Unlock a World of Free Content: Books, Music, Videos & More Await!

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክርስቲናያን መንፈሳዊ ትምህርቶች እና ጽሁፎች ቻናል⛪️

Description
የዚህ ቻናል ዋና አላማ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መምህራን ትምህርቶችና ጽሑፎችን የሚናስተላልፍ የተዋህዶ ልጆች ቻናልነዉ
1ኛቆሮንቶስ1÷23፤እኛ፡ግን፡የተሰቀለውን፡ክርስቶስን፡እንሰብካለን፤ይህም፡ለአይሁድ፡ማሰናከያ፡ለአሕዛብም፡ሞኝነት፡ነው
24፤ለተጠሩት፡ግን፥አይሁድ፡ቢኾኑ፡የግሪክ፡ሰዎችም፡ቢኾኑ፥የእግዚአብሔር፡ኀይልና፡የእግዚአብሔር፡
ጥበብ፡የኾነው፡ክርስቶስ፡ነው።

ማነኛው አስተያየት
@geremch. @Aboyite.
Advertising
We recommend to visit

★ሰውን በማዝናናት የብቃት ማረጋገጫ ያለው ብቸኛው ቻናል ሁሌም Telegram ላይ በጥበብ ደምቀን እናሸበርቃለን

💌 Contact us, @Modenyazbot

»የተመረጡ እና ማንም ያላያቸው የአማሪኛ ቀልዶች እንዲሁም የሚያስደንቁ ስዕሎችንና ቪዲዮ ያገኛሉ።

° ° [ ሙድ እንያዝ በእኛ የአራዶች መዝናኛ ] ° °

° ° Creator @Teke_Man ° °

Last updated 2 weeks ago

☕ ስለ ኢትዮጲያ ቡና የሚወጡ ወቅታዊና ትክክለኛ የክለቡ መረጃዎች አዚህ ያገኛሉ!

➪የዝዉዉር ዜና
☞የአሰልጣኞች አስተያየት
➪ጎሎች እና ቪዲዮዎች
☞የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
➪ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት ከየስታድየሙ !

➡መወያያ ግሩፓችን @Ethiopia_coffee_Sc

📩ሀሳብ ወይም አስተያየት ካሎት
በዚህ 👉 @EthiopianCoffeeScBot ✍
BOT ማድረስ ይችላሉ!

Last updated 2 weeks, 1 day ago

እንኳን ወደ # ሉሲ የቴሌግራም ቻናል በደህና መጡ
#የሉሲ /LUCY DINKINESH E/ቤተሰብ ሰለሆኑ ደስብሎናል።

መረጃ መስጠት የምትፈልጉ በዚ አድርሱን 👉 @CACA77

# የኢትዬጵያዊነት የአሸናፊነት መገለጫ አርማችን ነው!
ነፃነታችንን 💪በፈርጣማው ጡንቻችን ይረጋገጣል
👉 ኢትዬጵያዊነት አርበኝነት የማንነት አርማች ነው
🙏🙏🙏

Last updated 1 month, 3 weeks ago

1 week, 4 days ago

*🌷የልደታ ማርያም እናቴ ነይ ከልጅሽ ጋር
ሁሌም በሕይወቴ ×(2)
❤️***

2 weeks, 3 days ago
2 weeks, 5 days ago

*ጴጥሮስ አሸናፊ

ክህደተ ይሁዳ ወምክረ አይሁድ ፤ የመልካም መዓዛና የእንባ ዕለት
                        ሰሙነ ሕማማት ዘረቡዕ

❖ ምክረ አይሁድ

ወእምዝ ተጋብኡ ሊቃነ ካህናት ወሊቃናት ሕዝብ ውስተ ዐጸደ ሊቀ ካህናት ዘስሙ ቀያፋ።  ወተማከሩ ከመ ኢየሱስሃ በሕብል የአኀዝዎ ወይቅትልዎ። ወይቤሉ ባሕቱ አኮኬ በበዓል ከመ ሀከከ ኢይኩን ውስተ ሕዝብ።
በዚያን ጊዜ የካህናት አለቆች የሕዝብም ሽማግሎች ቀያፋ በሚባለው ሊቀ ካህናቱ ግቢ ተሰበሰቡ፥ ኢየሱስንም በተንኰል ሊያስይዙት ሊገድሉትም ተማከሩ። የማቴዎስ ወንጌል 26:3-4

