Federal Justice and Law Institute

Description
We recommend to visit

꧁❀✰﷽✰❀꧂
In The Name Of God

تبلیغات? :

https://t.me/+TJeRqfNn3Y4_fteA

Last updated 2 months, 2 weeks ago

☑️ Collection of MTProto Proxies


? تبليغات بنرى
@Pink_Bad

? تبليغات اسپانسری
@Pink_Pad


پینک پروکسی قدیمی ترین تیم پروکسی ایران

Last updated 2 months ago

Official Channel for HA Tunnel - www.hatunnel.com

Last updated 6 months ago

2 weeks, 3 days ago
Federal Justice and Law Institute
2 weeks, 3 days ago
Federal Justice and Law Institute
2 weeks, 3 days ago
Federal Justice and Law Institute
3 months ago

via:- FDRE Ministry of Justice/ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ፍትሕ ሚኒስቴር

Federal Justice and Law institute 2

3 months ago

በሰው አካልና ጤና ላይ ጉዳት በማድረስ የሚፈፀሙ ወንጀሎች
መግቢያ
ማንኛውም ሰው የማይደፈርና የማይገሰስ በህይወት የመኖር፣ የአካል ደህንነትና የነፃነት ሰብአዊ መብት አለው። ሰብአዊ መብቶች የሰው ልጅ ሰው በመሆኑ ብቻ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የሚያገኛቸው መብቶች ናቸው። በመሆኑም የሰው ልጆች በህይወት የመኖር መብት፣ የአካል ደህንነታቸው የመጠበቅ መብት፣ የነፃነት መብት፣ ከኢሰብዓዊ አያያዝ የመጠበቅ እና በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ-መንግስት በምዕራፍ ሶስት ላይ የተዘረዘሩት ሰብዓዊ መብቶች አሏቸው።
በህገ መንግስቱ የተዘረዘሩት መሰረታዊ የመብቶችና የነፃነቶች ድንጋጌዎች ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕግጋት፣ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ስምምነቶችና ዓለም አቀፍ ሠነዶች መርሆች ጋር በተጣጣመ መንገድ ይተረጎማሉ (ሕገ-መንግስት አንቀፅ 13(2))። እነዚህ ሰብዓዊ መብቶች በህገ መንግስቱ እውቅና ሽፋን ከማግኘታቸው በተጨማሪ በወንጀል ህጋችን ውስጥ እነዚህን ሰብዓዊ መብቶች በመጣስ ወይም ባለማክበር የሚፈፀሙ ወንጀል የሆኑትን ድርጊቶች ወይም ተግባራት እና የሚያስከትሉት ቅጣት በስፋት እና በዝርዝር ተደንግጓል። በመሆኑም ሰዎች በየእለት ተእለት እንቅስቃሴያቸው እነዚህን ድንጋጌዎች ላለመተላለፍ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል። በዚህ አጭር የንቃተ-ህግ ፅሁፍ በሰው አካል እና ጤና ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች እና ስለሚያስከትሉት የወንጀል ተጠያቂነትና ቅጣት፣ እንዳስሳለን።
1. በሰው አካልና ጤና ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች
