● Welcome to Ethio music Channel
➤ For any promotion and Advertising 📩 inbox @Markonal21 ወይም @ethiomusic21bot
.
.
● የበጎ አድራጎት ስራዎችን በነፃ ፖስት እናደርጋለን ለመልካምነት ቦታ አይመረጥም ! ያዋሩን
.
.
● የሀገር ውስጥ አዳዲስ
ሙዚቃዎች
አልበሞች በፍጥነት ያገኛሉ
.
● እንዲሁም በቀናነት JOIN & SHARE ያድርጉ !
Last updated 6 months ago
?? የምርጥ ሙዚቃዎች መገኛ ??
For promotion and Advertisements
? @Mussegirma
#ካሮት_ሙዚክ✋
ሰለ ቻናላችን ማንኛውንም የፈለጉትን ሙዚቃ እና ያለወትን ቅሬታ
ሆነም አስተያየት በማለት
በዚህ #bot✍ ማቅረብ ትችላላችሁ፡፡
???????????
http://t.me/yekonjochumenahriabot
እናመሰግናለን?
Admin
@Aymu_xo
የጠዘጠዘኝ ኑሮን ጎርሼ
እንባ የጨረሸኝ ዉስጥዉስጥ አልቅሼ
የሸረሸረኝ
የምድር ርብራብ
እንደ ቅልብልብ
ከወዲያ ወዲህ ያነጣጠረኝ
ሞት ሞት ሲሸተኝ
ማር ነዉ እያለ
እሬት ሲያግተኝ
ከዚህ ምስቅልቅል
ግማሽ ፈገግታህ የሚነርተኝ!!
ግማሽ ፈገግታ
ኑሮ አደካክሞት የማይረታ!!
እንኳን አልሞላህ
እንኳን ለ ሙሉ አለም አልደላህ
በሳቅህ ወጀብ
በጥርስህ መደብ
በክፋይ ብቻ
ለጋ ነፍሴ ላይ ሳቅህ ሲደንስ
ዱንያ ስትለጋኝ
በሰራችዉ ጎርፍ
ድል ቷንኳ ሰርቶ ሀሴት ሲደግስ
አስበኀዋል ሳቅህ ቢሞላ?!
ሩሄ ችላ??
እንኳን ልትችል
ከኑሮ ቀድማ በሳቅህ ፍንግል!!
አንተዬዋ...
በፈጠረህ አንተን ረቂቅ
ሞልተህ እንዳትስቅ!!
እንዳይታይ ጥርስህ ሙሉ
ለጭንቀቴ ሀሳብ ሁሉ
ክፋይህ አስማት አለበት
ደሞ
እንዲህ አለም በጀሽ ሲርቃት
ነፍሴን ጭንቀት ሲያስጨንቃት
መሞላትህ ያስፈራኛል
እንደ ሀበሻ መድሀኒት
ሲቃ ሀሴቴ
በዝቶ ሚገድል ይመስለኛል!
ብቻ ብቻ
መቆም ከብዶኝ ስንገዳገድ
በከንፈርህ ቀጭን ገመድ
ነፍሴ እንዳትነድ
ሳትሞላዉ
ግማሽ ሳቅን ወዲህ ስደድ!!
(ሳቅህ እና ይሄ አበባ❤)
There are days that i say
"ኦ አላህ !
እነዚያን የለመንኩህን ሁሉ ሰጥተኸኝ ቢሆን ኖሮስ ?
What would my life look like?
አልሀምዱሊላህ ።"
"ትወጂዉ የለ?"
"እና?" አልኳቸዉ።ደነገጡ።"እሱማ..." ብዬ እንደልማዴ ምቅለሰለስ መስሏቸዉ ነበር።
"እና?? እና ምን ማለት ነዉ? በቃ ልትፈቺዉ ነዉ? ምን ነካሽ ልጄ!
ልጅሽስ?
በይ ተማርኩ ተማርኩ ስትዪ አጉል ዘመናዊነት አያጥቃሽ።ደሞ
ባልን እንዳመሉ እየሸመገሉ መኖር ነዉ የ ሴት ወግ!
እንደዉ ገና ለ ገና መታኝ ብለሽ ቤትሽን ልትበትኚ???"
