Ezedin Sultan

Description
We recommend to visit

Solcu Gazete Telegram kanalı.

Reklam ve iletişim için: @iletisimads

Last updated 1 week ago

Gündemi tek mesajla takip etmek için bildirimleri açabilirsiniz.

İletişim: @bptdestek

Last updated 2 months ago

Telegram sayfamda, Instagramda paylaşamadığım, +18 paylaşımlar yapıyorum🌹

Last updated 1 week, 5 days ago

4 weeks ago

M Sanni Ali ትዝብት፣ የኔም ትዝብት ነው 😏😣🤨

ትናንት ማታ ስለ ስራ ላይ የወተት ምርት ላይ ዶ/ር ጄሉ ከግብርና ምርምር ያቀርብ ነበር:: ካልተሳሳትኩ 60 ከዝም 40 ሰው ነበር የታደመው!

እግራች ወስፌ ደረታችን ሰፌድ (Thin Muscle thread interwoven around ribs) የመሰለው የምግብ እጥረት ነው በተለይ በልጅነታችን - እንቁላል ል አይበላም : ወተት ማምረትም መጠቀምም ስለማንችል! መቼም ማራስመስ እና ኩዋሺያኮርን በአይኑ ያየ አይኖርም ማህተሙ ግን እግር ላይ አለ::

ማማ እና ሾላ ቀጭን ወተት በውሀ ነገር ናቸው! የሆላንድ ወተት የደረሰበትን በሰፊው ሌላ ግዜ እፅፍላችሁዋለሁ:: ሆላንዶች እግራቸው የኛ ተቃራኒ ነው - በወተት ቺዝ እና ሳይክል የዳበረ ነው:)

እኔ ከ16/17 አመት በፊት በዘርፋ በማማከር ትንሽ የወትት እርባታወችን አይቻለሁ:: እጅግ በጣም ሁዋላ ቀር ነን!
የወተት ዱቄት አገር ውስጥ ገብቶ: የልጅ ወተት በውድ ከውጭ ገብቶ - ለነዳጅ ዶላር የለንም ቢል ትክክል ነው!

አታውቁ ከሆነ የአዲስ አበባ ሀብታም ልጆች የሚያድጉት የአየር መንገዱ ሆስቴሶች በሚያስገቡት የአውሮፓ እና አሜሪካ ወተት ነው:) በነዚህ ሀገራት የህፃናት ወተት (እና ዳይፐር) የሱፐር ማርኬት ዋጋው ለሀገራቱ ነዋሪወች በግማሽ ይቀንሳል - ለዚህም ለንግድ እንዳይውል በአንድ ግዜ ከ2 በላይ መግዛት አይቻልም!

ማታ ይሰጥ የነበረው ትምህርት ከስፋቱ ባሻገር ግልፅነቱ ማራኪ ነበር! ክህሎት ላይ ያተኮረም ነበር!

እኔን የገረመኝ 125K አባል ያለው "ስለ ስራ" ላይያላችሁ አባላት ላም ባታረቡ እንኳን የወተት ላም የሚያረባ ዘመድ እንኳን የላችሁም?! ምክኒያቱ ምናልባት የተደራሽነት ከሆነም አድሚኖቹ አስቡበት Birhan Nega Ina Omer Zubeyda Awel et al. እስኪ!

የ1 ጥሩ ላም ዋጋ 150-175ሺ በደረሰበት ሀገር ማኪያቶ ከየት ነው የምትጠጡት:)?

መካከለኛ ወይንም ጀማሪ ባለሙያን አማክሩኝ ብትሉ ብዙ ብር ትጠየቃላችሁ - ትምህርት በነፃ ሲቀርብላችሁ ዘመድ አዝማዳችሁን ጋብዛችሁም ቢሆን አስተምሩ! ያለ ትምህርት የሚሰራ ስራ የትም አያደርስ!

ሀገር ውስጥ ስራ የለንም ባይሆን ይህ ዘርፍ እንደ ሀገርም ትልቅ ለውጥ ያመጣል - የመንግስት ፓሊሲ ምን ነበር!!?

ትልቁ ተመራማሪ ዶ/ር የምርምር ፕሮፓዛል ግምገማ ላይ መቀሌ ላይ ወተትን ማቀነባበር ላይ የምርምር ስራ ያቀረበ ልጅ ነበር - አራት ሰአት ላይ ተት አልቋል በሚባልበት ከተማ ወተት ከየት እምጥተህ ነው የምታቀነብብረው ነበር ያለው!

እኛ ተመተናል የሚለው ብቻ እማ አይገልፀውም!

