የስራ ማስታወቂያ ከጋዜጣ ፣ ከቲቪና ራዲዮ ፣ ከማስታወቂያ ቦርድ ፣ ከድህረ-ገፅና ከማህበራዊ ሚዲያና ከመሳሰሉት ቦታዎች በአንድ ቦታ ተሰብስበው ያግኙ::
#Group t.me//Ethio_Jobs2000
#የመዝናኛ ቻናል https://t.me/+UPjrnHF6QzI0ZmQ0
https://t.me/+h0l2XzeI8RQyODlk
For promotion ? @Share_Home
Last updated 1 month, 2 weeks ago
ከቅዳሜ በስተቀር በየዕለቱ፣ ከሰኞ እስከ ዓርብ ረፋድ ከ3:30 እስከ 5:00፣ እሁድ ከጠዋቱ 2:00 እስከ 4:00 በብስራት ኤፍ ኤም 101.1
Last updated 7 months, 4 weeks ago
Certified Professional Life Coaches
የቻናላችንን አነቃቂ ቪዲዮ መመልከት ለምትፈልጉ
https://www.youtube.com/@inspireethiopiamedia ? ይሄንን ሊንክ ይጫኑ
Last updated 9 months, 4 weeks ago
"የወንድምህን ኃጢአት መሸፈንና የእርሱን ኃጢአት እንደራስህ አድርግህ በእርሱ ፋንታ መሞት ካልቻልክ ቢያንስ ስለ ኃጢአቱ አትፍረድበት።››
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"ሲያመነዝር ያየኸውን ሰው አንተ ንጹሕ ብትሆንም አትናቀው። ምክንያቱም አታመንዝር ያለው ጌታ አትፍረድም ብሏል።"
አባ ቴዎዶር
"አንድ ሰው ኃጢአት ሲሠራ ብታይ እንኳን አትፍረድበት:: አንዳንዴ ዓይንህም ሊሳሳት ይችላል።"
ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው
"ለኃጢአተኛው ክንፍህን ዘርጋለት:: ኃጢአቱን ልትሸከምለት ባትችል እንኳን ሸፍንለት።"
ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ
"ሁል ጊዜ ከወደቃችሁ በኋላ ወዲያውኑ መነሳትና ወደ እግዚአብሔር መመለስ አስፈላጊ ነው" ይሉናል፡፡ ሁላችንም ያለማቋረጥ ኃጢአትን እንሠራለን፤ ተንሸራተንም እንወድቃለን፡፡ ምንም እንኳን በቀን መቶ ጊዜ ብንወድቅም ወደ ኋላ ዞር ብለን ሳናይ ተነስተን ወደ እግዚአብሔር መመለስ አለብን የሆነው ሆኗል፤ ያ ጊዜም አልፎአል፡፡ ከእግዚአብሔር እርዳታ እንጠይቅ፤ ተስፋችንን ከውስጣችን ሊያጠፋ ለሚፈልገው ዲያብሎስ፤ "እግዚአብሔር ከእኔ በላይ እኔን ይወደኛል ይቅርም ይለኛል" እንበለው፡፡
(አረጋዊ ታዴዎስ)
🌿 @Father_advice🌿
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
እግዚአብሄር ቸር ነው!
ሰው እግዚአብሄር ቸር ለመሆኑን ማስረጃ ቢጠይቅህ
የራስህን ጉድ ታውቃለህ እና እኔን ችሎአል እና እግዚአብሄር ቸር ነው ኑ ቅረቡ ይምራችኋል!
©አባ ገብረ ኪዳን
“ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ ከኃጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ፤”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥15
ምን የማያልፍ ነገር አለ
ቀኑን ወስዶ ጨለማን ያመጣ ጨለማውን ወስዶ ቀኑን ያመጣል
የውርደት ዘመን በክብር ዘመን ይተካል
የማጣት ዘመን በማገኜት ዘመን ይተካል
ደግሞ ሁል ጊዜ ደስታ ቢሆን እግዚአብሄር ይረሳል
ሁል ጊዜም መከራ ቢሆን ሰው በሞት ያልቃል
እግዚአብሄር ግን እያፈራረቀ ህይወትን ቀጣይ አድርጓአል
"ክፉ ዘመን ቢመጣና በቤተክርስቲያን መገልገል ባንችል ቀድሰን የምናቆርበዉ እናንተ ቤት ስለሆነ ክርስቲያኖች ሆይ የምትኖሩበትን ቤት በቅድስና ና በክብር
ያዙት፤ ጠብቁት"
(ሊቀ ሊቃዉንት ስምዐኮነ መልአክ)
ክርስቲያን ማለት ቤቱን ቤተክርስቲያን
ቤተክርስቲያንን ደግሞ ቤቱ የሚያደርግ ነው!
