● Welcome to Ethio music Channel
➤ For any promotion and Advertising 📩 inbox @Markonal21 ወይም @ethiomusic21bot
.
.
● የበጎ አድራጎት ስራዎችን በነፃ ፖስት እናደርጋለን ለመልካምነት ቦታ አይመረጥም ! ያዋሩን
.
.
● የሀገር ውስጥ አዳዲስ
ሙዚቃዎች
አልበሞች በፍጥነት ያገኛሉ
.
● እንዲሁም በቀናነት JOIN & SHARE ያድርጉ !
Last updated 6 months ago
?? የምርጥ ሙዚቃዎች መገኛ ??
For promotion and Advertisements
? @Mussegirma
#ካሮት_ሙዚክ✋
ሰለ ቻናላችን ማንኛውንም የፈለጉትን ሙዚቃ እና ያለወትን ቅሬታ
ሆነም አስተያየት በማለት
በዚህ #bot✍ ማቅረብ ትችላላችሁ፡፡
???????????
http://t.me/yekonjochumenahriabot
እናመሰግናለን?
Admin
@Aymu_xo
ሰው እንደ አሸን በዝቶ በሞላበት ምድር
አፌ ሳይናገር ቃላት ሳልደረድር
የሰው ዘር መራቤን የአይኖቼን ናፍቆት
ካንድ አንቺ በስተቀር ማን አይቶኝ ማን አውቆት
ምክንያት ስፈልግ እንባዬን ለመዝራት
የትም ትቢያ ሲሆን የወንድነት ኩራት
ከማኩረፍ ስላመድ
ከሀዘን ስዛመድ
ህይወት ተስፋ ሲያጥረኝ ሞቴን ስደግሰው
ካንድ አንቺ በስተቀር
ማን ነበረ ያለኝ 'አይዞህ' ቀርቦ እንደሰው
የፊቴን ጨለማ ግንባርሽ ደገመው
የእንባየ መስመር ጉንጭሽን አመመው
ሲከፋኝ ተከፋሽ
ስወድቅ አብረሽ ጠፋሽ
መሠልሽ እና እራሴን ጠበበቺኝ አለም
ካንቺ ወርድ ቁመት የሚበልጥ የለም።
የፍቅር መለኪያው
የሠላም መስበኪያው
ከዚህ እስከ አንቺ ነው የደግነት ዙፋን
ታዲያ
እኔና ምስሌ ዛሬ ለምን ከፋን
ለምደን ብትርቂን አቋቋምም ጠፋን።
ቢሆንም ሔደሻል
ወጋገን ራቀህ
ከፊት ለፊትህ ላይ ጨለማ ተጣለ?
መጓዝ ስትጀምር
ሀሞትህ ፈሰሰ ጉልበትህም ዛለ?
እንዳው የሱስ ነገር የሚልህ ሰው በዛ
ንግግርህ ሁሉ አጧል አይደል ለዛ
ደከመህ
ታከተህ ሰለቸችህ አለም?
አይዞህ ቀና በል ግድ የለም
መንገዶቹ ሁሉ
በተዘጉ ጊዜ ከተስፋህ ተሟገት
ወትሮስ
ፋሲካ ለመድረስ
ያደክም የለም ወይ መስቀሉን መጎተት
ካደረጉበት ግፍ ከፈተኑት አንጣር
ምን አላት እና ነው ለመነሳት መጣር
የልቅ
ወደ ነገ መንገድ
ዝም ብለህ ተራመድ
መንገድህ አልቀናም
ዳግም ስትራመድ ፤ መንገዳገድ በዛው
ሺ ላብ ጠብ አድርገህ
ለቁርስህ አይበቃም ፤ ድካምህ የገዛው።
ለውጥ ልብህ አለ ፤ ውሉን አትጨብጥም
የነካኸው ሁሉ
ያተርፈኛል ስትል ፤ አይነቱን አይሰጥም።
ሰው ሁሉ የሚልህ ፤ መጓዝህን አታቁም
ግን~~~
ታግለህ ከዛሬ ጋር ፤ ጥለኸው አታውቅም።
ገፍ ጨብጠህ ነፋስ ፤ ወርቅ ስታፍስ አመድ
አሁን ደረስኩ ስትል ፤ ሌላ ቀጣይ መንገድ
ይሄን ሁሉ ትጋት ፤ ያልተረዳ ዘመድ
ከበበህ ዙሪያህን ፤ ማረፊያ ጥላ አጣህ
እንደ ትላንትናህ
ለነገ የሚሆን ፤ ተስፋ ሳቲዝ ወጣህ?
በቃ ባለህ እርጋ ፤ ወደ ውስጥህ ተንፍስ
ወዝህን በምንም ፤ ሜዳ ላይ አታፍስ
ለውጥ ካልተፃፈ
ወይም ከዘገዬ ፤ ካሰብከው ላይ ማረፍ
ያለህን አትጣል ፤ ከያዝከው ነው ማትረፍ።
✍እኔን ባይ
በመኖር አጸድ ውስጥ
(በእውቀቱ ስዩም)
ጊዜ ከሰው መሀል- መርጦ ሲያቀማጥል
ማጣት አለ ደሞ፥
የወለዱትን ልጅ፥ ጉድፍ ላይ የሚያስጥል
በተፈሰከ ቀን፥ ጾምን የሚያስቀጥል::
እድልና ትግል በሚጫወቱበት
በደልዳላው ስፍራ
አለቃና ጭፍራ-
-ቃል ሲለዋወጡ፥ ውልና መሀላ
“አብረን እናድጋለን” ቢባል ለይስሙላ
ወንዙን ሳያጎድል ፥ሐይቁ መች ሊሞላ፤
ጸሐይ ብትወጣ
ፍጥረት በጠቅላላው ጸጋዋን ቢቀበል
የደመናም ጠበል፥
ለሁሉ ቢደርስም
አንደኛው አያድግም፥ አንዱን ሳያከስም::
እፈራለሁ
[ ምካኤል ምናሴ]
ቆይ፥
መንፈስ ብትሆኚስ?
