር” ሲል አቡ ሁረይራህ ረዲየላሁ ዐንሁ፡ “አይሆንም። ይልቁንም በአላህ ሐቅ ጀምር፣ እሱን ቀዷእ አውጣ። ከዚያ በኋላ የፈለግከውን ትርፍ ፆም ፁም” አሉ። [ሙሶነፍ ዐብዲረዛቅ፡ 7715]

መልስ፦ ግንዛቤው ላይ የተለያዩ ሃሳቦች ከመሰንዘራቸው ጋር ቀጥታውን ስንወስድ ከዓኢሻ ሐዲሥ ጋር የሚቃረን ነው። የዓኢሻ ሐዲሥ ደግሞ የነብዩ ﷺ ኢቅራር (ማፅደቅ) ያለበት ስለሆነ ቅድሚያ ይሰጠዋል።

ስለዚህ የረመዳን ፆም ቀዷ ያለበት ሰው
① ለቀዷው ሰፊ ጊዜ ስላለና
② የሸዋል ጊዜ አጭር ስለሆነ ሸዋልን አስቀድሞ መፆም ይችላል።

  • ይህንን ነጥብ ዘለግ አድርጌ መዳሰስ የፈልግኩት ሸዋል ቢያልፍም እንኳ ቀዳኡን ሳይፆሙ የሸዋልን ስድስት ቀናት መፆም አይቻልም የሚሉ ዑለማዎችን ፈትዋ ነጥለው ትኩረት የሚሰጡ ስላሉ ነው። ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት መፆም ይቻላል የሚለው አቋም የብዙሃን ዑለማእ ምርጫ ነው። በሸይኽ ሙቅቢል ፈትዋ ፅሁፌን ላሳርግ:-
1 month, 3 weeks ago

የዒድ ሶላት እንዳያልፈን!

3 months, 2 weeks ago

""ሙሓደራ ክፍል 190 ""

አዲስ ሙሓደራ ክፍል 02

ረድ በ ወሰን ተላላፊዎች ላይ

የ ሚዳሰሱ ነጥቦች ለ አብነት 👇

““የ አቡዘር (አቡ ጦልሓ) ስህተቶች እና ግጭጭቶች…““
🎤 በ ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ከሚሴ (አቡ ሐቲም)

https://t.me/UstazKedirAhmed

3 months, 3 weeks ago

ጥንቃቄ
~
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ብዙ ወጣት ሴቶች በሚዝናኑባቸው ቦታዎች ትላልቅ ከተማዎች ላይ GHB የሚባል ኬሚካል ተበራክቷል። "ጋባዦች" አንድ መጠጥ ውስጥ የGHB ጠብታ ሲጨምሩበት ተጠቂዎች (አብዛኛውን ጊዜ ሴቶች) በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ያሉበት፣ አብረዋቸው የነበሩበትን እና የተወሰዱበትን ቦታ አያስታውሱም። ገንዘብ ተከፍሏቸው የደነዘዙ ሴቶችን ለማስደፈር የሚያቀርቡ ውጣት ወንዶችም ሴቶችም ይሄንን እየሰሩ የሚኖሩ ብዙዎች ናቸው። በተለይ "የቤት ልጅ" አይነት የሚባሉ (ተማሪዎች) እና ሌሎች ወጣት ሴቶች የዚህ ወንጀል ተጠቂ እየሆኑ ነው። GHB ከሰውነታቸው ወጥቶ ሲነቁ በማይታወቅ ቦታ ብዙ ጉዳት ደርሶባቸው ራሳቸውን ያገኛሉ። ምን እንደተፈጠረ አያውቁም። GHB የሰው ሕይወት ሊያጠፋ ይችላል። በከተሞች መዝናናት እና መገባበዝ ደግሞ የተለመደ ስለሆነ ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል። እንዲህ አይነት ወንጀሎች በቅርብ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ውጪ ከኖሩ ኢትዮጵያውያን ነው።

