Unlock a World of Free Content: Books, Music, Videos & More Await!

⚜የጥንት ኢትዮጵያውያን ድንቅ ምርምሮች💎

Description
_______________________
The Ethiopians were the first who invented the science of stars and gave name to the planets.
አንጋፋው የታሪክ ተመራማሪ ሉስያን
🟢ለአስተያዬት
@RAFATOALBOT

promotion Makers
@DINK_MIRMIROCH_BOT
_______________________
Advertising
We recommend to visit

https://www.hulepay.com/

Last updated 1 week, 3 days ago

🍿የ VIP ቻናላችንን በአነስተኛ ክፍያ በመቀላቀል ሁሉንም ፊልሞችን ማግኘት ትችላላቹ።
🍿 CHANNEL ~> @Wase_Records
🍿 BOT ~> @Wase_Records_Bot
🍿 OWNER ~> @The_hacker_person
🍿 VIP ~> @The_hacker_person

Last updated 3 days, 8 hours ago

አፍሪወርክ ቢዝነሶች እና የግል ቀጣሪዎች ለስራቸው ከሚፈልግዋቸው ፍሪላንሰሮች ፣ ቋሚ ሰራተኞች እንዲሁም የትርፍ ጊዜ ሰራተኞች ጋር በቀጥታ የሚገናኙበት ፕላትፎርም ነው።

አሰሪዎች ስራ ለመልቀቅ @freelanceethbot ይጠቀሙ

Afriwork in English @freelance_ethio

Last updated 1 month, 3 weeks ago

2 months ago

ሰባተኛው ፊደል<<ቶ>>

ይህ ሆሄ በቀመር ሲቆጠር አስረኛ ነው።
"ቶ" በመልካ ፊደሉ ሰው መሳይ ነው። ባለ ስድስት መቶ ገቢር ፈዋሽ ዕፅም"ዕፀ ልባዊትም" ቅርጿ <<ቶ>> መሳይ ናት።
'ቶ' ቃል ሥጋ ሆነ የሚለውን ምስጢር ይዟል።

"ቃል" የሚለው ፊደል በቀመር ሲተነተን
ቀ= 8 ነው።
ለ=2 ነው።
ድምር=10 ይሆናል።
10 ደግሞ የ "ቶ" ፊደል መነሻ የ'ተ' ቀመር ነው።
'ቶ' በፈጣሪ መንፈስ ነፀብራቅነት ለሙሴ ተሰጥታ ባህርን የከፈለች ዘንግ ናት።
ይህ ለመግቢያ የተፃፈ የ'ቶ' ፊደል ትርጉም ነው። ሙሉ ታሪኩን እናንተ አንብቡት።
ዋና ምንጭ፦የወርቅ ዘንግ መፅሐፍ በመስፍን ሰሎሞን  MESFIN SELOMON(የስነ_ፊደል_ተመራማሪ)

"የጥንት ኢትዮጵያውያን ድንቅ ምርምሮች"
"የጥንት ኢትዮጵያውያን ድንቅ ምርምሮች"

10 months, 3 weeks ago

የፍልስፍናው ንጉስ ዘርዓያዕቆብ

ዘርዓያዕቆብ የተወለደው በ (1592 ) ዓ.ም ከአንድ የአክሱም ድሃ ገበሬ ሲሆን የትውልድ ሐረጉ የሚመዘዘው ግን ከአክሱም ካህናት ወገን ነው፡፡ “ዘርዓያቆብ" የሚለው መጠሪያ የክርስትና ስሙ ሲሆን ቤተሰቦቹ ያወጡለት ስም ግን ወርቄ ነው፡፡ የዘርዓያዕቆብ ፍልስፍናዊ አኗኗር የሀገራችን ሰዎች ለፍልስፍና ካላቸው አሉታዊ አመለካከት በተቃራኒ ነው፡፡ የሀገራችን ሰዎች ፍልስፍና ሰዎችን ከሀዲ የሚያደርግ እራሳቸውን እንዲጥሉ ፀጉራቸውን እንዲያንጨባርሩ ለአለባበሳቸው ግዴለሽ እንዲሆኑ ከሰው ጋር እንዳይገጥሙ ማህበራዊ ህይወት እንዳይኖራቸው የሚያደርግ  ገፋ ሲልም የሚያሳብድ ትምህርት ነው ብለው ያስባሉ፡፡ ይሄንን አመለካከት ፉርሽ የሚያደርግ የመጀመሪያው ሰው ዘርዓያዕቆብ ነው፡፡