በአካል ላይ ጉዳት የማድረስ ተግባር በወንጀልም ሆነ በፍትሐ ብሔር ተጠያቂነትን ሊያስከትል የሚችል ተግባር ነው። በህገ-መንግስቱ አንቀፅ 16 ላይ እንደተደነገገው ማንኛውም ሰው በአካሉ ላይ ጉዳት እንዳይደርስበት የመጠበቅ መብት አለው። የወንጀል ሕጉም ይሄንን መሰረታዊ የሰው ልጆች መብት ጥበቃ ለማድረግ የወንጀል ድንጋጌዎችን አስቀምጧል። ለወንጀል ድንጋጌዎቹ በመርህነት የተቀመጠው የወንጀል ሕጉ አንቀፅ 553 እንደሚያስረዳው ማንም ሰው አስቦ ወይም በቸልተኝነት በሌላው ሰው አካል፣ አዕምሮ ወይም ጤና ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ በወንጀል ተጠያቂ ይሆናል። የደረሰው የአካል ጉዳት መጠን (ክብደትና ቅለት) የሚረጋገጠው በሕክምና ማስረጃ ሲሆን ይህም የሆነበት ምክንያት ማስረጃ እንደመሆኑ መጠን በገለልተኛ እና ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መረጋገጥ ስለሚገባው ነው።
በወንጀል ህጉ ውስጥ ሆን ተብሎ የሚፈፀም በሰው አካል ላይ ጉዳት የማድረስ ወንጀል ከባድ በሆነ ጊዜ በአንቀፅ 555፣ ቀላል ጉዳት ሲሆን በአንቀፅ 556 እና ለእጅ እልፊት በአንቀፅ 560 ወይም ከዚህ ውጪ የሆነ በደንብ መተላለፍ ደረጃ አንቀፅ 840 ሊታይ የሚችል ሲሆን በቸልተኝነት የሚፈፀም በአካል ላይ ጉዳት የማድረስ ወንጀል ደግሞ ለብቻ በአንቀፅ 559 ላይ ተመልክቶ እናገኘዋለን።
ታስቦ ስለሚፈፀም ከባድ የአካል ጉዳት የወንጀል ህጉ እንደሚከተለው ይደነግጋል፡- ማንም ሰው አስቦ፡-
ሀ/ የተጎጂውን ሕይወት በሚያሰጋ ወይም በሰውነቱም ሆነ በአዕምሮው ላይ ለዘወትር ጠንቅ በሚያተርፍ ሁኔታ በሌላ ሰው ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ወይም
ለ/ የሌላ ሰውን አካል ወይም አስፈላጊ ከሆኑት ብልቶቹ ወይም ሕዋሳቶቹ አንዱን ያጎደለ፣ እንዳይገለግሉ ያደረገ ወይም በሚያሰቅቅና ጉልህ ሆኖ በሚታይ ሁኔታ መልኩን ያበላሸ እንደሆነ ወይም
ሐ/ በማናቸውም ሌላ መንገድ ከባድ የሆነ ጉዳትን ወይም በሽታን በሌላ ሰው ላይ ያደረሰ እንደሆነ፤ እንደነገሩ ሁኔታና ከባድነት ከ15 አመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ወይም ከአንድ ዓመት በማያንስ ቀላል እስራት ይቀጣል። በከባድ የአካል ጉዳት ማድረስ ከሚያስጠይቁ ድርጊቶች በምሳሌነት ለማየት ያክል፡- የጥርስ ማውለቅ፣ አይን ማጥፋት፣ የእግር ወይም እጅ ስብራትና እንዳያገለግሉ ማድረግ፣ በፈላ ውሀ ወይም በአሲድ ፊት ላይ ጉዳት በማድረስ መልክ የሚያጠፋ ወይም የሚያሰቅቅ ጠባሳ እንዲኖር ማድረግ እና የመሳሰሉት በአካል ላይ የሚፈፀሙ ከባድ የአካል ጉዳቶችን ያካትታል።
በሌላ በኩል ጉዳት አድራሹ ድርጊቱን የፈፀመው ለመግደል አስቦ ከነበረ ምንም እንኳን የደረሰው ጉዳት አካል ላይ ቢሆንም የአፈፃፀሙን ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት በግድያ ሙከራ ሊጠየቅ ይችላል። ይህ ማለት ሙከራ የሚያስቀጣው የተሞከረው ወንጀል ሊያስቀጣ በሚችለው ልክ በመሆኑ (አንቀፅ 27(3)) ከተራ ግድያ እስከ ከባድ ግድያ ባሉት የቅጣት ዓይነቶች ውስጥ ከ5 ዓመት ፅኑ እስራት ጀምሮ እስከ የዕድሜ ልክ ወይም በሞት ሊያስቀጣ ይችላል ማለት ነው።
