የስራ ማስታወቂያ ከጋዜጣ ፣ ከቲቪና ራዲዮ ፣ ከማስታወቂያ ቦርድ ፣ ከድህረ-ገፅና ከማህበራዊ ሚዲያና ከመሳሰሉት ቦታዎች በአንድ ቦታ ተሰብስበው ያግኙ::
#Group t.me//Ethio_Jobs2000
#የመዝናኛ ቻናል https://t.me/+UPjrnHF6QzI0ZmQ0
https://t.me/+h0l2XzeI8RQyODlk
For promotion ? @Share_Home
Last updated 1 month, 2 weeks ago
ከቅዳሜ በስተቀር በየዕለቱ፣ ከሰኞ እስከ ዓርብ ረፋድ ከ3:30 እስከ 5:00፣ እሁድ ከጠዋቱ 2:00 እስከ 4:00 በብስራት ኤፍ ኤም 101.1
Last updated 7 months, 4 weeks ago
Certified Professional Life Coaches
የቻናላችንን አነቃቂ ቪዲዮ መመልከት ለምትፈልጉ
https://www.youtube.com/@inspireethiopiamedia ? ይሄንን ሊንክ ይጫኑ
Last updated 9 months, 4 weeks ago
+++####መርፌ_ወይስ_ጊንጥ?###+++
ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ሰው ወደ ግል ቤተ መጻሕፍቱ ሄደና ከመደርደሪያው አንድ መጽሐፍ ሲያነሣ ጣቱን መርፌ የወጋው ያህል ተሰማው። ሰውዬውም ጣቱን የወጋው መጽሐፉን ተውሶ ከወሰደ አንድ ግድየለሽ ሰው በአንደኛው ገጽ ላይ የተሰካ መርፌ እንደ ኾነ አድርጎ ነበር ያሰበው። በቀጣዩ ቀን እብጠቱ ከተወጋው ጣቱ ላይ ጀመረና ሙሉው እጁንና ክንዱን ከዚያም መላው ሰውነቱ አበጠ። በጥቂት ቀናት ውስጥ ሰውዬው ሞተ።
ሰውዬው ጣት ላይ ጉዳት ያደረሰው በመጽሐፉ ገጾች በአንዱ ተሰክቶ በነበረ መርፌ ሳይኾን ከመጽሐፉ መደርደሪያ ውስጥ ተደብቆ በነበረው አንድ መርዛማ ጊንጥ ነበር፤ ሰውየውም መርፌ መስሎት ስለ ነበር የደረሰበትን ጉዳት ቸል ስላለው ነበር የሞተው። በእውነት ከጊንጥ በላይ አደገኛ መርዝ የተሸከሙ፥ የሰውንም ሐሳብ የሚነድፉና ሥውር ሕማምን የሚያመጡ ብሎም የዘለዓለምን ሕይወት እስከማሳጣት የሚያደርሱ ብዙ መጻሕፍት አሉ። ከእነዚህም መጻሕፍት ውስጥ አንዱ በሐዋ 19፥19-20 ላይ የተጠቀሰው ነው። "ብዙዎች አስማተኞችም መጻሕፍቶቻቸውን እየሰበሰቡ እያመጡ በሕዝቡ ኹሉ ፊት በእሳት ያቃጥሉ ነበር፤ ያቃጠሏቸው የመጻሕፍት ዋጋም ሃምሳ ሺህ ብር ነበር። እንዲህም እያለ የእግዚአብሔር ቃል በኃይል ያድግና ይበረታ ነበር።" ይላል። (የሺዋስ መኳንንት (ዲ/ን፣ ዶ/ር፣ ተርጓሚ)፣ ምንም አልሰማሁምና ሌሎችም፣ 2012 ዓ.ም፣ ገጽ 133-34)።
እንግዲህ የብዙዎቻችን የሞት አኗኗር አንዱ ምንጭ የምናነባቸው መጻሕፍት ጥመት ጭምር ነው። ውስጣችን በኃጢአተኝነታችን ከደረሰበት ድብደባ የተነሣ መንፈሳውያት መጻሕፍትን ገፍቶ ወደ ዓለማዊነት የሚወስዱ፣ ሰውነትን የሚያረክሱ መጻሕፍትን ማንበብ ላይ የተጠመደ ነው። ስለዚህ መድኃኒት የሚኾኑንን ቅዱሳት መጻሕፍትን ትተን መርዝ የሚኾኑንን ርኲሳት መጻሕፍት አድፍጠን በማንበብ ላይ ነን። አስተሳሰባችን መርዛማ የኾነውም ከዚህ የተነሣ ነው።