እንደ ሁልጊዜዉ ጎረቤቶቻችንን ሰብስቦ ሽምግልና ልኮ መቀመጣቸዉ ነዉ።ያኔ እንደዛ ሲሰድበኝ ፤ አንዴ ስራዬን ፣ አንዴ ቤቴን ፣ አንዴ ልጄን ፣ ብዙ ጊዜ ስድቡን እና ዱላዉን ሽሽት እየተክለፈለፍኩ ስውል የቀጠቀጠኝ ማግስት ተሰብስበዉ መጥተዉ
" 'እንደ ድሮ አትዘንጥም' አለን እኮ!
'ስመጣ በተቀደደዉ ሺቲዋ ነዉ ማገኛት' አለ ስናወራዉ..... እንደዉ ልጄ ወንድም አይደል? ቤቱን ሊሞላ አይደል ሚለፋዉ? አይኑ ብዙ ቀላዉጦ ስለሚመጣ እንደምንም ታጥበሽ ልብስ ቀይረሽ ብጠብቂዉ እኮ ደስ ይለዋል...ጎሽ!....እንደ ሴት እንደ ጥበብሽ ያዝ አርጊዉ እስቲ..." ያሉኝ። ሲደበድበኝ ያገላገሉኝ።
እጄን በ አፌ ጭኜ ያቺን አስቤዛ እና የቤት-ኪራይ መክፈል ለዚህ ሁሉ ነገሩ መሸፈኛ መሆን መቻሉን ሳይ ግርምም ድንግጥም ያረገኛል።እንደዉ ረብጣዉን ቢያዘንበዉ እራሱ የዚህን በደል ይሸፍነዋል? አረ እንዴት ማባበል ቻሉበት?
በእርግጥ አልዘንጥም!!
ሳያገባኝ በፊት የነበረኝ ሊፒስቲክ ሲያልቅ ጠይቄዉ 'አሁን ያለሁበትን ወጪ እያየሽ!" ሲለኝ ከሱ አይበልጥም ብዬ ትቻለዉ።ደግሜም አላነሳዉ።ልብስም ቢሆን ቤተሰቦቼ ጋር ቤተሰቦቹ ጋር ስሄድ እንዳላሳጣዉ እያልኩ ከሽንኩርት ከ ቲማቲም እየለቀምኩ በሰበሰብኩት ቦንዳ ልቃርም እንጂ አልጠይቅም።ሁሉንም ማድረጌ ለ ፍቅሩ ነበር።አጥቼ እንኳን ማስበዉ የሱን አለመዋረድ ነበር። ሲመታኝ መታገሴ የነገ ይቅርታዉን አምኜ ነበር።
ጭቅጭቁን ፣ ስድቡን ባስክ ሲልም ዱላዉን መቀበል ሲሰለቸኝ እንደመከሩኝ ለመዘነጥ ልጄን ይዤ ወጣሁ።"ምን ጎደለሽ?" ሲለኝ ብዘረዝር ለማይገባዉ ችግሮቼ... ትቼዉ ስራዬን ቀጠልኩ።ተፍ ተፍ ብዬ ሊፒስቲኩንም ፤ ልብሱንም ሸማመትኩ።ትንሽ መለስ አልኩ።የድሮ እኔን በ ትንሽ በ ትንሹ መሰልኩ።ከዛ ጎረምሳ ያዝሽብኝ ብሎ ዱላዉን ዘረጋዉ።
ደከመኝ
ሰለቸኝ
ቆረጠልኝ!!!
ለ እዉር መፅሃፍ አይሰጡትም። ለ አይናማም ብሬል አይገባዉም።ቋንቋችን ለየቅል ፤ ሀሳባችንም በየፊናችን ሲሆን የገጠመ እስኪገኝ መታገስ እያለ ካልገጠምነዉ ካልገጠምን ሙግት ትርፉ መሰበር ነዉ።
አይሆኑ አሰባበር ፤ አይሆኑ አወዳደቅ ከሚሆን ደሞ በጊዜ መሸኛኘት እንዴት እንደሚያድን!
በጊዜ አልሄድኩም።ቆይቼም ግን አልቀርም።ስብርባሪዬን ለቅሜ ተነሳሁ።በተረፈዉ ለ ልጄ ልኑር። ከምንም በላይ ደሞ ለራሴ ልቅር!
"ታግሶ በትዳሯ ተከብራ እንደመኖር! ልጇን አባት አልባ ልታረገዉ፤ አይ የሴት ወጉ እንዲህም አልነበር! ተነካዉ ተብሎ ፍቺ??!!..."