ከክርስቶስ ልደት በፊት በ60 ዓ.ዓ የኖረው ጠቢቡ #ሲሴሮ ስለቁጣ ሲናገር ፦ << በንግሥና ዙፋን ተቀምጦ በቁጣ ቀንበር ስር እንደሚሰቃይ ንጉስ የሚያሳዝን የለም።>> ይላል፡፡
ንጉስ ግኔስ ፒሶ ፦ ቁጡ ፣ ግትር እና ማስተዋል የጎደለው ንጉስ ነበር ። #ፒሶ :: አንድ ቀን አንድ ወታደር ለአሰሳ ከወጣበት ሲመለስ አብሮት የወጣውን የመቶ አለቃ ትቶት ብቻውን ይመለሳል ። ይህን የሰማው #ንጉስ ፒሶ ወታደሩ እንዲገደል ትእዛዝ ሰጠ ። ለሞት ፍርዱም ምክንያት ፦ " ወታደሩ መቶ አለቃውን ገድሎት ሊሆን ይችላል ፤ ባይገድለውም ደግሞ አለቃው ትቶ መምጣቱ በራሱ ብቻ ያስገድለዋል " የሚል ነበር ።
ሞት የተፈረደበትን ወታደር የሚገድል ሌላ ወታደር ታዘዘና ወደ አንድ ከፍታ ይዞት ይወጣና ሰይፉን መምዘዝ ሲጀምር። መቶ አለቃው ድንገት ከተፍ ይላል ። ገዳዩ እና ተገዳዩ በዚህ ደስ ተሰኝተው ከመቶ አለቃው ጋር ሦስቱም ወደ ቤተ መንግስቱ ይመጣሉ ። ይህን ጊዜ በቤተ መንግስቱ ደስታ ይሆናል ። ነገር ግን #ፒሶ ሶስቱን ወታደሮች በአንድ ላይ ሲመለከት በቁጣ ነደደ ። ወዲያው ሦስቱም እንዲገደሉ ትእዛዝ ሰጠ።
የፒሶ ምክንያት ደግሞ ፦
<<የመጀመሪያው እንዲሞት እስቀድሜ ስለፈረድኩበት ይሞታል
ሁለተኛው ወታደሩን እንዲገድል ትእዛዝ ከሰጠሁት በኃላ ትእዛዜን ባለመፈፀሙ ይሞታል ፣
ሦስተኛው የመቶ አለቃ ደግሞ ለወታደሩ መሞት ምክንያት ስለሆነ እሱም ይሞታል>> በማለት ፈረደ ።
#ግትርነት_ውስጥ_ምህረት_የለም!!!
እኔ ያልኩት ብቻ ይሆናል ከሚል ግትርነት ራቅ አንዳንዴ መሸነፍ መልካም ነውና!
ኢሳይያስ 53
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል?
² በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል፤ መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም።
³ የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።
⁴ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው።
⁵ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።
⁶ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።
⁷ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።
⁸ በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ?