የአይሁድ ሊቃነ ካህናት እና ጸሐፍት ተሰብስበው ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው ምክር ያጠናቀቁበት ቀን በመሆኑ ዕለቱ ምክረ አይሁድ ተብሏል፡፡
አይሁድ በዚህ ምክራቸው ላይ በጣም ትልቅ ጭንቀት ነበር፡፡ ምክንያቱም ወቅቱ የፋሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት ቀን የተቃረበ በመሆኑ፣ ብዙው ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረኩ፣ ተአምራቱንም የሚያደንቁ ስለ ነበር ሁከት እንዳይፈጠር ነው፡፡
"ወእምዝ ሖረ አሐዱ እምዐሠርቱ ወክልኤቱ አርዳኢሁ ዘስሙ ይሁዳ አሰቆሮታዊ ኀበ ሊቃነ ካህናት ወይቤሎሙ ሚመጠነ ትሁበኒ ወአነ ለክሙ አገብኦ። ወወሀብዎ ሠላሳ ብሩረ ። ወእምአሜሃ ይፈቅድ  ይርከብ ሣኅተ ከመ ያግብኦ ።"
በዚህ ጭንቀት ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ፣ በመካከላቸው በመገኘት የምክራቸው ተባባሪ ሆኖ ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸውበጌታ መያዝ ተስማምተዋል።
[ማቴ. ፳፮፥፩፡፲፬ ፣ ማር. ፲፬፥፩፡፪ ቁ ፲.፲፩፣ ሉቃ. ፳፪፥ ፩፡፮]

❖ የመልካም መዓዛ ቀን

ወበጺሖ ኢየሱስ  ቢታንያ ቤተ ስምዖን ዘለምጽ መጽአት ኀቤሁ ብእሲት እንዘ ባቲ ብረሌ ዘምሉእ ዕፍረተ ውስቴቱ ዘብዙኅ ሤጡ ወሶጠት ዲበ ርእሱ ለኢየሱስ እንዘ ይረፍቅ ።
ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ (በለምጻሙ ሰምዖን) ቤት ተቀምጦ ሳለ፣ መላ ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት፣ /ባለሽቱዋ ማርያም/፤ “ ከእንግዲህ ወዲህ በኃጢአት ተበላሽቶ ይኖር የነበረውን ሕይወቴን እንደዚህ መልካም ሽቱ የሚያጣፍጥ፣ ኃጢአትን ይቅር የሚል አምላክ መጣ” ስትል ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ፣ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ፣ በአልባስጥሮስ ብልቃጥ የተሞላ ሽቱ ይዛ በመሔድ በጠጉሩ /በራሱ/ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባችው ዕለተ ረቡዕ የመዓዛ ቀን ተብሏል። ማቴ ፳፮፥፮-፯

❖ የእንባ ቀን

ይህም ይህቸው ባለሽቱዋ ሴት (ማርያም እንተ እፍረት) በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ፣ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት በዕንባዋ እግሩን አጥባዋለችና፣ በጠጉሯም በእንባዋ ያጠበችውን እግሩን አብሳዋለችና፡፡
[ማቴ.፳፮፥፮፡፲፫ ፣ ማር.፲፬፥፫፡፱፣ ዮሐ.፲፪፥፩፡፰]
ከዚህ ልንማር የሚገባው ነገር አለ፤ ይኸውም የራስን ኃጢአት በማሰብ ማልቀስና የተወደደ መሥዋዕት አድርጐ ለእግዚአብሔር ማቅረብን ነው፡፡ የማርያም እንተ ዕፍረትን ኃጢአት ይቅር ብሎ መብዓዋን የተቀበለ አምላክ ዛሬም በመካከላችን አለና፡፡
ማር ፲፬፥፱