ለእኔ ብቻ የሚታይ ፥ ከህልም የተሰራ፥
'ዴልዩዥን' ብትሆኚስ?
የምኞት መዶሻ ፥ ጠራርቦ ያቆመሽ ፥ የልቤ ፈጠራ፤
ከጨዋታ መሐል ፥ ድንገት ብትጠፊብኝ፤
'የታለች?' ስላቸው፥
'ማን ናት ደሞ?' ብለው ፥ ሰዎች ቢስቁብኝ፤
ህልም ብትሆኚስ?
ስነቃ ብትቀሪስ?
ቆይ አሁን፥
ጭራሹን ባትኖሪስ?
ሞልተሽኝ በእቅፌ፥
እጆቼን ቀንፌ፥
ደስታዬ እንደድመት ፥ ልቤን እየላሰው፥
ሳቅ ሆዴን ሲያምሰው፥
ባዶዬን ቢሆንስ፥
ብቻዬን እንደእብድ ፥ የምታየው ለሰው?
እንደንፋስ ነክቶኝ ፥ ሲያልፍ ሰቀቀኔ፥
ከተዳከምሁበት ፥ ከውብ ሰመመኔ፥
'ቢሆንስ?' እያልሁኝ፥
ድንገት እየባነንሁ ፥ እፈራለሁ እኔ፥
መቼም፥
ነፍሱን መርጦ አጥቦ ፥ ውድ አካል ቢያለብሰው፥
ምን ያህል ቢወደድ ፥ ፍቅር ቢያንተርሰው፥
እንዲህ ሁሉ አምሮለት፥
በስጋና በደም ፥ አይገለጥም ሰው።
እንደ እርግማን ሲሆንብን
አሜን ብለን የደረሰን ገፍ ምርቃት
እየፈጩን አስገብተው በዘመን ቋት
ስንሳቀቅ
ስንጨነቅ
ስንወረር በመከራ ስንከበብ በጥላሸት
ሲሆንብን ሰላም ውሎ ብርቅ ማምሸት
አይዞን ያለን ማን ነበረ
የልቅ እንድህ
የደገፍነው ቀን ሲያነሳው ፊት አዞረ።
ፀንቶ እንድቆም ሁለት እግሯ
ራስ መቻል
መጠንከር ነው ንጎጎሯ
እንደ ዋዛ ሞት አይጥለው የበረታን
ስቀንባት ልታስቆጨን በጥረቷ ልትረታን
ትወጣለች በተስፋ ቃል
ሰው ለመሆን
ራስ ችሎ ለመራመድ ስንት ድካም ግን ይበቃል?።
ያለሁት ምድር
ለዛውም ደግሞ መኖሬ ምንም
ምኞቴ ሰማይ
አንድ ሰው ቅሉ ሁለት ባይሆንም
እየተጋጨሁ
በራሴ ሜዳ ከራሴ ትግል
ግማሽ ውስጠቴ
ሌላኛው ጎኔን ሲነካኝ ፍንግል
ጣር ሁኖብኛል
በወጀብ መሐል ፀንቶ እግር ማቆም
እኔው አጥፍቼ
ደግሞ በፀፀት ጣቴን መጠቆም።
ስትፈልግ አሁን ማረኝ
አይኔን ዳብሰህ አነጋግረኝ
ተስፍ ስጠኝ ስንቅ ለነገ
መኖር ህልሜን
አይመፅውተኝ የፈለገ
ከነ አልጋዬ ስበህ አንሳኝ
አለሁ ልበል
በሰው መሐል ሰው አይርሳኝ።
ካስፈለገም
አሁን ለያት ስጋ ነፍሴን
አልወደውም በተስፋ ቃል ምልልሴን
ጢንጥዬ ሙቅ ብርሃን ሳያገኙ
ጨለማ ውስጥ እየዋኙ
ሌላ ቀን ነው በሚል ተስፋ
ለምን ዛሬ ኑሬ ልጥፋ።
● Welcome to Ethio music Channel
➤ For any promotion and Advertising 📩 inbox @Markonal21 ወይም @ethiomusic21bot
.
.
● የበጎ አድራጎት ስራዎችን በነፃ ፖስት እናደርጋለን ለመልካምነት ቦታ አይመረጥም ! ያዋሩን
.
.
● የሀገር ውስጥ አዳዲስ
ሙዚቃዎች
አልበሞች በፍጥነት ያገኛሉ
.
● እንዲሁም በቀናነት JOIN & SHARE ያድርጉ !
Last updated 6 months ago
?? የምርጥ ሙዚቃዎች መገኛ ??
For promotion and Advertisements
? @Mussegirma
#ካሮት_ሙዚክ✋
ሰለ ቻናላችን ማንኛውንም የፈለጉትን ሙዚቃ እና ያለወትን ቅሬታ
ሆነም አስተያየት በማለት
በዚህ #bot✍ ማቅረብ ትችላላችሁ፡፡
???????????
http://t.me/yekonjochumenahriabot
እናመሰግናለን?
Admin
@Aymu_xo