★ሰውን በማዝናናት የብቃት ማረጋገጫ ያለው ብቸኛው ቻናል ሁሌም Telegram ላይ በጥበብ ደምቀን እናሸበርቃለን
💌 Contact us, @Modenyazbot
»የተመረጡ እና ማንም ያላያቸው የአማሪኛ ቀልዶች እንዲሁም የሚያስደንቁ ስዕሎችንና ቪዲዮ ያገኛሉ።
° ° [ ሙድ እንያዝ በእኛ የአራዶች መዝናኛ ] ° °
° ° Creator @Teke_Man ° °
Last updated 1 month, 3 weeks ago
እንኳን ወደ # ሉሲ የቴሌግራም ቻናል በደህና መጡ
#የሉሲ /LUCY DINKINESH E/ቤተሰብ ሰለሆኑ ደስብሎናል።
መረጃ መስጠት የምትፈልጉ በዚ አድርሱን 👉 @CACA77
# የኢትዬጵያዊነት የአሸናፊነት መገለጫ አርማችን ነው!
ነፃነታችንን 💪በፈርጣማው ጡንቻችን ይረጋገጣል
👉 ኢትዬጵያዊነት አርበኝነት የማንነት አርማች ነው
🙏🙏🙏
Last updated 3 weeks, 4 days ago
በዚህ ቻናል
⚡ህይወትን የሚያንፁ የስነ-ልቦና ምክሮች
⚡መሳጭ የፍቅር ታሪኮች እና ወጎች
⚡ጥልቅ ማህበራዊ እና ፍልስፍናዊ እይታዎች
⚡ውብ የጥበብ ስራዎች
በፅሁፍ እና በድምፅ/Audio ይቀርባሉ።
#ሼር በማድረግ ወዶጅዎን የዚህ የእውቀት እና የጥበብ ድግስ ታዳሚ እንዲሆኑ ይጋብዙ።
Last updated 9 months, 3 weeks ago
Your name gives me
Your name gives me
The strength to climb up mountain
I have passed through the snare
With your intercession
Holy virgin Mary
I’ve broken free through
your mediation
Above all creation
he has filled you with grace
His son born from your womb
Your flesh He has embraced
The vessel for the world
to be saved Yes it’s true
holiest of holies virgin
Mary it’s you
I will pass through the storm
With my support Mary
My weakness will vanish
Under the shade you bring
Without you we could not
Have received medicine
The heavenly manna through
You we were given
The father of David praise to the creator
Blessings have filled my home
Through the interceder
Those who draw near to you
In body and spirit
The heavenly reward from Him they’ll inherit
So that my soul be filled
And I may not hunger
From your abundant well
Nourish me my mother
By entering your home
Finally, I’m at peace
My clothes have been made new
From the stain I’m released
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯
በዚህ ሊንክ ግቡ ጀምሯል
👇
https://t.me/dnzema?livestream
አንዳንድ ነጥቦች በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ ሀገራቸው እንዳይገቡ መከልከል ዙሪያ፦
1. ለዚህ አሳዛኝ ድርጊት የተቀነባበረ ሽፋን በቅርብ ሲሰጥ እንደምንሰማ የታወቀ ነው። በመንግሥት አካላት ተደርሶ የሚቀርበው ድራማና ዶክመንተሪ አያልቅምና ያልሠሩትን ወንጀል ሲያሸክሟቸውና ሲያጥላሉዋቸው እንሰማ ይሆናል። ስለዚህም ከሚዲያ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ልሳን የሆኑ ሚዲያዎችን ብቻ እንከታተል።