ዘርዓያዕቆብ በዓለማዊ ህይወቱ በጣም ሀብታም  በመንፈሳዊ ህይወቱ በጣም የሚተጋ በማህበራዊ ህይወቱም ሚስት አግብቶ ልጆችና የልጅ ልጆች ያየ ሰው ነው፡፡ የሰው ልጅ ህይወቱን በብልፅግና በደስታ በምስጋና ና በጠንካራ ማህበራዊ ህይወት ውስጥ መኖር አለበት ብሎ ያስባል ይሄንንም በተግባር በህይወቱ አሳይቶናል፡፡ ዘርዓያዕቆብ ረጅም ዕድሜ (93 ዓመት) መኖር የቻለውም ከዚህ ፍልስፍናዊ አመለካከቱ የተነሳ ነው፡፡

7ቱ የዘርዓያዕቆብ የፍልስፍና አምዶች :-
የዘርዓያዕቆብ ፍልስፍና በ7 መሰረታዊ ሃሳቦች ላይ የቆመ ነው፡፡

  1. እግዚአብሔር ሰውን አይልክም

  2. እግዚአብሔር የሚገለፀው በተፈጥሮ ህግና ስርዓት ውስጥ ብቻ ነው ይሄም የተፈጥሮ ህግና ስርዓት ብቸኛው እውነት ነው፡፡

የመጀመሪያ አምድ ብቻውን በ23 ገፆች ተተንትኗል፡፡ ይህ የፍልስፍና አምድ የዘርዓያዕቆብ ሜታፊዚክስ የቆመበት ዋነኛው መሰረት ነው፡፡ እግዚአብሔር ሰውን የማይልክ ከሆነ በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ያለው በካህናቱ የተሰራው ድልድይ ይሰበራል፡፡ ዘርዓያዕቆብ ይሄንን ድልድይ ከሰበረ በኋላ ሌላ ድልድይ ለመስራት መከራውን ያያል፡፡ ይህ አዲስ ድልድይ የመስራት ጥረት ነው የዘርዓያዕቆብ ሜታፊዚክስ ና ኢቲክስ፡፡ በጣም አስገራሚ የሚያደርገው ደግሞ የ19ኛው ክ/ዘ የጀርመን ፈላስፎች የሆኑት ሼሊንግና ሔግልም የዘርዓያዕቆብ ዓይነት የሜታፊዚክስ ፕሮጀክት ነበራቸው፡፡

  1. ይሄንን የተፈጥሮ ህግና ስርዓት (ብቸኛ እውነት) በመረዳት ስለ እግዚአብሔር ህልውና ባህሪና ፍላጎት የሚነግረን ልቦናችን ነው።

  2. ልቦና የማይደርስበት ሃይማኖታዊ አስተምህሮ መኖር የለበትም፡፡ በመሆኑም ሁሉም ሃይማኖታዊ አስተምህሮዎች በልቦና የሚፈተሹና የሚረጋገጡ መሆን አለባቸው፡፡ ለዚህም ነው ዘርዓያዕቆብ የመላዕክትንም ሆነ የመናፍስቱን ጉዳይ እንዲሁም 5ቱን ሃይማኖታዊ ሚስጥራትን (ሚስጥረ ሥጋዌ፣ ሚስጥረ ሥላሴ፣ ሚስጥረ ጥምቀት፣ ሚስጥረ ትንሳኤና ሚስጥረ ቁርባን) ለመፈተሽ ርዕሰ ጉዳዩ ያላደረጋቸው፡፡
    ምክንያቱም እነዚህ ነገሮች በልቦና ( በአመክንዮ በ Reason)መፈተሽ የሚችሉ ነገሮችአይደሉም፡፡

5.ሃይማኖታዊ አስተምህሮዎች ልቦናችን ከሚነግረን የተፈጥሮ ህግጋት ጋር መጣላት የለበትም የሚጣላም ከሆነ ስልጣኑ (ትክክለኛው) ሃይማኖት የሚለው ሳይሆን የተፈጥሮ ህግ (ልቦናችን) የሚነግረን ነው፡፡

  1. ልቦና (አዋቂነት Consciousness) ለሰው ልጅ ነፃ ፍቃድን ሰጥቷል፡፡ ስለዚህ የሰው ልጅ ላይ አስቀድሞ የተወሰነ ነገር የለም፡፡