እንበለ ደዌ ወሕማም ፤ እንበለ ጻማ ወድካም
   ዓመ ከመ ዮም ፤ ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ     
       እግዚአብሔር ለብርሃነ ትንሣኤሁ
           በፍስሓ ወበሰላም*

https://t.me/dmtse_tewaedo

2 months ago
ይህ ዘመን የተመቸው ለአቡነ ሩፋኤል ብቻ …

ይህ ዘመን የተመቸው ለአቡነ ሩፋኤል ብቻ ነው የተመቸው አይሰግዱ አይፆሙ እንዲ ደልበው ።

እኛማ መነኮሳት የአብነት ተማሪዎች  ምዕመናን እየታረድን እየተሰደድን  ነው ።

2 months ago

✥የዓብይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት✥

✥ቅድስት✥

በመባል የታወቃል ።

በዚህ ቀን እግዚያአብሔር አምላክ ቅዱስ ነውና እኛም ቅዱስ እንድንሆን ይፈልጋል ሁሉም የተቀደሰ ህይወት እንዲኖረው ይሻል። እኛም እርሱን መስለን በሮሜ 8÷28 የልጁን መልክ እንዲመስሉ አስቅድሞ ወሰነ ይላልና። እግዚያአብሔር አምላክ በቅድስና እንዲመራን የርሱ መልካም ፍቃድ ይህውንልን።

ሌላው ግን በዚህ ጊዜ ቅድስት ተብሎ በሚታወቀው ሳምንት ውስጥ የምናስበው ምንድነው? ስንል ሰንበትን ነው። እግዚያአብሔር አምላክ ሰንበትን እንደቀደሳት ሰንበትን ቀድሶ ለኛ ቅድስት አድርጎ እንደሰጠን የሚያሳይ ነው።

ሰንበት ስናከብር ሁለት ሰንበት እናከብራለን።
በኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን።
1ኛ ቀዳሚ ሰንበት
2ኛ ሰንበተ ክርስቲያን
የክርስቲያን ሰንበት ቀዳሚ ሰንበት የተባለቺው #ቅዳሜ ነው። ለምሳሌ ውዳሴ ማርያም በንደግምበት ሰዓት ውዳሴሃ ለእግዝተነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ ዘይትነበብ በዕለተ ቀዳሚት ሰንበት ። ይላል።

የቀደመች ሰንበት የአይውድ ሰንበት ወይም በብሉይ ዘመን የምትከበር ሰንበት ሁሉም ሰው ሊያከብራት የምትገባ ሰንበት። ዘፍጥረት 2÷3 እግዚያአብሔር አምላክ ሁሉን በስድስት ቀን ከፈጠረ በዋላ በሰባተኛው ቀን አረፈ የሰባተኛው ቀንም ቀደሰው።
አከበረው ሰንበት አለው። ዘጸአት 20 ላይ ስንመለከት ከአስርቱ ትዛዛት አንዱ ሰንበቴን አክብር ነው። ወይም ሰንበትን አክብር ነው።

እዚህ ሰንበት ቅዳሜ ላይ ጌታ ከፈጠረው ፍጥረት ሁሉ አረፈ ። ለምን አረፈ?
ደክሞት በፍፁም አይስማማውም።
ለስም አጠራሩ ክብር ምስጋና ይግባው።
ከምንሰራው ስራ አርፈን እግዚያአብሔርን እናመሰግነው ዘንድ ነው።
ስለዚህ ቅዳሜ የስጋ እረፍት ነው።

2ኛ ሰንበት እውድ ነው።
እውድን ሰንበት እንደውም የቀኖች ሁሉ ንግስት ነው የሚላት አትናቲዮስ ሲጠራት ። የእለታት ሁሉ ንግስት አባይ ታላቅ እለት ይላታል።

