🍿የ VIP ቻናላችንን በአነስተኛ ክፍያ በመቀላቀል ሁሉንም ፊልሞችን ማግኘት ትችላላቹ።
🍿 CHANNEL ~> @Wase_Records
🍿 BOT ~> @Wase_Records_Bot
🍿 OWNER ~> @The_hacker_person
🍿 VIP ~> @The_hacker_person
Last updated 6 days, 8 hours ago
አፍሪወርክ ቢዝነሶች እና የግል ቀጣሪዎች ለስራቸው ከሚፈልግዋቸው ፍሪላንሰሮች ፣ ቋሚ ሰራተኞች እንዲሁም የትርፍ ጊዜ ሰራተኞች ጋር በቀጥታ የሚገናኙበት ፕላትፎርም ነው።
አሰሪዎች ስራ ለመልቀቅ @freelanceethbot ይጠቀሙ
Afriwork in English @freelance_ethio
Last updated 1 month, 3 weeks ago
ለ108 የውጪ ሀገር ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች የአጭር ጊዜ የቀረፃ ፈቃድ ተሰጠ
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባለፉት ስድሰት ወራት ለ108 የውጪ ሀገር ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች የአጭር ጊዜ የቀረፃ ፈቃድ መስጠቱን አስታወቀ፡፡
ባለስልጣኑ የቀረፃ ፈቃዱን የሰጠው ከ31 የውጪ ሀገር መገናኛ ብዙኃን፣ ከፊልም ሰሪ ድርጅቶች እና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ለመጡ 108 ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች መሆኑን ነው የገለጸው፡፡
ባለሥልጣኑ፤ በታሪካዊና ተፈጥሯዊ ቅርሶች እንዲሁም ባህላዊ እሴቶች ዙሪያ ዶክመንተሪ ፊልም ለመስራት፣ ከመንግስት ኃላፊዎች እና ከታዋቂ አትሌቶች ጋር ቃለ-መጠይቅ ለማድረግ፣ ወቅታዊ ጉዳዮችን እና የልማት ስራዎችን በሚመለከት የዜና ዘገባ ለመስራት ፈቃድ ለጠየቁ የውጪ ሀገር መገናኛ ብዙኃን እና ድርጅቶች የአጭር ጊዜ የቀረፃ ፈቃድ መስጠቱን አስታውቋል፡፡
ሀገሪቱን ለውጪው ዓለም ለማስተዋወቅ ለሚመጡ ባለሙያዎች፤ ፈቃድ ከመስጠት ባለፈ ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በመተባባር በነፃነት ተንቀሳቅስው እንዲሰሩ ድጋፍ በማድለግ ላይ እንደሚገኝ ነው ባለስልጣኑ የገለጸው፡፡
በቀጣይም የጥምቀት በዓል እና የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔን ለመዘገብ ለሚመጡ የውጪ ሀገር ጋዜጠኞች እና የፊልም ባለሙያዎች፤ አስፈላጊውን አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ከባለስልጣኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
ምንጭ: አዲስ አድማስ
JC SA!
እዉነቱን በኃላፊነትና በሚዛናዊነት እንነግራችኋለን!!
Join our channel & group 👇
@HUJCSA
@HU_JCSA_Group
ሰላም ውድ የኢንክሉሲቭነስ ክበብ አባላት እንዴት ቆያችሁ እሁድ በቀን 07/04/2016 አ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ኢንክሉሲቭነስ ክበብ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ዋናው ግቢ ውስጥ የፅዳት ስራ ልንሰራ አስበናል ስለሆነም የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እንዲሁም የኢንክሉሲቭነስ ክበብ አባላት በዕለቱ ተገኝታችው የበጎ ስራው አካል እንድትሆኑ ስንል በአክብሮት እንጋብዛችዋለን።
በዕለቱ እሚሰሩ ስራዎች
👉 የአካል ጉዳተኛ ተማሪዎችን ዶርም ማፅዳት
👉 ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ውስጥ እሚገኙ ቆሻሻዎችን እንዲሁም ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ያልሆኑ ቦታዎችን በማፅዳትና በማስተካከል ሰኞ እና ማክሰኞ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲን ለሚቀላቀሉ አዲስ ገቢ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች እንዲሁም አካል ጉዳተኛ ላልሆኑ ተማሪዎች ግቢውን በጥሩ መንፈስ እንዲቀላቀሉ የማረግ ስራ እንሰራለን።
መገናኛ ቦታ
የኮምፕሌክስ መግቢያ ደረጃ ላይ
ቀን እና ሰአት
እሁድ 07/04/2016 አ.ም ከጠዋቱ 2፡30
ለበለጠ መረጃ
0931294893
0985960598
ማርፈድ የተከለከለ ነው።መገናኛ ሰአታችን ይከበር!!