ኮፒ
"ሼር" ቢደረግ ለወገን ይጠቅማል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor

3 months, 3 weeks ago

አንድ ነጥብ
~
የትግራይ ህዝብ በጦርነቱ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰበት የሚታወቅ ነው። ሰሞኑን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳይ ሰዎች ከ67 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው እርዳታ ማድረጋቸው ጥሩ የድጋፍ ስራ መሆኑን አውስቼ "አላህ ጀዛቸውን ይክፈላቸው" ብል ይሄ ስሜት ያሰከረው መንጋ ሲንጫጫ ነበር። ከዚህ በፊት የመስጂድ ቦታ ለሰጡን አካላት ምስጋና ስገልፅ ምንም ያላሉት እነዚያ ሙስሊሞች ስላልሆኑ ነው። አንዳንድ ሰዎች ዘንድ "እናመሰግናለን፣ አላህ ይስጥልን" ማለት ለሙስሊሞች ሲሆን የቢድዐን አካል ማወደስ፣ የመንሀጅ መንሸራተት ሲሆን ለካፊሮች ሲሆን ግን ችግር የለውም። እንዲያውም እንደ ንቃት ነው የሚቆጠረው። ነገሮች እንዴት እየተያዙ እንደሆነ ቆም ብለን እናስተውል።
በተረፈ የመጅሊስ ሰዎች አካሄድ እንከን የለሽ ነው የሚል አቋም የለኝም። ባደባባይ ከሚታዩ ችግሮቻቸው ውስጥ በአንድ ሁለቱ ላይ ከዚህ ቀደም በግልፅ ፅፌያለሁ።
ለማንኛውም አንድ አካል ችግር ቢኖርበት እንኳ በመልካም ስራው ላይ "ጀዛሁላሁ ኸይራ" ማለት አቧራ የሚያስነሳ አይደለም።
1- ኢብኑ ባዝ - ረሒመሁላህ - ከሙሐመድ አልገዛሊ "መዐ'ላህ" ኪታብ በረጅሙ ከወሰዱ በኋላ መጨረሻ ላይ "ጀዛሁላሁ ኸይራ" ይላሉ። [ነቅዱል ቀውሚየቲል ዐረቢያ] [መጅሙዑ ፈታዋ፡1/317]
2- ሸይኹል አልባኒይም - ረሒመሁላህ - አሕመድ ዲዳትን ትልቅ ጂሃድ ላይ እንዳሉ በመግለፅ "ጀዛሁላሁ ኸይራ" ይላሉ። [ሲልሲለቱል ሁዳ ወኑር]
3- ሸይኽ ሙሐመድ ዐሊ ኣደምም እንዲሁ ከዩሱፍ አልቀርዳዊ "ፊቅሁ ዘካ" ኪታቡ ረዘም ያለ ክፍል ከወሰዱ በኋላ "ጀዛሁላሁ ኸይራ" ይላሉ። [ዘኺራ፡ 22/168] አለፍ ብለውም እንዲህ ሲሉ ስራውን ከማድነቅ ጋር ዱዓእ ያደርጋሉ:- انتهى ما كتبه الدكتور القرضاويّ شكر اللَّه سعيه، وهو بحثٌ نفيسٌ جدًا.
የቀርዷዊ ማንነት የሚታወቅ ነው።
አሁንም ሸይኹል አልባኒይ ለሙሐመድ አልገዛሊይ እና ዩሱፍ አልቀርዷዊይ አድናቆታቸውን ከገለፁ በኋላ ለቀርዷዊ "አላህ ይጠብቀው። ሙስሊሞችንም ይጥቀምበት" ብለዋል። [ጋየቱል መራም፡ 7]
አልባኒይ የነዚህን አካላት ብልሹ አካሄድ በመተቸት የታወቁ ናቸው። ከመሆኑም ጋር "በመልካም ስራቸው" ላይ አላህ እንዲመነዳቸው ዱዓእ ሲያደርጉ እናያለን። መሰል አካሄድ ብንፈልግ ሌሎችም ጋር እናገኛለን። "ሙብተዲዕን ማድነቅ ይቻላል" እያልኩ አይደለም። ይልቁንም ነገሮችን መለየትና በልክ መያዝ እንልመድ እያልኩ ነው።
ያያያዝኩት በሕሩ ተካ በጉራጌ ዞን ጉንችሬ ላይ የነበረን ሁከት ተከትሎ የነበረውን ሂደት አስመልክቶ ርስቱ ይርዳውን፣ የፍትህ ሚኒስቴርን፣ አስተዋይና ሚዛናዊ ብሎ የገለፃቸውን ክርስቲያኖችን፣ የጉንችሬና የእነሞር አመራሮችን ያደነቀበትና ያመሰገነበት ነው። ለሽፋን ከሚቀርቡ ሰሞንኛ ግርግር ውጭ እነዚህ የተጠቀሱት አካላት ለአካባቢው ችግር ወይ ጠንሳሽ ናቸው። ወይ አፍራሽ ሚና የነበራቸው ናቸው። ወይ ደግሞ ኃላፊነታቸውን ባለመወጣት ችግሩ እንዲቀጥል ያደረጉ ናቸው።
(የተነሳውን ነጥብ ጥለው በማስቀየስ ላይ እንደሚጠመዱ እጠብቃለሁ።)
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor

7 months, 1 week ago

ደርስ
~
መንሀጁ ሳሊኪን
ክፍል:- 0️⃣0️⃣7️⃣
* የደርሹ መነሻ፦ والفرض من هذا
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor

7 months, 2 weeks ago

ደርስ
~
ሪያዱ ሷሊሒን
ክፍል:- 9️⃣9️⃣
የለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 251፣ باب فضل الغني الشاكر
የኪታቡን ሶፍት ኮፒ በዚህ ማግኘት ትችላላችሁ
https://t.me/IbnuMunewor/3505
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor

7 months, 2 weeks ago

ከደቂቃዎች በኋላ በዚሁ ቻናል የሪያዱ ሷሊሒን ደርስ ይኖራል፤ ኢንሻአላህ።

8 months, 3 weeks ago

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته

📜መውሊድን በተመለከተ በኡስታዝ ኢብኑ ሙነውር የተዘጋጁ ከፊል ፅሁፎችን በቀላሉ እንዚህን ሊንኮች በመጫን ማንበብ ትችላላችሁ።

1, ነብዩ ﷺ መቼ ተወለዱ?
https://t.me/IbnuMunewor/893

2, መውሊድን ማን ጀመረው? በመረጃ ለሚያምኑ ብቻ
https://t.me/IbnuMunewor/869

3, መውሊድ ለምን አላማ እንደተጀመረ ያውቃሉ?
https://t.me/IbnuMunewor/876

4, መውሊድና ነባሩ እስልምና አይተዋወቁም! {ምስክር እራሳቸው!}
https://t.me/IbnuMunewor/884

5, “በአላህ እዝነት ይደሰቱ...” - ትልቁ የመውሊድ አጋፋሪዎች ምርኩዝ
https://t.me/IbnuMunewor/2227

6, የሰኞ ፆም እና መውሊድ
https://t.me/IbnuMunewor/2214

7, ዐቂቃ ሌላ መውሊድ ሌላ!
https://t.me/IbnuMunewor/2261

8, ዓሹራን ለመውሊድ?
https://t.me/IbnuMunewor/2269

9, መውሊድ ውስጥ እነዚህ አደጋዎች አሉ!
https://t.me/IbnuMunewor/2294

10, በመውሊድ ላይ ስለሚፈፀመው ጭፈራ ዑለማዎች ምን እንዳሉ ታውቃለህ?
https://t.me/IbnuMunewor/882

11, መውሊድን የሚፈቅዱትም አይፈቅዱትም!
https://t.me/IbnuMunewor/2298

12, መውሊድ የማያከብር ሰው የሙሐመድ ﷺ ጠላት ከሆነ፣ ገና የማያከብር ሰው የዒሳ ጠላት ነው!
https://t.me/IbnuMunewor/886

13, እውን የሡወይባ ታሪክ ለመውሊድ ማስረጃ ይሆናል?
https://t.me/IbnuMunewor/2234

14, ሸውካኒ እና መውሊድ (ወሳኝ ነጥቦች የተዳሰሱበት)
https://t.me/IbnuMunewor/898

15, ሲዩጢ፣ የመውሊድ ደጋፊዎች ሌላኛው ምርኩዝ
https://t.me/IbnuMunewor/2277

16, እውን ኢብኑ ተይሚያ መውሊድን ፈቅደዋል?
https://t.me/IbnuMunewor/878

17, በሸይኹል አልባኒ እና “መውሊድ ይፈቀዳል” በሚል ሰው መካከል የተደረገ ድንቅ ቃለ-ምልልስ
https://t.me/IbnuMunewor/34

18, ከ“ወሃብዮች” በፊት የነበሩ የመውሊድ ተቃዋሚዎች
https://t.me/IbnuMunewor/1624

19, መውሊድ ተከሽኖ
https://t.me/IbnuMunewor/2309

20, ለምንድን ነው የመውሊድ ተቃውሞ ኢኽዋኖችን ምቾት የሚነሳቸው?
https://t.me/IbnuMunewor/918

21, መሷሊሐል ሙርሰላ፣ የመውሊድ አክባሪዎች የመጨረሻው ምሽግ
https://t.me/IbnuMunewor/2302

We recommend to visit

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ ነው። ሰውነትን አስቀድመው ግለሰብን፣ ህዝብና ሀገርን የሚያከብሩ፣ ሚዛናዊ አመለካከትን ያዳበሩ፣ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን ቤት ነው።

ያግኙን +251913134524

Last updated 2 months ago

ስለ መድፈኞቹ የሚወጡ መረጃዎች ለማግኘት የትም መሄድ አያስፈልግም

- የዝዉዉር ዜና
- የአሰልጣኞች አስተያየት
- የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
- ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት

ለማስታወቂያ ስራ  --> @MKHI7

Last updated 2 months ago

BoA Social media links
@ https://www.facebook.com/BoAeth
@ https://www.instagram.com/abyssinia_bank
@ https://www.linkedin.com/company/bankofabyssinia/
@ https://twitter.com/abyssiniabank
@BOA_ATM_bot

Last updated 1 month, 1 week ago