ለምን ?
በዚህ ቀን ደሞ ነብሳችን አርፋለች።
እንዴት ? አለምን በስድስተኛው  ቀን ፈጥሮ በሰባተኛው ቀን ያረፈው የሁሉ ፈጣሪ እግዚያአብሔር አለምን ለማዳን በጀመሪያውስንመለከት ትምህርት ዘወረደ እንደተመለከትነው ወርዶ ወደዚህ መቶ ነብሳችን በህለተ ሰንበት እውድ አሳረፋት። ማቴ 28÷1 ዮሐ 20÷1  በመቃብሩ ስፍራ በህለተ ሰንበት ወይም ደግሞ የሰንበቱ መጨረሻ በመጀመሪያው የሰንበት ቀንእነሆ ወደ መቃብሩ ስፍራ ኤዶ መቃብሩ ግን ባዶ ነበር። ነብሳችን ያረፈችበት ሰንበት እለተ ሰንበት እውድ ነበር ። እውድ ደግሞ ሰንበት ተብሎ ይጠራል።

1 ቀዳሚት ሰንበት ።
2 እውድ ሰንበት ።
ይኤንን እነሆ ሰንበታቴን አክብሩ ብሎ እንደተናገረ እነዚህን እናከብራለን ።

ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በፍጥሞ ደሴት ሳለው ይላል ። ራይ 1÷10 ላይ በጌታ ቀን በመንፈስ ነበርኹ አለ። የጌታ ቀን የሚላት እውድነው። ሐዋሪያት የጌታ ቀን ብለው ይጠርዋታል ።
ቅዳሜ ሥጋችን ያረፈበት የሚያርፍበት
እውድ ደግሞ ነፍሳችን የሚያርፍበት ልዩ ቀን ነው።  ቅድስት ሲል እግዚያአብሔር ቅዳሜን እግዚያአብሔር እውድን ለውላችን ቅድሶ ሰጠን ።

በዚህ ቀን አርፈን የታመመን እንድንጠይቅ ድውያን እድንጠይቅ እግዚያአብሔር ይፈልጋል።

ለስጋ ብቻ መሮጥ አይደለም ወገኖቼ ለዓለማዊ ነገር ብቻ መክነፍ አይደለም።
እግዚያአብሔር ዛሬ ይጠይቀናል ።
በዚህ ቀን ችግረኞችን እንድንጠይቅ እግዚያአብሔር ይሻል።

የህለተ ሰንበ በረከት እረድኤት ከኛጋር ይኑር።

ሼር በማድረግ ቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ።

👇👇👇👇👇👇👇
╔═✟✞════🇨🇬    ════✟✞═╗
@dmse_tewado                       @orthodoxswi_eywet
╚═✟✞════🇨🇬    ════✟✞═╝