መልካም እሁድ!
@highlight

4 weeks ago
የመማርን ጥቅም ከዚህ ገጠመኝ በላይ አስተማሪ …

የመማርን ጥቅም ከዚህ ገጠመኝ በላይ አስተማሪ የለም።
Hawlet Ahmed ይህ ሰው በመማሩ ምን ያህል እንደጠቀመ ተመልከችልኝ

አሊኑር አደም እባላለሁ:: ትውልድና ዕድገቴ ነገሌ ቦረና ከተማ ሲሆን ኑሮዬ አዲስ አበባ ነው ::

"እልህ ምላጭ ያስውጣል" ይላል ያገሬ ሰው።

አባቴ አለማዊ ትምህርት ሊያስተምረኝ ፍቃደኛ አልነበረም። መድረሳ አስመዝግቦኝ ቁርዓን ተማርኩኝ።
ከዕለታት አንድ ቀን የትምህርት ዕድል ያገኙ የሰፈሬ ልጆች የማላቀውን ፅሁፍ መሬት ላይ እየጻፉ ከት ብለው ይስቃሉ።

እልህ ያዘኝ። ማንበብ አለመቻለ አንገበገበኝ። ገንዘብ አጠራቅሜ ደብተር ገዛሁ። አንዱ ጎረቤታችን ልጁን ሊያስመዘግብ ወደ ትምህርት ቤት ሲሄድ ተክትዬ ሄድኩኝ። እንደ ወላጅ ሆኖ አስመዘገበኝ።

በዚህ ሁኔታ ነበር ወደ ትምህርት አለም የተቀላቀልኩኝ።
አረት ጊዜ Graduate አድርጌያለሁ:
~የመጀመሪያ የዶክትሬት ዲግሪ, በዉስጥ ደዌ ህክምና specialty እንድሁም በPublic Health masters ዲግሪ ከሀገር ዉስጥ ያገኘሁ ስሆን ከሀገር ዉጪ በጃፓን ሀገር
ከNagasaki University
በTROPICAL MEDICINE ተመርቅያለሁ:: አልሃምዱሊላህ!

በስራ ዓለም ታካሚዎችን ከማገልገል ጎን ለጎን የህክምና ተማሪዎችን አስተምራለሁ:: በተለያዩ ሀላፊነትም አገልግያለሁ :
1. ኮሌጅ ዲን (የህክምና እና ጤና ሳይንስ)
2. ዋናው ስራ አስክያጅ (ረፈራል ሆስፒታል)
3. በዉስጥ ደዌ ሕክምና ድህረ ምረቃ ትምህርት ፕሮግራም አስተባባሪ::

*ባለችኝ ትንሽዬ ዕውቀት በማንኛዉም ሰዓት ለሚገጥማችሁ የጤና ችግሮች ልታማክሩኝ ትችላላችሁ ::
አመሰግናለሁ!

4 weeks ago
የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር የመንገደኞች ትራንስፖርት …

የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር የመንገደኞች ትራንስፖርት አገልግሎት ሊጀምር መሆኑን ኢንጂነር ታከለ ኡማ ገለጹ

ቅዳሜ ጥር 17 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮ ጅቡቲ ምድር ባቡር አክሲዮን ማህበር ከመጪው የካቲት ወር ጀምሮ በኦንላይን ቦታ በማስያዝ የህዝብ መንገደኞች ትራንስፖርት አገልግሎት እንደሚጀምር የአክሲዮን ማህበሩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ገልፀዋል።

ኢንጂነር ታከለ ኡማ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ "ጥራት ያለዉና እና ቀልጣፋ የጉዞ አገልግሎት ለመስጠት ሲባል እንዲሁም ትክክለኛ የመንገደኛ መረጃን ለማረጋገጥ እና ከችግር የጸዳ ጉዞን ለማመቻቸት አስፈላጊ በመሆኑ ለሁሉም የሀገር ውስጥ ተሳፋሪዎቻችን ብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) በመጠቀም ኦንላይን ቦታ ለመያዝም  ሆነ ለመጓዝ  መስፈርት መሆኑን ለማስታወስ እንወዳለን" ሲሉ አስታውቀዋል።

3 months, 4 weeks ago

ግዴታው: ሀብታም መሆን ወይስ ራስን መቻል??

3 months, 4 weeks ago

ለትብብራችሁ እናመሰግናለን፣ ተገኝቷል!

4 months ago

ሸማቾች/ገዢዎች/ ብር ሳይዙና ለመግዛት ሳይወስኑ ገበያ ወጥተው ጠይቀው በምን ሊያስቀይሱ(ሊፈረግጡ) ይችላሉ?
(ነጋዴዎች ስለከፋቸው ለማቻቻል የተዘጋጀ?