  2. እጅግ የተዋጣለትና ትክክለኛው የአኗኗር ዘዴ ከተፈጥሮ ህግና ስርዓት ጋር መስማማት ነው፡፡ በመሆኑም ባህላችንና ማህበራዊ አደረጃጀቶቻችን (ህጎቻችን) ሁሉ የተፈጥሮን ህግና ስርዓት መሰረት ያደረጉ መሆን አለባቸው፡፡ ዘርዓያዕቆብን የምተነትነው እነዚህን ሰባት የፍልስፍና አምዶቹን እየመነዘርን ነው፡፡

አፄ ዘርዓያዕቆብ፣ አፄ ሱስንዮስና ፈላስፋው ዘርዓያዕቆብ በጣም ብዙ ሰዎች አፄ ዘርዓያዕቆብ እና ፈላስፋው ዘርዓያዕቆብ አንድ ዓይነት ሰዎች ይመስሏቸዋል፡፡ ሆኖም ግን ሁለቱ ሰዎች በመካከላቸው የ200 ዓመት ልዩነት አላቸው፡፡ አፄ ዘርዓያዕቆብ የተወለዱት በ1391 ዓ.ም ሲሆን ፈላስፋው ዘርዓያዕቆብ የተወለደው ደግሞ በ1592 ዓ.ም ነው፡፡ የአፄ ዘርዓያዕቆብ የንግስና ዘመን ከ1426-1460 ዓ.ም ድረስ ነበር፡፡ ሌላው፣ አፄ ዘርዓያዕቆብ እና አፄ ያዕቆብ ሁለት የተለያዩ ንጉሰ ነገስታት እንደሆኑ መታወቅ አለበት፡፡ ፈላስፋው ዘርዓያዕቆብ የተወለደው በአፄ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት ጊዜ ነው፡፡ ፈላስፋው ዘርዓያዕቆብ በአፄ ያዕቆብ ዘመነ መንግስት ጊዜ የተወለደ ቢሆንም በህይወት ዘመኑ ውስጥ ግን በእርስበርስ ጦርነት የተፈራረቁ ሰባት ነገስታትን አይቷል።

ፈላስፋው ዘርዓያዕቆብ የሞተው በ1685 ዓ.ም በአፄ እያሱ 1ኛ ዘመነ መንግስት ወቅት ነው፡፡ ሥልጣን የዕድሜ ልክ ችሮታ በሆነበት ሀገር ከአፄ ያዕቆብ እስከ አፄ እያሱ 1ኛ ድረስ  (ከ1595-1674) ባሉት 79 ዓመታት ውስጥ ሰባት ነገስታት መፈራረቃቸው ፈላስፋው ዘርዓያዕቆብ የኖረበት ዘመን የእርስበርስ ጦርነት ዘመን እንደነበረ ያመላክታል ደግሞም ታሪክም የሚነግረን እንደዚያው ነው፡፡ ሆኖም ግን ፈላስፋው ዘርዓያዕቆብ ስለጦርነት አስከፊነትና እንደዚህ ዓይነት ጦርነቶች እንዲቀሩ የመንግስት አወቃቀር ላይም ሆነ የስልጣን ሽግግር እንዴት መሆን እንዳለበት አስተያየት አልሰጠም፡፡ በሐተታው ምዕራፍ 12 ላይ ብቻ “ነገሥታት ሽንጋዮችንና ግብዞችን ይወዳሉ ” ከማለት እና አፄ ፋሲለደስን በግል ባህሪው ላይ ከመተቸት በስተቀር፡፡ ባጭሩ “መንግስት” የሚለው ፅንሰ ሐሳብ የፍልስፍና ዋነኛ ርዕሰ ጉዳይ ቢሆንም በዘርዓያዕቆብ ፍልስፍና ውስጥ ግን ትኩረት አላገኘም፡፡
ሌላው የዘርዓያዕቆብ ዋነኛ ጥረት በዕውቀት ላይ የተገነባ ማህበረሰብ መፍጠር ነበር፡፡ ዕውቀት ድንቁርናን ብቻ ሳይሆን ድህነትንም ያጠፋል ብሎ ያምናል፡፡ በመሆኑም፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ከድንቁርናና ከድህነት ተላቆ የበለፀገና ስልጡን እንዲሆን የዘርዓያዕቆብ ብቻ ሳይሆን የእሱ ተማሪ የነበረው የወልደ ህይወትም ምኞት ነበር፡፡  ዘርዓያዕቆብ የወጣትነትና የትምህርት ዘመኑን የኖረው በአፄ ሱስንዮስ ዘመነ መንግስት ጊዜ ነው፡፡ የአፄ ሱስንዮስ ዘመን የሃይማኖት ጭቅጭቅና ጦርነት የነበረበት ወቅት ብቻ ሳይሆን ዘመናዊ ትምህርትና የለውጥ ስራዎች የተጀመሩበት ወቅትም ነበር።  