በጎነት ለራስ ነው።
Inclusiveness Club
join our Channel 👇👇
https://t.me/inclusivness_club
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተማሪዎች መማክርት አባላትን ይፋ አደረገ ።
የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ላለፉት 5 ሳምንታት አዲስ የመማክርት አባላትን ሲፈትንና ሲመለምል ቆይቶ
የተዘጋጀውን ፈተና በጥሩ ውጤት ያለፉትን 3 የስራ አስፈፃሚዎች፣12 የዘርፍ መሪዎች፣2 አፈ ጉባኤ
እና 1 ኦዲተር ለዩኒቨርስቲው ከፍተኛ አመራር እና ለተማሪዎች ይፋ አደረገ ።
በስልጣን ርክክብ ወቅት የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ከበደ እንደተናገሩት የተማሪዎችን ሰላም እና ደህንነት እንዲሁም የመማር ማስተማር ሂደት ስላማዊ እና የተመቻቸ እንዲሆን የምትሰሩ የተማሪዎች ተጠሪ በመሆናችሁ ትልቅ ኩራት ሊሰማችሁ ይገባል ብለዋል።
አስከተለውም ይህንን ትልቅ ሀላፍነት የተሸከማችሁ በመሆኑ በትጋት እና በጽናት የዩኒቨርስቲውን ራዕይና
የተማሪዎችን ፍላጎት ከግብ እንድታደርሱ ስል ተይቋል።
ያቀዳችሁትን እቅድ ከግብ እንዳታደርሱ ከሚያደርጉት ከአላስፈላጊ ወሬና ሹክሹክታ እራሳችሁን እንድትጠብቁ ሲሉም አቶ ተመስገን ተናግረዋል።
በመጨረሻም ላለፉት ሁለት አመታት ዩኒቨርሲቲውን ስያገለግሉ ለቆዩ ለቀድሞ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ፕሬዚዳንት አቶ ዘለቀ ገመቹ እና ለመማክርት አባላት ልባዊ ምስጋናን ያቀረቡ ሲሆን
አዲስ የተመረጡትንም የተማሪዎች መማክርት፣ እንዲሁም አዲሱን የተማሪዎች ፕሬዝዳንት ተማሪ እሴይ ጴጥሮን እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሰሆን የምርጫ ህደት አስተባባሪዎች በተገኙበት ህዳር 24/ ሰኞ 5:00 የስልጣን ርክክብ ተከናውኗል።
የስም ዝርዝራቸውና ስልጣናቸው እንደሚከተለው ተቀምጠዋል
1,እሴይ ጰጥሮስ......ፕረዚዳንት
2,ሚስጥር አሸናፊ....ም/ፕረዚዳንት
3,ቃልኪዳን ስጦታ...ፀሐፊ
4,እንዲሪያስ ፎራ....ጠቅላላ አገልግሎት
5,አጫሉ ደረጀ..........የዲስፕሊን ዘርፍ ሀላፊ
6,ተመስገን ጎቤ.......የጤና ዘርፍ ሀላፊ
7,ሚካኤል ኡጋሞ......የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሀላፊ
8,ነጋሽ ዮሐንስ........የምግብ ዘርፍ ሀላፊ
9,በላይ ጰጥሮስ......የ finance ዘርፍ ሀላፊ
10,ሱመያ ሙስጠፋ...የሴቶች ኘሬዝዳንት
11,አሰበ ፍቃዱ ......በጎ አድራጎት ዘርፍ
12,አዚዛ ይማም......አካዳሚክ ዘርፍ ሀላፊ
13,መቅደስ ደሳለኝ.....የክበባትና የማህበራት ዘርፍ
14,ቹዳየር ዋኝረክ......የስፖርት እና መዝናኛ ክፍል
15,ፍጹም እሸቱ..................ዋና አፈ ጉባኤ
16,ሳሙኤል ወንድሜነህ .....ምክ/አፈ ጉባኤ
17,ፊልጶስ ጥዕመልሳን......ኦዲተር
የሁሉም የስራ አስፈፃሚዎች እና የመማክርት አባላት
የስልጣን ዘመናቸው ለሚቀጥሉት ሁለት አመታት ይሆናል ።
ዘጋቢ ሚካኤል 4ተኛ አመት የጋዜጠኝነት እና ስነ ተግባቦት ት/ክፍል ተማሪ
🍿የ VIP ቻናላችንን በአነስተኛ ክፍያ በመቀላቀል ሁሉንም ፊልሞችን ማግኘት ትችላላቹ።
🍿 CHANNEL ~> @Wase_Records
🍿 BOT ~> @Wase_Records_Bot
🍿 OWNER ~> @The_hacker_person
🍿 VIP ~> @The_hacker_person
Last updated 6 days, 8 hours ago
አፍሪወርክ ቢዝነሶች እና የግል ቀጣሪዎች ለስራቸው ከሚፈልግዋቸው ፍሪላንሰሮች ፣ ቋሚ ሰራተኞች እንዲሁም የትርፍ ጊዜ ሰራተኞች ጋር በቀጥታ የሚገናኙበት ፕላትፎርም ነው።
አሰሪዎች ስራ ለመልቀቅ @freelanceethbot ይጠቀሙ
Afriwork in English @freelance_ethio
Last updated 1 month, 3 weeks ago