በወንጀል ህጉ አንቀፅ 556 ስር እንደተደነገገው በአንቀፅ 555 ከተመለከቱት ሁኔታዎች ውጪ አስቦ በሰው አካል ላይ ጉዳት ያደረሰ ሰው ታስቦ በሚፈፀም ቀላል የአካል ጉዳት ወንጀል የግል አቤቱታ ሲቀርብበት ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም መቀጮ ይቀጣል። ጉዳቱ ከዚህ ከፍ ያለ ክብደት ካለው በወንጀል ክስ አቅራቢነት የሚያስቀጣ ሆኖ ከ6 ወር እስከ 3 ዓመት ለመድረስ በሚችል ቀላል እስራት የሚያስቀጣው፡-
1. ጥፋተኛው ጉዳቱን ያደረሰው በመርዝ ወይም በገዳይ መሳሪያ ወይም የአካል ጉዳት ለማድረስ በሚችል በማናቸውም ሌላ መሳሪያ በመጠቀም እንደሆነ፤
2. ጥፋተኛው የሙያ ወይም ሌላ ግዴታን በመተላለፍ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ፤
3. ተጎጂው ደካማ፣ በሽተኛ ወይም ራሱን ለመከላከል የማይችል እንደሆነ ነው።
በሌላ በኩል በአካል ላይ ጉዳት ማድረስ በቸልተኝነትም ሊፈፀም ይችላል። ይህ በሚሆንበት ጊዜ የወንጀል ህጉ አንቀፅ 559 ተግባራዊ ይሆናል ማለት ነው። በዚህም መሰረት ማንም ሰው በቸልተኛነት በሌላ ሰው አካል ወይም ጤንነት ላይ ቀላል ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ከ6 ወር በማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም ከብር 1 ሺ በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል። የደረሰው ጉዳት በአንቀፅ 555 የተመለከተው ዓይነት (ከባድ የአካል ጉዳት) ከሆነ ወይም ጉዳት አድራሹ የሌላን ሰው አካል ወይም ጤንነት የመጠበቅ የሙያ ወይም ሌላ ግዴታ ያለበት እንደ ህክምና ባለሞያ ወይም አሽከርካሪ ያለ ሰው ከሆነ ቅጣቱ ከ6 ወር የማያንስ ቀላል እስራትና ከ1 ሺ ብር የማያንስ መቀጮ ይሆናል። ከዚህ ጋር በተያያዘ በአንድ ድርጊት (ለምሳሌ በመኪና አደጋ) ከአንድ በላይ በሆኑ ሰዎች ላይ ጉዳት ሊደርስ የሚችልበት ዕድል ሰፊ ነው። እንዲህ ዓይነት ሁኔታ በሚያጋጥምበት ጊዜ ጉዳት አድራሹ በተደራራቢ ክስ ሊጠየቅ እንደሚችል በወንጀል ሕጉ አንቀፅ 60(ሐ) ስር ተደንግጓል።
የወንጀል ህጉ አንቀፅ 560 ደግሞ እንደነገሩ አካባቢ ሁኔታ እስከ 3 ወር ቀላል እስራት ሊያስቀጡ የሚችሉ የአካል ጉዳት ወይም በጤንነት ላይ ጉድለት ሳያደርስ በሌላ ሰው ላይ የሚፈፀምን የእጅ እልፊት ወይም የመጋፋት ድርጊትን ይመለከታል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሆኖ በሌላ ሰው ላይ ጉዳት ያደረሰ ሰው ቅጣቱ ሊቀልለት የሚችልበት አጋጣሚ ይኖራል። በዚህም መሰረት የአስገዳጅ ሁኔታን ወሰን በማለፍ ጉዳት ቢደርስ፣ ከፍ ባለ ደም በሚያፈላ መቀስቀስ ምክንያት ወይም ባልጠበቀውና ህሊናን በሚያውክ ድንገተኛ ምክንያት ተነሳስቶ ጉዳት ማድረስ፣ በተጎጂው ጠያቂነት መሰረት የደረሰ ጉዳት ሲሆን ቅጣቱ ከ4 ዓመት የማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም ከብር 4 ሺ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ የሚቀጣ ይሆናል (የወንጀል ሕግ አንቀፅ 557)። ከዚህም በተጨማሪ ቀላል የአካል ጉዳት ለማድረስ አስቦ ከባድ የአካል ጉዳት ያደረሰ ሰው ከ6 ወር እስከ 3 ዓመት በሚደረስ ቀላል እስራት የሚቀጣ ይሆናል (የወንጀል ሕግ አንቀፅ 558)።