የ ሴቶቹ ጩኀት ከጀርባ እየገፋኝ ተነሳሁ
Almost በሚባል ደረጃ ሙስሊም ማህበረሰብ በማይበዛበት አከባቢ የተማረች ሙስሊም ሴት በተለይ የ መንግስት ት/ት ቤት የሆነ ጊዜ ከ ትምህርቷ እና ከ ሂጂቧ ምረጪ ተብላ ታግላለች ወይም የታገለች የ ቅርብ ጓደኛ አላት።ትግሉ ጥሏት ያቋረጠችዉን ቤቱ ይቁጠራት ተብሎ
ታላቆቻችን ታግለዉታል!
እኛ ታግለነዋል!
ታናናሾቻችን እየታገሉት ነዉ!
በዚህ ከቀጠልን ገና ዛሬ የተወለዱትም
ነገ የሚወለዱትም ደርሰዉ ይታገሉታል!!
መፍትሄዉ በ ሆይ ሆይታ የዛን ትምህርት ቤት ጉዳይ መፍታት እንዳልሆነ ዘመናት የዘለቀዉ ጩኀታችን ምስክር ነዉ።በ ት/ት ሚኒስተር ፖሊሲ ዘንድ መቀመጥ ያለበት ነገር ነዉ።
"ማንም ተማሪ የመማር መብት አለዉ"ከሚል ህግ ከፍ ብለን
"ማንኛዋም ሙስሊም ሴት ሂጀብ ለብሳ መማር ትችላለች" ወደሚል የተደነገገ የማይነካ ከ ፎርም ከፍ ያለ የማይጣስ ህግ መምጣት አለብን።ህጉን የካደ ከነ ቅጣቱ!
As of June 2024, a total of 8.32 M children “remain out of school or have intermittent access to schooling” (G-50%) due to humanitarian emergencies and protracted crises, nearly three times what is was on year ago (June 2023). In Q2 of 2024, a total of 60 schools have been rehabilitated or have been rehabilitated or undergoing rehabilitation ; over 9K school are partially or severely managed across the country
ይሄ እንግዲህ የ ቅርብ ጊዜ መረጃ ነዉ።ወደ ስምንት ሚሊየን ሳስት መቶ ሀያ ሺህ ተማሪዎች በጦርነት ፤ በ ተፈጥሮ አደጋ እና በመሳሰሉት ከ ትምህርት ገበታቸዉ ተፈናቅለዋል። ባለፉት አመታት ባሳለፍናቸዉ ጦርነቶች ደሞ የዚህ ዋና ተጠቂ የ ትግራይ ክልል መሆኑ አያጠያይቀንም እና የተፈናቀሉት ተማሪዎቼን ለመመለስ እየሰራዉ ነዉ ከሚል ተቋም እና ክልል ይሄ ቀሽም ክልከላ "ቢመጡም አይጠቅሙም!" ከሚል ጭፍን ጥላቻ እንጂ ለአንዱ እየሰራዉ አንዱን እያባረርኩ ነዉ የሚል ብሂል ከየትም አይሆንም።
ከፀጋዎችህ ብዙዉን ሰጠኀን።ጎዳዩ የተቀባዩ መጉደል እንጂ የሰጪዉ መሰሰት አልነበረም።እየተንገጫገጨ የቀረ ብርጭቆ ከነበረዉ እያጎደለ እንዴት ሊሞላ ይችለዋል?የ ፀጋዎችህ ብዛት ከስስታምነታችን እጅግ ቢገስፍስ አይደል ከመንገጫገጭ ጋር መሞላታችን....ያ ረሂም....ታዉቀን የለ? ለአፍታ ብትተወን ገደል መገኛችን እንደሚሆን?
ፈራን!
እራሳችንን ፈራን!
አካሄዳችንን ፈራን!
ደጃፍህ ላይ ቆመን እንኳን ከመስገጃዉ ትይዪ እያየን ፣ ስለጉዳያችን አንተን ከማማከር አርቆ የሚያሳስቡን ብክነተ ሀሳቦች ይዘዉን እንዳይነጉዱ ፈራን!
የተዉከን ቀን የምወድቅበትን ፈራን!. ከጎዶሎ ላይ ቆመን ባዶነትን ፈራን....