በእርግጥ የብዙዎቻችን ሕይወት እንዲህ ነው። የመጻሕፍት መደርደሪያ በኾነው ልቡናችን ውስጥ ጊንጥ የተባለ የዝሙት ፈቃድ ተቀምጦ አርክሶናል፤ ኾኖም በፈቃዳችን ጥመት ምክንያት እንዲያ እንደ ኾንን ገና አልገባንም። ድርጊታችን ጎጂ መኾኑ ቢታየንም ቀላል ነው እያልን በስንፍና በመጽናታችን ምክንያት ለሞት ይዳርገናል። የሕይወት ፍልስፍናችን በብዙ ጊንጦች ነፍሳችንን ወግቶ መርዛማ አድርጓታል። ይኸውም ዘረኝነት፣ ፍቅረ ነዋይ፣ ልልነት፣ ግትርነት፣ ትዕቢትና መሰል መርዞች ነፍሳችንን ወጋግተው አሳብጠዋታል። ሕይወታችን ወደ ሞት መዳረሻ እየሄደ እንደ ኾነ እስኪረሳን ድረስ በጽኑዕ ጉዳትና ሕማም ውስጥ ነን። ይህ በእጅጉ ያሳዝናል።
ከኹሉም ነገር በላይ እጅግ በጣም አጽንቶ ውስጣችንን የወጋን ጊንጥ ሱሰኝነት ነው። የዝሙት ፊልም፣ የመዳራት፣ የመቀማጠል፣ የዘፈን፣ የጭፈራ፣ የስካር፣ የአደንዛዥ ዕፅ፣ የግብረ አውናን፣ የስካር፣ የሲጋራና የጫት ሱስ ወጋግቶ መርዞናል። በዚህም ምክንያት እንደ ጤናማ ሰው ማሰብ አቅቶን ሕማማችንን ንስሐ የማያስፈልገው ቀላል አድርገን ቆጥረነዋል። ሱሰኝነት ነፍስንም ሥጋንም የሚመርዝ ከጊንጥ የበለጠ ጊንጥ መኾኑን ረስተን ለጊዜያዊ ደስታችን ብለን ሰንፈን ተኝተናል። በጊንጦቹ ምክንያት የመጣብንን የርኲሰት እብጠት በሽታ ከልብ በኾነ ጸጸትና በአንብዓ ንስሐ ማጥፋት ሲገባን ይኹን እያልን ጉዳታችን እያመጣብን ያለውን ውጤት ማየት ተስኖናል።
አባታችን አዳም የእግዚአብሔርን ሐሳብ ክዶ በሚስቱ በሔዋን በኩል የቀረበለትን የዲያብሎስን ቃል ተቀብሎ፥ የብርሃን ልብሱን ባወለቀ ጊዜ፥ ወዲያውኑ የበለስ ቅጠል ማገልደምን ምርጫው አደረገው። ይህም ማለት ኃጢአቴ ቀለል ያለች ናት፥ በዚህ የበለስ ቅጠል እንደ መሸፈን ያለች ናት ሲል ነው። ዲዲሞስ ዓይነ ስውሩ ߵߵአዳምና ሔዋን የበለስን ቅጠል ማገልደማቸው ኃጢአታቸውን ቀላል ለማድረግና ለመደበቅ የሚያደርጉትን ትግል የሚያሳይ ነውߴߴ ይላል። ስለዚህ ነገሮችን ለዘብ አድርገን ለመደባበቅ ከመሞከር ከሥር መሠረታቸው ነቅለን ለመጣል መትጋት ይሻለናል። ካልኾነ ወደ ሞት እየተፋጠንን የምንሄድ መኾኑን ልብ እንበል።
#እንኳን_ደስ_አላችሁ_ዐይነ_ልቡና_ገበያ_ላይ_ውላለች_የምታገኟት_ሰርዲኖስ_መጻሕፍት_መደብር_ላይ_ነው። ሙሉ አድራሻውን ከታች ይመልከቱ።
#ብዙዎች_ጋ_እንዲዳረስ_ሼር_በማድረግ_መረጃውን_በማቀበል_እባክዎት_የበኩልዎትን_ይወጡ🙏
-ሰርዲኖስ የመጻሕፍት መሸጫ መደብር የነበረበትን ቦታ ቀይሮ ማኅበረ ቅዱሳን ፊት ለፊት 5 ኪሎ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሚገኝበት በአዲሱ የቤተክህነት ሕንፃ አንደኛ ፎቆ ላይ ይገኛል። ደንበኛ ይኹኑ።
0910934578
Rahel Emiru
ሌላውን ለጊዜው እንተውና እንዲህ ዓይነት መሠረታዊ ትምህርቶች ላይ ስሕተት ተፈጥሯል። እነዚህን ስሕተቶች ቢያርም መልካም ነው። እግዚአብሔር ወንድማችንን ከክፉ ነገር ኹሉ ይጠብቅልን። እንዲህ ዓይነት ስሕተቶችንም እንዲያርም እግዚአብሔር ኃይሉን ያድልልን። ምናልባትም አሁን ላይ እነዚህን ስሕተቶቹን አርሟቸውም ሊኾን ይችላል። ከኾነም እጅግ ደስ የሚያሰኝ ነው። እንዲህ አላልኩም ቢል እንኳን ደስታዬ ወደር የለውም። ዋናው ጉዳይ መስተካከሉ ነውና። አኹንም አቋም ኾኖ የተያዘ ከኾነ ግን ትልቅ ችግር ነው። ወንድም እኅቶቻችን ሆይ በአገልግሎት ተሠማርተን ላለነው ለኹላችንም ከወደዳችሁን ከልብ ጸልዩልን፤ ክፉ ሰይጣን ቀስ አድርጎ እንዳይጥለንና እንዳያጠፋን የእውነት የኾነ ልባዊ ጸሎት ያስፈልገናልና። ፍቅራችሁን እኛን ሊያድንና ሊጠቅመን በሚችል መንገድ ግለጹ እንጂ ሊጎዳን በሚችል መንገድ አታድርጉት።
ቸር ሰንብቱ!