3 months ago

በሰው አካልና ጤና ላይ ጉዳት በማድረስ የሚፈፀሙ ወንጀሎች
መግቢያ
ማንኛውም ሰው የማይደፈርና የማይገሰስ በህይወት የመኖር፣ የአካል ደህንነትና የነፃነት ሰብአዊ መብት አለው። ሰብአዊ መብቶች የሰው ልጅ ሰው በመሆኑ ብቻ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የሚያገኛቸው መብቶች ናቸው። በመሆኑም የሰው ልጆች በህይወት የመኖር መብት፣ የአካል ደህንነታቸው የመጠበቅ መብት፣ የነፃነት መብት፣ ከኢሰብዓዊ አያያዝ የመጠበቅ እና በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ-መንግስት በምዕራፍ ሶስት ላይ የተዘረዘሩት ሰብዓዊ መብቶች አሏቸው።
በህገ መንግስቱ የተዘረዘሩት መሰረታዊ የመብቶችና የነፃነቶች ድንጋጌዎች ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ሕግጋት፣ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ስምምነቶችና ዓለም አቀፍ ሠነዶች መርሆች ጋር በተጣጣመ መንገድ ይተረጎማሉ (ሕገ-መንግስት አንቀፅ 13(2))። እነዚህ ሰብዓዊ መብቶች በህገ መንግስቱ እውቅና ሽፋን ከማግኘታቸው በተጨማሪ በወንጀል ህጋችን ውስጥ እነዚህን ሰብዓዊ መብቶች በመጣስ ወይም ባለማክበር የሚፈፀሙ ወንጀል የሆኑትን ድርጊቶች ወይም ተግባራት እና የሚያስከትሉት ቅጣት በስፋት እና በዝርዝር ተደንግጓል። በመሆኑም ሰዎች በየእለት ተእለት እንቅስቃሴያቸው እነዚህን ድንጋጌዎች ላለመተላለፍ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል። በዚህ አጭር የንቃተ-ህግ ፅሁፍ በሰው አካል እና ጤና ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች እና ስለሚያስከትሉት የወንጀል ተጠያቂነትና ቅጣት፣ እንዳስሳለን።
1. በሰው አካልና ጤና ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች
በአካል ላይ ጉዳት የማድረስ ተግባር በወንጀልም ሆነ በፍትሐ ብሔር ተጠያቂነትን ሊያስከትል የሚችል ተግባር ነው። በህገ-መንግስቱ አንቀፅ 16 ላይ እንደተደነገገው ማንኛውም ሰው በአካሉ ላይ ጉዳት እንዳይደርስበት የመጠበቅ መብት አለው። የወንጀል ሕጉም ይሄንን መሰረታዊ የሰው ልጆች መብት ጥበቃ ለማድረግ የወንጀል ድንጋጌዎችን አስቀምጧል። ለወንጀል ድንጋጌዎቹ በመርህነት የተቀመጠው የወንጀል ሕጉ አንቀፅ 553 እንደሚያስረዳው ማንም ሰው አስቦ ወይም በቸልተኝነት በሌላው ሰው አካል፣ አዕምሮ ወይም ጤና ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ በወንጀል ተጠያቂ ይሆናል። የደረሰው የአካል ጉዳት መጠን (ክብደትና ቅለት) የሚረጋገጠው በሕክምና ማስረጃ ሲሆን ይህም የሆነበት ምክንያት ማስረጃ እንደመሆኑ መጠን በገለልተኛ እና ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ መረጋገጥ ስለሚገባው ነው።