ምንጭ :- ሐተታ ዘርዓያዕቆብ እና መጽሐፈ ጨዋታ ስጋዊ ወመንፈሳዊ

11 months, 2 weeks ago
[አዲስ ለየት ያለ ነገር](https://t.me/M_RAFATOEL)

አዲስ ለየት ያለ ነገር
ጻሕው
ይሕ የምታዩት ምስል የጻሕው ፎቶ ነው።
  ከአራዊት ሁሉ ደስተኛና ተወዳጅ ነው፤ እርሱ የእባብ ጠላት ነው።
ጥቂት ከበላ ጠግቦ በጉድጓዱ ውስጥ ይተኛል ፤ በሦስተኛውም ቀን ከእንቅልፉ ተነሥቶ በሩቅም በቅርብም ያሉ ቃሉን ወይም ድምፁን እስኪሰሙ ድረስ በታላቅ ድምፅ ይጮኻል ፤ መዓዛው በጣም ውብ መዓዛ ከመሆነ የተነሣ አራዊት ሁሉ ይከተሉታል።

ከዚጋ CLICK ያድርጉ!!! 
ከዚጋ CLICK ያድርጉ!!!
ከዚጋ CLICK  ያድርጉ!!!

"የጥንት ኢትዮጵያውያን ድንቅ ምርምሮች"
"የጥንት ኢትዮጵያውያን ድንቅ ምርምሮች"

11 months, 3 weeks ago

ሰባቱ ምዕዛሮች

ሰላም ክቡራን
ስለፀኃይ ምዕዛር በኢትዮጵያውያን ሊቃውንት

እንደ ቀደሙ ኢትዮጵያዊያን የስነ ፈለክ ሊቃውንት ገለጻ ..ከጸኃይ የሚወጣው ጨረር ወይንም ምዕዛር ይባላል።በተፈጠረች ጊዜ ሽህ ወይንም ሰባት እጅ  ምዕዛር የነበራት ፀኃይ
105(፩፻፭) ለጨረቃ
100(፻) ለከዋክብት
100(፻) ለደመናት
100(፻) ለቀላያት
አካፍላ 595(፭፻፱፭) እሷ ይዛለች።
     የብርሃን አረጫጯ ራሱን የቻለ ስርዓተ ቀመር ያለው ነው።5 ኪዳነ ወልድ መዝገበ ቃላት ላይ ፀኃይ ሕይወቷ እስካለ ድረስ ሰባቱ ምዕዛራት እንደማይዘናጉ ከየቀመሩ በስፋት ተቀምጧል።

ፀኃይ በሳይንስ ገለፃ
      የፀኃይ ሕይወት ዋናው መሠረት ኃይድሮጅን ነው ይላል።
ጉልበቷን የምታመነጨው ከእንብርቷ ነው።
ሳይንስ እንዳለው ፀኃይ የምታመነጨው ሃይድሮጅን ያለቀ እለት ምዕራፉ ይዘጋል። እስከ ዚያ ድረስ ግን ፀኃይ የማይዘጉ ሰባት ምዕዛሮች አሏት።
ውድ ቤተሰቦች በዚህ ቻናል በሳምንት አንድ ጊዜ እንለቃለን።
  የወደፊቱ ሳምንት ርዕስ ስለ ሰው አንጎል በቀደምቶቹ ኢትዮጵያዊያን እና በሳይንስ ስለተቀመጠለት ምልከታ ይሆናል።
ሳምንት ሌላ ርዕስ እስከምንገናኝ መልካም የስራ፣የንባብ፣ ሳምንት ይሁንላችሁ።

"የጥንት ኢትዮጵያውያን ድንቅ ምርምሮች"
"የጥንት ኢትዮጵያውያን ድንቅ ምርምሮች"

1 year, 1 month ago

የጆሮ አቀማመጥ የሰውን ማንነት እንደሚገልፅ ያውቃሉ?