2 months, 1 week ago

ዘወረደ /ዘመነ አዳም/

የዐቢይ ጾም የመጀመሪያ ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡ ዘወረደ ማለት፣ ከላይ የመጣ፣ የወረደ ማለት ነው፡፡ ይህም የአምላካችን ሰው መሆን ያመለክታል፡፡ ከሰማይ ከወረደው በቀር ወደሰማይ የወጣ የለም ካለው ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ቃል በመነሳት ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በዚህ ዕለት ምስባክ “ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ በቃሉ” በማለት በጾመ ድጓው መጀመሪያ ላይ ገልጾት ይገኛል፡፡
አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አይሁድ ሰቀሉት፣ የሰማይን ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም አላወቁም ብሎ ተናግሮ ነበር፡፡ ይህም ድርሰት በቤተ ክርስቲያናችን የጾም መጀመሪያ የሆነው ዕለተ ሰንበት ዋዜማ፣ መግቢያ፣ /መሐትው/ ሆኖ ከዋዜማ በፊት ምንጊዜም በየዓመቱ ይቆማል፡፡ ይዘመራል፡፡ ይመሰገናል ማለት ነው፡፡
ስለዚህ የሳምንቱ ስያሜ ከዚህ የተወሰደ ነው፡፡ እንዲሁም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራውን የጀመረው፤ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ሰው በመሆን ፣ በዮርዳኖስ ተጠምቆ በማስተማር እንደሆነ ሁሉ የመጀሪያው ሳምንት ዘወረደ ይባላል፡፡
በዚህ ሳምንት በተለይም እሑድና ሰኞ የሚነገሩት ውዳሴያት ከመጻሕፍተ ኦሪትና ነቢያት የተወሰዱ ናቸው፡፡ ሁለተኛም ሙሴኒ በመባል ይታወቃል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ አዳምን ለማዳን ከሰማይ መውረዱንና በመስቀል መሰቀሉን ስለሚያወሳ ነው፡፡
የቤተ ክርስቲያናችን ታሉቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ፣ በዘወረደ ጾመ ድጓው ሰንበት ለሰው ልጆች ብቻ ሳይሆን፣ ሕይወት ላለው ነገር ሁሉ ጸጥታና ሰላም የሰፈነባት የዕረፍት ቀን ስለመሆኗ “አዘዞ እግዚአብሔር ለሙሴ ወይቤሎ ሰብዕከ ወላህምከ ወኲሉ ቤትከ ያዕርፍ በሰንበት” ዘፀ.20፥10፣23፣12፣ ጾመ ድጓ፣ እግዚአብሔር ሙሴን ሕዝብህ የከብትህ መንጋህ ቤተሰብህ ሀሉ በሰንበት ቀን ከድካማቸው ይረፉ በማለት አዘዘው ይላል፡፡ በዚህም ዘመነ ጾም፣ ወይም ጾመ ሙሴ ይባላል፡፡
በጾመ ድጓው ዘወረደ እየተባለ የሚታወቀው፣ በጾመ አርባው ወቅት በተለይም በመጀመሪያው ሳምንት የሚገኘው ያሬዳዊ ድርሰት በነግህ በሠለስት፣ በቀትርና በሠርክ እንዲሁም ቅዳሜና እሑድ በሌሊት የሚዘመር ነው፡፡ በውስጡም የያዘው ፍሬ አሳብ፣ የጾምን፣ የጸሎትን፣ የምጽዋትንና የፍቅርን ጠቃሚነት አጉልቶ የሚያስተምር ነው፡፡
በዚህ በጾም ወቅት በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት በአብዛኛው ከቅዱስ ያሬድ ድርሰቶች ውስጥ የሚዘመረው ምዕራፍ የተባለው ነው፡፡ ምዕራፍ የተባለበት ምክንያትም በየመዝሙራቱ መሀል ሃሌታና ድጓ እያስገባ ለመዝሙሩ ማረፊያ ስላበጀለት በዚህ ምክንያት ምዕራፍ የሚል ስያሜ ሊያገኝ ችሏል፡፡ ይህ የዜማ መጽሐፍ በሁለት ታላላቅ ክፍሎች ይከፈላል፡፡ ይኸውም የዘወትር ምዕራፍና የጾም ምዕራፍ በመባል ይታወቃል፡፡የዘውትር ምዕራፍ የሚባለው በዓመቱ ውስጥ ባሉት ቀናት ውስጥ ሳምንታትና በዓላት ሁልጊዜ በአገልግሎት ላይ የሚውል ሲሆን፣ የጾም ምዕራፍ የሚባለው ደግሞ በጾመ አርባ ብቻ ለአገልግሎት የሚውል ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በዐሥሩ ምህላት አርዕስተ ምህላ በዚሁ ክፍል ይካተታል፡፡ የምዕራፍ ቅንብር ከመዝሙረ ዳዊት፣ ከድጓና ከጾመ ድጓ ጋር የተቀናጀ ነው፡፡ የትምህርት አሰጣጡም እንደ ድጓው ወይም እንደ ዝማሬ መዋሥዕቱ መጽሐፍ ተዘርግቶ ሳይሆን በቃል የሚጠናና የሚወሰን ነው፡፡ ስለሆነም ምዕራፍን ለመማር 150 መዝሙረ ዳዊትን፣ ከነቢያት 15 ምዕራፎችንና 5 መኃልያተ ሰሎሞንን በቃል ሸምድዶ መያዝ ይጠበቅበታል፡፡ ወይም ግድ ነው፡፡
ጾምን መጾም የፈቃድ ብቻ ሳይሆን የትእዛዝም ነው፡፡ በዘመነ ብሉይ ነቢዩ ኢዩኤል “ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ” ጾምን ያዙ አጽኑ ምሕላንም ዐውጁ ሸማግሌዎቹን ከፈጣሪያችን ቤት ሰብስባችሁ በአንድነት ሁናችሁ ወደ እግዚአብሔር ጩሁ /ለምኑ/ ብሏል፡፡ ኢዮ.ምዕ.1፥11፣ 2፣12፣15-16 ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ወኲኑ ላዕካነ፣ ለእግዚአብሔር በጾም ወበንጽሕ፡፡ በጾም፣ በንጽሐና ተወስናችሁ እግዚአብሔርን አገልግሉ ብሏል 2ቆሮ.6፥4-6፡፡
ጾም ከሌለ ወይም ተገቢ ካልሆነ ጌታችን በምትጾሙበት ጊዜ እንደ ግብዞች አትሁኑ ስለ ጽድቅ የሚራቡ የሚጠሙ ንዑዳን ክብራን ናቸው ለምን አለ? ማቴ.5፥፣6፣16፡፡ ነቢዩ ዳዊትም ሰውነቴን በጾም አሳመምኳት በቀጠና፣ በሰልት አደከምኳት ለምን አለ መዝ.34፥68፣ ት.ዳን. 9፥3-4፣ 14፥5
ነብዩ ሚኪያስ ሐዋርያት ሙሸራውን ከነሱ ለይተው የሚወስዱበት ጊዜ ይመጣል ያን ጊዜ ይጾማሉ ያለውን የጌታን ቃል መሠረት በማድረግ ክርስቶስ በሞት ከተለያቸው በኋላ ጾመዋል፡፡ ጾምንም ሠርተዋል የሐዋ.ሥራ 13፥3፡፡ ሠለስቱ ምዕትም ሐዋርያት የጾሙትንና እንዲጾም የወሰኑትን መጾም ይገባል ብለው ቤተ ክርስቲያን የተቀበለቻቸውን አጽዋማት እንዲጾሙ መወሰናቸው ይህን የጌታ ቃል መሠረት በማድረግ ስለሆነ፣ የትእዛዝ መሆኑን ተገንዝበን መጾም አለብን፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ሠራዔ ሕግ እንደመሆኑ አርባ ቀን አርቦ ሌሊት ጾመ እንጂ እርሱ ሳይጾም ጾሙ አላለንም ማቴ.4፥2፡፡