በወንጀል ህጉ ውስጥ ሆን ተብሎ የሚፈፀም በሰው አካል ላይ ጉዳት የማድረስ ወንጀል ከባድ በሆነ ጊዜ በአንቀፅ 555፣ ቀላል ጉዳት ሲሆን በአንቀፅ 556 እና ለእጅ እልፊት በአንቀፅ 560 ወይም ከዚህ ውጪ የሆነ በደንብ መተላለፍ ደረጃ አንቀፅ 840 ሊታይ የሚችል ሲሆን በቸልተኝነት የሚፈፀም በአካል ላይ ጉዳት የማድረስ ወንጀል ደግሞ ለብቻ በአንቀፅ 559 ላይ ተመልክቶ እናገኘዋለን።
ታስቦ ስለሚፈፀም ከባድ የአካል ጉዳት የወንጀል ህጉ እንደሚከተለው ይደነግጋል፡- ማንም ሰው አስቦ፡-
ሀ/ የተጎጂውን ሕይወት በሚያሰጋ ወይም በሰውነቱም ሆነ በአዕምሮው ላይ ለዘወትር ጠንቅ በሚያተርፍ ሁኔታ በሌላ ሰው ላይ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ወይም
ለ/ የሌላ ሰውን አካል ወይም አስፈላጊ ከሆኑት ብልቶቹ ወይም ሕዋሳቶቹ አንዱን ያጎደለ፣ እንዳይገለግሉ ያደረገ ወይም በሚያሰቅቅና ጉልህ ሆኖ በሚታይ ሁኔታ መልኩን ያበላሸ እንደሆነ ወይም
ሐ/ በማናቸውም ሌላ መንገድ ከባድ የሆነ ጉዳትን ወይም በሽታን በሌላ ሰው ላይ ያደረሰ እንደሆነ፤ እንደነገሩ ሁኔታና ከባድነት ከ15 አመት በማይበልጥ ፅኑ እስራት ወይም ከአንድ ዓመት በማያንስ ቀላል እስራት ይቀጣል። በከባድ የአካል ጉዳት ማድረስ ከሚያስጠይቁ ድርጊቶች በምሳሌነት ለማየት ያክል፡- የጥርስ ማውለቅ፣ አይን ማጥፋት፣ የእግር ወይም እጅ ስብራትና እንዳያገለግሉ ማድረግ፣ በፈላ ውሀ ወይም በአሲድ ፊት ላይ ጉዳት በማድረስ መልክ የሚያጠፋ ወይም የሚያሰቅቅ ጠባሳ እንዲኖር ማድረግ እና የመሳሰሉት በአካል ላይ የሚፈፀሙ ከባድ የአካል ጉዳቶችን ያካትታል።
በሌላ በኩል ጉዳት አድራሹ ድርጊቱን የፈፀመው ለመግደል አስቦ ከነበረ ምንም እንኳን የደረሰው ጉዳት አካል ላይ ቢሆንም የአፈፃፀሙን ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት በግድያ ሙከራ ሊጠየቅ ይችላል። ይህ ማለት ሙከራ የሚያስቀጣው የተሞከረው ወንጀል ሊያስቀጣ በሚችለው ልክ በመሆኑ (አንቀፅ 27(3)) ከተራ ግድያ እስከ ከባድ ግድያ ባሉት የቅጣት ዓይነቶች ውስጥ ከ5 ዓመት ፅኑ እስራት ጀምሮ እስከ የዕድሜ ልክ ወይም በሞት ሊያስቀጣ ይችላል ማለት ነው።
በወንጀል ህጉ አንቀፅ 556 ስር እንደተደነገገው በአንቀፅ 555 ከተመለከቱት ሁኔታዎች ውጪ አስቦ በሰው አካል ላይ ጉዳት ያደረሰ ሰው ታስቦ በሚፈፀም ቀላል የአካል ጉዳት ወንጀል የግል አቤቱታ ሲቀርብበት ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም መቀጮ ይቀጣል። ጉዳቱ ከዚህ ከፍ ያለ ክብደት ካለው በወንጀል ክስ አቅራቢነት የሚያስቀጣ ሆኖ ከ6 ወር እስከ 3 ዓመት ለመድረስ በሚችል ቀላል እስራት የሚያስቀጣው፡-