👉-ጆሮው ከማጅራቱ ፀጉር በታች ዝቅ ያለ ሰው ጨካኝና ወንጀለኛ ነው።

👉-ትንሽ ጆሮ ያለው ሰው የግል ጥቅሙን አሳዳጅ ነው።

👉-ትልቅ ጆሮ ያለው ሰው አስደሳች ፀባይ፣ቸርና በማህበራዊ ኑሮ የሚያምን ነው።

👉-ቆም-ቆም ጆሮ ያለው ሰው ግልፅና ነገር የማይሽግ ነው።

👉-ጆሮው ከጆሮ ግንዱ ጋር ልጥፍ ብሎ በመውረድ የጥያ  ቄ ምልክት ዓይነት ከሆነ ምኞትን የሚያበዛ ሰው ነው።
"የጥንት ኢትዮጵያውያን ድንቅምርምሮች"
"የጥንት ኢትዮጵያውያን ድንቅምርምሮች"

1 year, 1 month ago

የመተካከል ዕለት 26×7=182(ኢክኖክስ)

ወደ ሃሳበ ብርሃን እንሂድ
እንደ ኢትዮጵያውያኑ አቆጣጠር ዕለቱ መጋቢት ሃያ አምስት የመተካከል ፤የመመጋገብ፣ የእኩልነት ዕለትነው።

ይህ ወር ፀኃይ በምድር ወገብ በዜሮ ዲግሪ ላይ ያረፈችበት ዕለት ስለሆነ በመላውዓለም ቀኑም ሌሊቱም እኩል አስራ ሁለት ፣ አስራ ሁለት ሰዓትየሚሆንበት አለት መጋቢት 25።
ይህም "ወርሃ ዕሪና"ወይንም "እሪና ማዕልት ወእሪና ሌሊት" በመባል ይታወቃል።
ሣይንሱ ደግሞ ኢክኖክስ ይለዋል።
በአመት ውስጥ ሁለት ጊዜ ብቻ የሚከሰተው "ወሪሃ ዕሪና"  ዓለም በተፈጠረበት መስከረም እና ዓለም በዳነበት መጋቢት ላይ ያርፋል።
ወደ ቀመረ ፊደሉ ስንገባ በግዕዝ ምሉዓት ፊደላት የምንላቸው ወደ ታች በሙራድ ሲቆጠሩ ሃያ ስድስት ናቸው።
በድምፀት ወይንም ወደ ጎን ደግሞ ሰባት ናቸው።

በዚህ መሰረት ስናባዛቸው 26×7=182 ይሰጡናል።
ይህ "ወሪሃ ዕሪና" የሚያርፍበት ዕለት ነው። በዚህም መጋቢት ሃያ አምስት የመተካከል እለት ወይንም የአመቱ ግማሽ ሆነ ማለት ነው።

በቀመረ ፊደል ዘመን ሲለካ የሃያ ስድስቱ ፊደላትና የሰባቱ ድምፀት ብዜት በዓመት ውስጥ የሚገኘውን ብርሃን የያዘ የብርሃን ቀመር ነው 26×7=182።
መንፈሳዊ ሚስጢሩን እንድትመረምሩ መጋቢት ምንድነው?
ምን ምስጢር አለው? ከሚለው እንድትጀምሩ ሐሳባችን እናስቀምጣለን።
በሌላ ርዕስ ሳምንት እንመለሳለን  እስከዛው መልካም ሳምንት።

"የጥንት ኢትዮጵያውያን ድንቅምርምሮች"
"የጥንት ኢትዮጵያውያን ድንቅምርምሮች"

1 year, 2 months ago

ፀሀይ ትዞራለች!!!!

የኛ መሬት ፀሀይን ትዞራለቸ። ፀሀይ ደግሞ እንደሚታወቀው ሚልክዌ (Milkway_galaxy) የሚባለው ጋላክሲ ውስጥ ከሚገኙ ኮከቦች አንዷ ናት።

ፀሀይ አንድ ቦታ ላይ አደለቸም እስከመጨረሻው በዚህ ጋላክሲ ውስጥ ፤ ይልቁንም ጋላክሲውን ትዞራለቸ ( Orbit) ይሄም አንድ ዙር ለመጨረስ 230 ሚልዬን አመት ይፈጅባታል።

ፍጥነቷ ደግሞ በሰዓት 826,000km ነው።

ፀሀይ የምትዞረው ምኑን ነው?

ፀሀይ የምትዞረው በኛ ጋላክሲ መሀል ላይ የሚገኘውን ብላክኦል (Black hole) ነው።

🎱 ፀሀይ ስትዞር ለምን አልታወቀንም?