⁹ ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ፤ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገኘበትም ነበር።
ጌታዬ ሆነ ደም ግባት አልባ፣
ጀርባዉ በጅራፍ ስለእኔ ደማ፣
የእኔን መገረፍ እርሱ ተገርፎ፣
ክብር አለበሰኝ እርሱ ተገፎ፣ ( ×፪ )
በሀሰት ሸንጎ ወጥመድ ተጠምዶ
ጌታ ተያዘ ሕይወቴን ፈቅዶ
ክፉዎች ቢያዩት እንደ ወንበዴ
ለእኔ ግን ሆኗል መውጫ መንገዴ ( ×፪ )
ታስረሃል ስለእኔ ኢየሱስ መድኅኔ
ታስረኃል ስለኔ ኢየሱስ መድኅኔአገቱኒ ከለባት ብዙኀን
ወአኀዙኒ ማኅበሮሙ ለእኩያን
አገቱኒ ከለባት ብዙኀን
ሲዘብቱበት ምራቅ ሲተፉ
የማይደፈር ደፍረው ሲዘልፉ
በከበቡት ፊት ቃል ከለከለ
እኔ እንድናገር እርሱ ዝም አለ ( ×፪ )
ታርደሃል ስለእኔ ኢየሱስ መድኅኔ
ታርደሃል ስለእኔ ኢየሱስ መድኅኔ
ቀነዉኒ እደውየ ወእገርየ
ወኈለቁ ኩሎ አዕጽምትየ
ቀነዉኒ እደውየ ወእገርየ
ሕይወት መንጭቷል ተወግቶ ጎኑ
ለከሳሾቹ ተርፏል ማዳኑ
እጅ እግሩን ሚስማር ሲቸነክርው
የሞትን እሾህ ከኔ ነቀለው ( ×፪ )
ተወጋ ስለእኔ ኢየሱስ መድኅኔ
ተወጋ ስለእኔ ኢየሱስ መድኅኔ
ወወደዩ ሐሞተ ውስተ መብልዕየ
ወአስተዩኒ ብሒዓ ለጽምዕየ
ወወደዩ ሐሞተ ውስተ መብልዕየ
እርቃኑን ሆኖ ፈተለው ልብሴን
አንዲሁ ወዶኝ ጠጣ ኾምጣጤ
በምሕረቱ ጠል ነፍሴን አርክቶ
አለመለመኝ እርሱ ተጠምቶ ( ×፪)
ተጠማ ስለእኔ ኢየሱስ መድኅኔ
ተጠማ ስለእኔ ኢየሱስ መድኅኔ
"ቤተክርስቲያንን የሚያስቀጥሉ ሦስት ሰንሰለቶች አሉ እነርሱም:---
ትዳር ፣ ምንኩስና እና ክህነት ናቸው።
እነዚህ እክል ስለገጠማቸው ነው ቤተክርስቲያን እየተቸገረች ያለቸው እንጂ ሌሎች ሰዎች ወይም አህዛብ ክፉ ስለሆኑ አይደለም። እነሱ ደግ የሚሆኑበት ዘመን ነገም እኔ አልጠብቅም ሰይጣን ባለበት መልካም ነገር አይመጣም።
እኛ ግን የጎደለን ይህ ነው፣ በተከበረ ትዳር ፣በተከበረ ምንኩስና እና በተከበረ ክህነት ቤተክርስቲያን ትቀጥላለች።
ምሳሌ እንዴት ካልን፦
የተከበረ ትዳር:- የተከበረ መነኩሴ ይወልዳል።
የተከበረ መነኩሴ:- የተከበረን ጵጵስናን ያመጣል።
የተከበረ ጳጳስ:- የተከበረን ክህነትን ይሾምና
የተከበረው ክህነት:- የተከበረ ትዳርን ባርኮ ያጋባል። የተከበረው ትዳር መልሶ እንደገና የተከበረ ካህንን ይወልዳል።
በዚህ ዑደት ነው ቤተክርስቲያን ተጠብቃ የምትኖረው። አሁን ግን ምንጩ ደፍርሷል። ለዚህም ሁላችንም መስተካከል አለብን። አሁን እኔ ሁሉም ሥርዓት እየፈረሰ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ! ተምረን ማግባትና፣ተምረን መመንኮስም ሆነ ክህነት መያዝን ማስቀጠል አለብን።"
ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
የስራ ማስታወቂያ ከጋዜጣ ፣ ከቲቪና ራዲዮ ፣ ከማስታወቂያ ቦርድ ፣ ከድህረ-ገፅና ከማህበራዊ ሚዲያና ከመሳሰሉት ቦታዎች በአንድ ቦታ ተሰብስበው ያግኙ::
#Group t.me//Ethio_Jobs2000
#የመዝናኛ ቻናል https://t.me/+UPjrnHF6QzI0ZmQ0
https://t.me/+h0l2XzeI8RQyODlk
For promotion ? @Share_Home
Last updated 1 month, 2 weeks ago
ከቅዳሜ በስተቀር በየዕለቱ፣ ከሰኞ እስከ ዓርብ ረፋድ ከ3:30 እስከ 5:00፣ እሁድ ከጠዋቱ 2:00 እስከ 4:00 በብስራት ኤፍ ኤም 101.1
Last updated 7 months, 4 weeks ago
Certified Professional Life Coaches
የቻናላችንን አነቃቂ ቪዲዮ መመልከት ለምትፈልጉ
https://www.youtube.com/@inspireethiopiamedia ? ይሄንን ሊንክ ይጫኑ
Last updated 9 months, 4 weeks ago