1. ጥፋተኛው ጉዳቱን ያደረሰው በመርዝ ወይም በገዳይ መሳሪያ ወይም የአካል ጉዳት ለማድረስ በሚችል በማናቸውም ሌላ መሳሪያ በመጠቀም እንደሆነ፤
2. ጥፋተኛው የሙያ ወይም ሌላ ግዴታን በመተላለፍ ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ፤
3. ተጎጂው ደካማ፣ በሽተኛ ወይም ራሱን ለመከላከል የማይችል እንደሆነ ነው።
በሌላ በኩል በአካል ላይ ጉዳት ማድረስ በቸልተኝነትም ሊፈፀም ይችላል። ይህ በሚሆንበት ጊዜ የወንጀል ህጉ አንቀፅ 559 ተግባራዊ ይሆናል ማለት ነው። በዚህም መሰረት ማንም ሰው በቸልተኛነት በሌላ ሰው አካል ወይም ጤንነት ላይ ቀላል ጉዳት ያደረሰ እንደሆነ ከ6 ወር በማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም ከብር 1 ሺ በማይበልጥ መቀጮ ይቀጣል። የደረሰው ጉዳት በአንቀፅ 555 የተመለከተው ዓይነት (ከባድ የአካል ጉዳት) ከሆነ ወይም ጉዳት አድራሹ የሌላን ሰው አካል ወይም ጤንነት የመጠበቅ የሙያ ወይም ሌላ ግዴታ ያለበት እንደ ህክምና ባለሞያ ወይም አሽከርካሪ ያለ ሰው ከሆነ ቅጣቱ ከ6 ወር የማያንስ ቀላል እስራትና ከ1 ሺ ብር የማያንስ መቀጮ ይሆናል። ከዚህ ጋር በተያያዘ በአንድ ድርጊት (ለምሳሌ በመኪና አደጋ) ከአንድ በላይ በሆኑ ሰዎች ላይ ጉዳት ሊደርስ የሚችልበት ዕድል ሰፊ ነው። እንዲህ ዓይነት ሁኔታ በሚያጋጥምበት ጊዜ ጉዳት አድራሹ በተደራራቢ ክስ ሊጠየቅ እንደሚችል በወንጀል ሕጉ አንቀፅ 60(ሐ) ስር ተደንግጓል።
የወንጀል ህጉ አንቀፅ 560 ደግሞ እንደነገሩ አካባቢ ሁኔታ እስከ 3 ወር ቀላል እስራት ሊያስቀጡ የሚችሉ የአካል ጉዳት ወይም በጤንነት ላይ ጉድለት ሳያደርስ በሌላ ሰው ላይ የሚፈፀምን የእጅ እልፊት ወይም የመጋፋት ድርጊትን ይመለከታል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሆኖ በሌላ ሰው ላይ ጉዳት ያደረሰ ሰው ቅጣቱ ሊቀልለት የሚችልበት አጋጣሚ ይኖራል። በዚህም መሰረት የአስገዳጅ ሁኔታን ወሰን በማለፍ ጉዳት ቢደርስ፣ ከፍ ባለ ደም በሚያፈላ መቀስቀስ ምክንያት ወይም ባልጠበቀውና ህሊናን በሚያውክ ድንገተኛ ምክንያት ተነሳስቶ ጉዳት ማድረስ፣ በተጎጂው ጠያቂነት መሰረት የደረሰ ጉዳት ሲሆን ቅጣቱ ከ4 ዓመት የማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም ከብር 4 ሺ በማይበልጥ የገንዘብ መቀጮ የሚቀጣ ይሆናል (የወንጀል ሕግ አንቀፅ 557)። ከዚህም በተጨማሪ ቀላል የአካል ጉዳት ለማድረስ አስቦ ከባድ የአካል ጉዳት ያደረሰ ሰው ከ6 ወር እስከ 3 ዓመት በሚደረስ ቀላል እስራት የሚቀጣ ይሆናል (የወንጀል ሕግ አንቀፅ 558)።