ሠናይ መዋዕለ ጾም፡፡

የተሣተውን ፤ የተረሳው፤ የተገደፈውን፤ የነጠፈውን በቀና መንፈስ አቃንታቹ አንብቡት     
    
❤️ስለ  ማይነገር ስጦታው   እግዚአብሔር ይመስገን ❤️

ለመቀላቀል   👇

https://t.me/natanimube
https://t.me/dmse_tewado
https://t.me/maetebe_kbrenew
https://t.me/orthodoxswi_eywet
https://t.me/ortodoksawzmare
https://t.me/zmaredawt_zeortodocs

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን

2 months, 1 week ago

🤑💶 𝗖𝗶𝘁𝘆 𝗙𝗼𝗿𝗲𝘅 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 🤑
መማር የምትፈልጉ አንድ የሚገርም የ Forex ቻናል ያውቃሉ

@City_Forex_Ethiopia ይባላል ።
ተመዝገባችሁ መማር  የምትፈልጉ
አናግሯቸው እስከ 40% የሚደርስ  ቅናሽ አድርገዋል
☎️   09 77 33 85 86       🇪🇹
☎️   09 77 33 85 86       🇪🇹

ታዲያ ምን ይጠብቃሉ ቶሎ ተመዝግበው ይማሩ ! 💸

2 months, 1 week ago
2 months, 1 week ago

እንኳን ለአብይ ጾም በሰላም በጤና አደረሳቹ አደረስን

የመጀመሪያ እሁድ ዘወርድ ይባላል
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማያት ሰማይ ወርዱ እኛን ልያድን የመጣበት የተሰየመ ሳምንት ነው ሌላኛው ጸመ ህርቃል ይባላል