ስለ ክርስቶስ ማንነት ተሳስተው ለሚያሳስቱ ሰዎች እጅግ ድንቅ ትምህርት!
?አካል እና ባሕርይ
ተከታታይ የነገረ ክርስቶስ ትምህርት
ክፍል 3
ነገረ ክርስቶስን ለመረዳት የሚጠቅመን ትምህርት በዲ/ን ዮሐንስ ጌታቸው
ሙሉ ቪዲዮውን ሊንኩን በመጫን ዩትዩብ ላይ ማግኘት ትችላላችሁ ።
????????
ተከታታይ የነገረ ክርስቶስ ትምህርት ስለ ኾነ፤ እባክዎት ለብዙዎች እንዲደርስ Share በማድረግ የበኩሎትን ይወጡ፤ በዚህ ቻናል ውስጥም ያላችሁ ተከታተሉት። ያልገባችሁ፣ እንዲብራራ የምትፈልጉት ካለ ንገሩኝ በቀጣይ የማነሣ ይኾናል።
ቃል ሥጋ ሆነ ሲባል እንዴት ነው? የግድ ማወቅ ያለባችሁ ነገሮች!
ተከታታይ የነገረ ክርስቶስ ትምህርት
ክፍል 2
ነገረ ክርስቶስን ለመረዳት የሚጠቅመን ትምህርት በዲ/ን ዮሐንስ ጌታቸው
ሙሉ ቪዲዮውን ሊንኩን በመጫን ዩትዩብ ላይ ማግኘት ትችላላችሁ ።
????????
#በቦሌ_መድኃኔ_ዓለም_በአየር_መንገድ_ሠራተኞች_የተዘጋጀ_ሳምንታዊ_የማግሰኞ_መርሐ_ግብር_ተከታታይ_ትምህርት_በትንሹ_አዳራሽ_ከቀኑ_11፡50 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 1፡00 መጥተው መከታተል ይችላሉ።
እነዚህን ትምህርቶች እየገባችሁ ተከታተሉ፥ ለሌሎች ወንድም እኅቶችም አጋሩት።
የስራ ማስታወቂያ ከጋዜጣ ፣ ከቲቪና ራዲዮ ፣ ከማስታወቂያ ቦርድ ፣ ከድህረ-ገፅና ከማህበራዊ ሚዲያና ከመሳሰሉት ቦታዎች በአንድ ቦታ ተሰብስበው ያግኙ::
#Group t.me//Ethio_Jobs2000
#የመዝናኛ ቻናል https://t.me/+UPjrnHF6QzI0ZmQ0
https://t.me/+h0l2XzeI8RQyODlk
For promotion ? @Share_Home
Last updated 1 month, 2 weeks ago
ከቅዳሜ በስተቀር በየዕለቱ፣ ከሰኞ እስከ ዓርብ ረፋድ ከ3:30 እስከ 5:00፣ እሁድ ከጠዋቱ 2:00 እስከ 4:00 በብስራት ኤፍ ኤም 101.1
Last updated 7 months, 4 weeks ago
Certified Professional Life Coaches
የቻናላችንን አነቃቂ ቪዲዮ መመልከት ለምትፈልጉ
https://www.youtube.com/@inspireethiopiamedia ? ይሄንን ሊንክ ይጫኑ
Last updated 9 months, 4 weeks ago