6 months ago

የፌዴራል የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት ከፍትሕ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ሲሰጥ የቆየው የስራ ላይ ስልጠና ዛሬ ተጠናቀቀ

(ጳጉሜ 4/2016 ዓ.ም) የፌዴራል የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት ከፍትሕ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ሲሰጥ የቆየው የስራ ላይ ስልጠና ዛሬ ተጠናቀቀ፡፡

በስልጠናው ማጠናቀቂያ ዕለት በመገኘት ንግግር ያደረጉት በሚንስትር ማዕረግ የፌዴራል የፍትሕና ሕግ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ክቡር አምባሳደር ደግፌ ቡላ በንግግራቸው ተቋሙ የሚሰጣቸው ተግባርና ሃላፊነቶችን ለተሳታፊዎቹ በማስተዋወቅ የጀመሩ ሲሆን ይህ ስልጠናም የኢንስቲትዩቱ አንድ አካል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የፌዴራል የፍትሕና ኢንስቲትዩት በዋናነት እውቀት ላይ ሳይሆን ዋና የትኩረት አቅጣጫው ችሎታ እና ሥነ - ምግባር ላይ ነው ያሉት አምባሳደሩ እዚህ ያሉ ሰልጣኞች በመሉ እውቀትን ከዩንቨርሲቲ ይዘው የመጡ ስልሆነ እኛ ትኩረታችንን በተግባር የተደገፈ የዕለት ከዕለት ክንውኖች ላይ እናደርጋለን ብለዋል፡፡

በስራ ውስጥ ሆናቹህ መማርና መሰልጠን ተገቢ ነው፣ ማንበብና እራስን ማዳበር ደግሞ ብልህነት ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ በመሆኑም እዚህ ደረስኩኝ ብላቹህ መማርና ምንበብን ልታቆሙ አይገባም ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋ፡፡

የፍትሕ ሚኒስቴር ሚንስትር የሆኑት ክቡር አቶ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ በንግግራቸው ደግሞ ሙያዊ መቀንጨር እንዳያጋጥማቹህ እድሜ ልካቹህን መማር፣ እራሳቹህን ማሳደግና ብቁ አድርጎ መገኘት ይጠይቃል በማለት የስራ መመሪያ የሰጡ ሲሆን እውቀት ያለው፣ ክሂሎት ያዳበረ፣ ጽናት ያለው እና ህዝብና ሃገርን ለማገልገል የቆረጠ ባለሙ መሆን ይጠበቅባቹሃል ሲሉ በአደራ ጭምር አሳስበዋል፡፡

ስልጠናው ከነሃሴ 6/2016 - ጳጉሜ 01/2016 ዓ.ም የተሰጠ ሲሆን በአስራ አንድ የተለያዩ ርዕሶች ለ102 የቅድመ ስራ ሰልጣኞች ተሰጥቷል፡፡

============================
ዘገባው ፡- የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ነው!

We recommend to visit

꧁❀✰﷽✰❀꧂
In The Name Of God

تبلیغات? :

https://t.me/+TJeRqfNn3Y4_fteA

Last updated 2 months, 2 weeks ago

☑️ Collection of MTProto Proxies


? تبليغات بنرى
@Pink_Bad

? تبليغات اسپانسری
@Pink_Pad


پینک پروکسی قدیمی ترین تیم پروکسی ایران

Last updated 2 months ago

Official Channel for HA Tunnel - www.hatunnel.com

Last updated 6 months ago