የከበቡን ወንጀሎች ቁጥር አያዉቃቸዉ ይሆናል።ቀን በደረበ ቁጥር ፤ የትላንቱን ሳናራግፍ የምንጨምረዉ አንድ አንድ ዘለላዎች ተከማችተዉ ይዘዉን ሲነጉዱ ጨልፈን ልንቀምሰዉ የገባንበት የተሳሳተ መንገድ አዝፍቆ ሲነክረን ፤ የጥፍጥናም ይሁን ምሬት ስሜት ከቀልቦቻችን ምላስ ሲጠፉ ፤ አሸናፊ የሌለዉ ግብግብ ራሳችን ጋር ስንፈጥር ፤ የሸይጣን ዋንኛ ስራዉ የዚህን ሁሉ ሸክም ማራገፊያ እዝነቱን ከአይናችን መሸሸግ ነዉ።በአፋችን አሰር ግዜ የምናነበንበዉን የምህረቱን ስፋት ከቀልባችን ትርጉም ማሳጣት ነዉ። በቃን!...ዉስጣችን ካለ ሌላ ሰዉ ጋር ለብቻችን መጋፈጡ ይብቃን።ከልብህ ፤ የዉስጥህን እሚያቅ ሊረዳህ እጁን የዘረጋ ራህማኑ እንዳለ ታምናለህ? ታዲያ መሸሽህ ማብቂያዉ መቼ ነዉ? ሸሽተን መዳረሻችን ወየት ይሁን?
وَٱسْتَغْفِرِ ٱللَّهَۖ إِنَّ ٱللَّهَ كَانَ غَفُورًا رَّحِيمًا
ዛሬ ከልብህ አስተንትነዉ።ከራስህ እና ጌታህ ጋር ሰላም አዉርድ።መባልህን አስታዉስ
"ጠይቁኝ!እቀበላችኅለዉ"
ያረቢ
ሞልቼም አንተን እንዳረሳህ.... ባዶነቴም የፀጋን ምንነት እንዳያጠፋብኝ ዘንድ ልክ የሆነ መጉደልን ፤ ልክ የሆነ መሙላትን ከመታገሻ ቀልቢያ ጋር ትወፍቀኝ ዘንድ ተዋደቅኩ።
"እሷ ምን አላት?"
"ማይሰበር ሞራል ፤ ከማነብነብ ያለፈ የተማመነ ትከሻ ፤ የልብ ሙላት"
"ከወየት አመጣችዉ?"
"ከ አሊፍ ባ ዛይዘልቁ፤
እንኳን ለ ሰዉ ለዚያች ተበላሸችባቸዉ ቦርጫሟ ቲቪ እንኳ
'ቢስሚላህ'ን
ከቱፍታቸዉ ጋር እንደሚያሽራት ተማምነዉ ከጠገኗት እናቷ!
የራበዉ ሆዱን ፤ የጎደለ ሀጃዉን ወደ ዉስጥ ቀብሮ በ ሀቅ ላይ ቆሞ ከነገደዉ አባቷ!
በ አሚናቸዉ ፤ በ 'ይሁን አሁን!" ማሳረጊያዉ ላይ እንደሚሆን የሚያሳብቀዉ የ ጎረቤቷ ፊት ወዝ"
"ሀቋ ሲደፈር መቆሙንስ ከየት አገኘች?"
"ከልቧ ከቀረበዉ ጌታዋ!"
አልሀምዱሊላህ?
● Welcome to Ethio music Channel
➤ For any promotion and Advertising 📩 inbox @Markonal21 ወይም @ethiomusic21bot
.
.
● የበጎ አድራጎት ስራዎችን በነፃ ፖስት እናደርጋለን ለመልካምነት ቦታ አይመረጥም ! ያዋሩን
.
.
● የሀገር ውስጥ አዳዲስ
ሙዚቃዎች
አልበሞች በፍጥነት ያገኛሉ
.
● እንዲሁም በቀናነት JOIN & SHARE ያድርጉ !
Last updated 6 months ago
?? የምርጥ ሙዚቃዎች መገኛ ??
For promotion and Advertisements
? @Mussegirma
#ካሮት_ሙዚክ✋
ሰለ ቻናላችን ማንኛውንም የፈለጉትን ሙዚቃ እና ያለወትን ቅሬታ
ሆነም አስተያየት በማለት
በዚህ #bot✍ ማቅረብ ትችላላችሁ፡፡
???????????
http://t.me/yekonjochumenahriabot
እናመሰግናለን?
Admin
@Aymu_xo