አፍሪወርክ ቢዝነሶች እና የግል ቀጣሪዎች ለስራቸው ከሚፈልግዋቸው ፍሪላንሰሮች ፣ ቋሚ ሰራተኞች እንዲሁም የትርፍ ጊዜ ሰራተኞች ጋር በቀጥታ የሚገናኙበት ፕላትፎርም ነው።
አሰሪዎች ስራ ለመልቀቅ @freelanceethbot ይጠቀሙ
Afriwork in English @freelance_ethio
Last updated 1 month ago
ዜና እረፍት።
ፋሲል ጥላሁን በሞያው አርክቴክት እና የአርክቴክቸር መምህር ነው። ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በ ሀዋሳ S.O.S ትምህርት ቤት ከተማረ በኋላ ከ2005 - 2009 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ EiABC የመጀመሪያ ዲግሪውን በአርክቴክቸር እና ሁለተኛ ዲግሪውን ደግሞ እዛው በ EiABC ከ2012 - 2013 ዓ.ም በUrban Planning ተከታትሏል።
ከ2010 ዓ.ም እስከ አሁን ድረስ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የአርክቴክቸር መምህር ሆኖ ሲያገለግል ቆይቷል።
ከመምህርነቱ ባሻገር ጎን ለጎን የሚወደውን ሞያ እየተገበረው አያሌ የህንፃ ግንባታዎች ላይ ንድፍ እና ክትትል በማድረግ ይሳተፍ ነበር።
ፋሲል በሞያውም ሆነ በስራው እጅግ ምስጉን፣ ተወዳጅ እና ታታሪ ሰው ነበረ።
ባደረበት ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ገና በለጋ ዕድሜው፤ በዕለተ ረቡዕ ሚያዝያ 16/2016 ዓ.ም በተወለደ በ32 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል።
ስርዓተ-ቀብሩም ሚያዝያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም አርብ ከቀኑ 6:00 ወዳጅ ዘመዶቹ በተገኙበት በጥቁር ውሃ ማርያም ቤተክርስትያን ይከናውናል።
ለወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናትን እንመኛለን።
ነፍሱ በሰላም ትረፍ።
ኪነ-ቅርጽ።
ጥቁርአንበሳ ሀውልት፣ ሆለታ።
የየካቲት ፲፪ የሰማዕታት መታሰቢያን እና የሐረር የራስ መኮንን ሐውልትን የነደፉትና የቀረጹት ሁለቱ ኩሮኤሽያውያን (ያያኔው ዩጎዝላቪያውያን) ሚስተር አንቱን ኦገስቲንቺች እና ሚስተር ፍራኖ ክርሲኒች እንደሆኑ ይታወቃል። እነዚሁ ሰዎች የቀረጹት ሌላ ሦስተኛ ሐውልትም አላቸው። ጥቁር አንበሳ ይባላል። የጥቁር አንበሳ ሐውልት የተተከለው በሆለታ የጦር መኮንኖች ማሰልጠኛ አካዳሚ ግቢ ውስጥ ነው።
የምስል መግለጫ:
ምንጭ። ጀማል አብዱልአዚዝ እና ዘሪሁን ጉልቴ
@ethiopianarchitectureandurbanism
አፍሪወርክ ቢዝነሶች እና የግል ቀጣሪዎች ለስራቸው ከሚፈልግዋቸው ፍሪላንሰሮች ፣ ቋሚ ሰራተኞች እንዲሁም የትርፍ ጊዜ ሰራተኞች ጋር በቀጥታ የሚገናኙበት ፕላትፎርም ነው።
አሰሪዎች ስራ ለመልቀቅ @freelanceethbot ይጠቀሙ
Afriwork in English @freelance_ethio
Last updated 1 month ago