መልካም ጾም ይሁንልን ይሁንላቹ አሜን ሀገራችን ሰላም ያደረግንል

https://t.me/Egizhaberanidinew

Telegram

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክርስቲናያን መንፈሳዊ ትምህርቶች እና ጽሁፎች ቻናል⛪️

የዚህ ቻናል ዋና አላማ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መምህራን ትምህርቶችና ጽሑፎችን የሚናስተላልፍ የተዋህዶ ልጆች ቻናልነዉ 1ኛቆሮንቶስ1÷23፤እኛ፡ግን፡የተሰቀለውን፡ክርስቶስን፡እንሰብካለን፤ይህም፡ለአይሁድ፡ማሰናከያ፡ለአሕዛብም፡ሞኝነት፡ነው 24፤ለተጠሩት፡ግን፥አይሁድ፡ቢኾኑ፡የግሪክ፡ሰዎችም፡ቢኾኑ፥የእግዚአብሔር፡ኀይልና፡የእግዚአብሔር፡ ጥበብ፡የኾነው፡ክርስቶስ፡ነው። ማነኛው አስተያየት @geremch. @Aboyite.

እንኳን ለአብይ ጾም በሰላም በጤና አደረሳቹ አደረስን
2 months, 2 weeks ago

🤑💶 𝗖𝗶𝘁𝘆 𝗙𝗼𝗿𝗲𝘅 𝗘𝘁𝗵𝗶𝗼𝗽𝗶𝗮 🤑
መማር የምትፈልጉ አንድ የሚገርም የ Forex ቻናል ያውቃሉ

@City_Forex_Ethiopia ይባላል ።
ተመዝገባችሁ መማር  የምትፈልጉ
አናግሯቸው እስከ 40% የሚደርስ  ቅናሽ አድርገዋል
☎️   09 77 33 85 86       🇪🇹
☎️   09 77 33 85 86       🇪🇹

ታዲያ ምን ይጠብቃሉ ቶሎ ተመዝግበው ይማሩ ! 💸

We recommend to visit

★ሰውን በማዝናናት የብቃት ማረጋገጫ ያለው ብቸኛው ቻናል ሁሌም Telegram ላይ በጥበብ ደምቀን እናሸበርቃለን

💌 Contact us, @Modenyazbot

»የተመረጡ እና ማንም ያላያቸው የአማሪኛ ቀልዶች እንዲሁም የሚያስደንቁ ስዕሎችንና ቪዲዮ ያገኛሉ።

° ° [ ሙድ እንያዝ በእኛ የአራዶች መዝናኛ ] ° °

° ° Creator @Teke_Man ° °

Last updated 2 weeks ago

☕ ስለ ኢትዮጲያ ቡና የሚወጡ ወቅታዊና ትክክለኛ የክለቡ መረጃዎች አዚህ ያገኛሉ!

➪የዝዉዉር ዜና
☞የአሰልጣኞች አስተያየት
➪ጎሎች እና ቪዲዮዎች
☞የተጨዋቾች የህይወት ታሪክ
➪ጨዋታዎችን በቀጥታ ስርጭት ከየስታድየሙ !

➡መወያያ ግሩፓችን @Ethiopia_coffee_Sc

📩ሀሳብ ወይም አስተያየት ካሎት
በዚህ 👉 @EthiopianCoffeeScBot ✍
BOT ማድረስ ይችላሉ!

Last updated 2 weeks, 1 day ago

እንኳን ወደ # ሉሲ የቴሌግራም ቻናል በደህና መጡ
#የሉሲ /LUCY DINKINESH E/ቤተሰብ ሰለሆኑ ደስብሎናል።

መረጃ መስጠት የምትፈልጉ በዚ አድርሱን 👉 @CACA77

# የኢትዬጵያዊነት የአሸናፊነት መገለጫ አርማችን ነው!
ነፃነታችንን 💪በፈርጣማው ጡንቻችን ይረጋገጣል
👉 ኢትዬጵያዊነት አርበኝነት የማንነት አርማች ነው
🙏🙏🙏

Last updated 1 month, 3 weeks ago