ፀሀይ ስትዞር ብቻዋን አደለም ፀሐይ የራሷ የሆነ ክልል አላት ማለትም ስበቷ እስከሚደርስበት ድረስ ይሄም አንድ ሶላር (Solar system) ይባላል።

ፀሀይ ብቻዋን ሳይሆን አጠቃላይ ሶላሩን (Solar system) ይዛ ነው፤ የምትሄደው በዚህም የተነሳ በቀላሉ ላንረዳው እንችላለን እንቅስቃሴውን!!

🫧ለምሳሌ መሬት በራሷ ዛቢያ ትሽከረከራለች ፀሀይንም ትዞራለቸ፤ ነገር ግን እኛ የሚታወቀን ነገር የለም ማታ እና ቀን ከመፈራርቁ ውጪ ወይም ወቅቶች ከመፈጠራቸው በስተቀር!!!!
"IT'S TIME SCHOLARS TIME"
"IT'S TIME SCHOLARS TIME"

1 year, 2 months ago
[**REPOST**](https://t.me/ETHIO_DINK_MIRMIROCH)

REPOST
"አንዳንዶች የአድዋን ድል ድል ባናደርግ ይሻል ነበር" ይላሉ።
ለምን ሲባሉ " ሃገራችን እንደ ምዕራቡ ያደገች ሃገር ትሆን ነበር" ብለው ይመልሳሉ።
እውነቱ ግን ይሔ ነው፤ ስለ ቀደምት ስልጣኔያችን ራሳቸው የምዕራባዊያን እንቁ ተመራማሪዎች በድርሰቶቻቸው ይህን ጽፈዋል!!!

ከምዕራባዊያን ሳይንቲስቶች ብዙ ጊዜዋን ምርምር ላይ ያሳለፈች አንዷ ዶክተር ዱሩሱላ ይህን ጽፋለች <አውሮፓውያንም ሆኑ እስያውያን ባልሰለጠኑበት በዚያን ወቅት ኢትዮጵያ ከፍተኛ ስልጣኔ ላይ ነበረች> በማለት ተናግራለች።
ሄረን ሉድዊግ ደግሞ <<ከጥንታዊ ታሪክ ጀምሮ ኢትዮጵያውያን እጅግ የተከበሩ ነገር ግን ምስጢር የሆኑ በጦርነት ጊዜ ሃይለኛ ሕዝቦች ናቸው>> በማለት አድናቆቱን ገልጿል።
@ETHIO_DINK_MIRMIROCH
@ETHIO_DINK_MIRMIROCH

1 year, 2 months ago
[ዐውደ\_ወርኅ](https://t.me/ETHIO_DINK_MIRMIROCH)

ዐውደ_ወርኅ
ሠላሳ ቀናት መመላለስ ነው።

ዐውደ_ዓመት
365 ዕለት ከ 15 ኬክሮስ6 ካልዒት መመላለስ ነው።

ዐውደ_አበቅቴ
አስራ ዘጠኝ ዓመት መመላለስ ነው።

◌ይህ ፅሑፍ ከአሁን በፊት እዚህ ቻናል ላይ POST ተደርጎ ነበር። እስካሁን ፓስት ከተደረጉት ብዙ VIEW ያለው ይህ POST ነው። ከ1500 በላይ VIEW !!!
የጥንትኢትዮጵያውያንድንቅምርምሮች
የጥንትኢትዮጵያውያንድንቅምርምሮች

We recommend to visit

https://www.hulepay.com/

Last updated 1 week, 3 days ago

🍿የ VIP ቻናላችንን በአነስተኛ ክፍያ በመቀላቀል ሁሉንም ፊልሞችን ማግኘት ትችላላቹ።
🍿 CHANNEL ~> @Wase_Records
🍿 BOT ~> @Wase_Records_Bot
🍿 OWNER ~> @The_hacker_person
🍿 VIP ~> @The_hacker_person

Last updated 3 days, 8 hours ago

አፍሪወርክ ቢዝነሶች እና የግል ቀጣሪዎች ለስራቸው ከሚፈልግዋቸው ፍሪላንሰሮች ፣ ቋሚ ሰራተኞች እንዲሁም የትርፍ ጊዜ ሰራተኞች ጋር በቀጥታ የሚገናኙበት ፕላትፎርም ነው።

አሰሪዎች ስራ ለመልቀቅ @freelanceethbot ይጠቀሙ

Afriwork in English @freelance_ethio

Last updated 1 month, 3 weeks ago