? ገበያ አሁን ነው የወጣሁት፣ ጠይቄ ልምጣ፣ ዞር ዞር ብዬ ልይ
(ይሄኔ እግራቸው እስኪቀጥን ዞረዋል?

?ልክክ ብሎላቸው ይዞኛል
(ኧረ ሌላ የላችሁም?

? በገመቱት ዋጋ ሲሰጣቸው
(ባንክ ሄጄ ብር ይዤ ልምጣ?፣ ከዛ ብስ

? ደንበኛዬ ጋር ልግዛ ብዬ ነው እንጂ የተሻለ አግኝቻለሁ
(አንዴም ገዝተው አያውቁም እኮ?

?ተደራድረው ጨርሰው ሌላ ሰው ጠርተው በቃ ይቅር
(ሲፈረግጡ

? የሚፈልጉት ከለር ሲሰጣቸው እንዲህ አይነት የለህም
(ፋብሪካ የማያውቀው ከለር ምርጫ?
.
.
.
መነሻ ሀሳብ ከኮሜንት የተወሰደ

እስቲ እናንተም ጨምሩበት?

6 months, 3 weeks ago

በጊዜ መሸሽ ማሸነፍ ነው!

6 months, 3 weeks ago

የገረመኝን ትዝብት ላጋራችሁ
(በረከት በላይነህ ስለ ወላይታ ህዝብ ከሰጠው ምስክርነት ጋር የሚጣጣም)

በጠዋቱ በቅርቡ በግፍ የተገደለ አንድ ወንድማችን ችሎት ለመካፈል ተደራቢ ሆኜ ሄጄ ነበር። ለምስክር ከቀረቡ ሁለት የፖሊስ አባላት የሰማሁት ምስክርነት ስለገረመኝ ላጋራችሁ አመጣሁት።

ክስተቱ ከተከሰተ 6 ወር ሆነው። ገዳዮቹ ሟችን ከአዲስአበባ ሀዋሳ ኮንትራት ያዙ። አላማቸው ዝርፍያ ስለነበር አዳማ ፈጣን መንገድ ውስጥ በአሰቃቂ ሁኔታ ገድለው፣ ሬሳውን በዘግናኝ ሁኔታ ጥለው መኪናውን ይዘው ይሰወራሉ።

የዛሬ ፖሊሶች ከወላይታ ሶድ ድረስ ለመመስከር የመጡት ከዚህ ቡኋላ የተከሰተውን ክስተት ነው(ሀሳቡ ሲጨመቅ)

ገዳይ መኪናውን ከወሰደ ቡኋላ አባቱ ዘንድ ወላይታ ሶዶ ወስዶ ያስቀምጣል። መኪናው የተቀመጠባቸው አባት ለልጃቸው ሶስት ቀን በተደጋጋሚ ቢደውሉ ስልክ አላነሳም። ይሄኔ ወደ ፖሊስ ዘንድ ሄዱ . . .

"እኔ ልጄን አላሳደኩትም። ከኔ ጋር አላደገም። አሁን ያለበትን ተጨባጭ ባህሪ አላውቅም። አንድ መኪና ባለሙያ ይዤ እመጣለሁ ብሎ አስቀምጦ ሄዷል። ስደውልለት አያነሳም። መኪናው የራሱ ከሆነ አመሳክራችሁ ትሰጡታላችሁ። መኪናው ለጊዜው ፖሊስ ጣቢያ ይቀመጥ" ለፖሊስ አመለከቱ

ገዳይ የመኪናውን ቁልፍ የቤቱ መግቢያ ላይ አንጠልጥሎ ነበር። ፖሊስም ጉዳዩ እስኪጣራ መኪናውን ተረክቦ ጣቢያ ወስዶ አስቀመጠ።

አባት ማለት እኚህ ናቸው። ለእውነት የቆሙ።

(ለመኪና ስርቆት የሰዎችን ህይወት ለሚቀጥፉ ጥሩ መቀጣጫ የሆነ ቅጣት ያገኛቸዋል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ

We recommend to visit

Solcu Gazete Telegram kanalı.

Reklam ve iletişim için: @iletisimads

Last updated 1 week ago

Gündemi tek mesajla takip etmek için bildirimleri açabilirsiniz.

İletişim: @bptdestek

Last updated 2 months ago

Telegram sayfamda, Instagramda paylaşamadığım, +18 paylaşımlar yapıyorum🌹

Last updated 1 week, 5 days ago