2. መንግሥት ይህን መሰል አንገት ሰባሪና ድፍረት የተሞላበት ድርጊት ሲፈፅምም ብፁዕነታቸው ያሉበትን ኃላፊነት ከግምት አላስገባም። ክብራቸውን የሚወክሉትን ቤተ ክርስቲያንና ሕዝባቸውን አላከበረም። በዚህ ጸያፍ ድርጊቱ እርሳቸውን ብቻ ሳይሆን መላውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አማኝን እንዳሳዘነ መታወቅ አለበት።
3. ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ፓትርያርኩን ሸክም ጎንበስ ብለው የሚሸከሙ አባት ናቸው። የዛሬው የመንግስት ድርጊት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስን ከሜዳው በማግለል የቅዱስ ሲኖዶስን ማዕከላዊነት የመናድ ሙከራ ነው።
4. ብፁዕነታቸው በእምነታቸው የማይደራደሩ ታላቅ አባት ሲሆኑ እርሳቸውን ወደ ሀገራቸው እንዳይገቡ የማድረግ ርምጃ የቤተ ክርስቲያንን በር የበግ ለምድ ለለበሱ ተኩላዎችና ለእንደ ልቡዎች ክፍት የማድረግ ዕቅድ አካል ነው። ከዚያም ውጪ ሌሎች ውጪ የሚኖሩ አበው ብፁዓን አባቶችንም አፍ የማስያዣ አካሄድ ነው።
5. በሌላ በኩል በውጪ ያሉ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ቁጣቸውን ማሳደር አለባቸው። ምክንያቱም መንግሥትም ሆነ ሕገ ወጥ አካላት በተለያዩ ሚዲያዎች በኩል ይህን ነገር እያራገቡ ጫና ፈጥረው ሌላ ሲኖዶስ እናቋቁም የሚል ሀሳብ እንዲፈጠር መሥራታቸው አይቀርምና በዚህ በኩል ረጋ ብሎ መጠንቀቅ ተገቢ ነው። ተተኪ ጸሐፊ ይመረጥ የሚል ሤራ እንዳይሸርብም ነቅቶ መጠበቅና መሥመር ማስያዝ እንደሚገባው ሳይረሳ!!
6. ይህ ድርጊት ቤተ ክርስቲያንን ለመከፋፈል የታሰበ እቅድ ነው። ስለዚህም እንደ ምእመን በበለጠ የቤተ ክርስቲያን አንድነት ላይ ማተኮርና ቤተ ክርስቲያናችንን በንቃት መጠበቅ አለብን።
7. ይሄ ጉዳይ መሥመር እንዲይዝ የሚያደርጉ አባቶችን በሚያስፈልጋቸው ሁሉ ማገዝና ትዕዛዛቸውንም እንደ ልጅ መፈጸምም ይገባናል።
ልዑል እግዚአብሔር ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ይጠብቅልን
#ኢንፈርህሞተ
#ሞትንአንፈራውም
ብርሃኑ ተ/ያሬድ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአሜሪካ የነበራቸውን ሐዋርያዊ አገልግሎት ጨርሰው ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ እንዳይገቡ መከልከላቸው ተሰምቷል።
ብፁዕነታቸው ከሳምንታት በፊት በቋሚ ሲኖዶስ እውቅና ወደ ሀገረ ስብከታቸው በመሄድ የአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ ዓመታዊ በዓል፣ የከተራና የጥምቀት በዓላትን ከመንፈስ ልጆቻቸው ጋር ያከበሩ ሲሆን ለአዳጊ ሕጻናትም ማዕረገ ዲቁና መስጠታቸው ይታወቃል።
ወደ ሀገር እንዳይገቡ የተከለከሉት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ አሁን ወደ አሜሪካ ተመለሡ።
ንስሐ ለተጠመቁ ሰዎች ከጥምቀት በኋላ የተሰጠች ሀብት ናት፡፡ ይህንንም የሚያስረዳ ነገር በጥምቀት ከእግዚአብሔር ከምትገኝ ልጅነት ሁለተኛ ማዕረግ ናት፡፡ በሃይማኖት ገንዘብ ያደረግነው የመንግስተ ሰማይ መያዣ ከናት፡፡
በንስሐ ምክንያት የእግዚአብሔርን ቸርነት እናገኛለን፡፡ ንስሐ ለሚሿት ሰዎች የተከፈተች የይቅርታ በር ናት፡፡ በንስሐ በርነት ከፈጣሪ ወደሚገኝ ቸርነት እንቀርባለን፡፡ መከላከያ ከሚሆን ከንስሐ ርቀን ይቅርታን አናገኝም፡፡
አምላክ የጻፈው መጽሐፍ እንደተናገረ ሁላችን በድለናልና ያለ ዋጋ በይቅርታው ከኃጢአት እንነጻለን፡፡ ንስሐ እግዚአብሔርን በመፍራት፣ በሃይማኖትና በልቡና የምትገኝ ሁለተኛ ጸጋ ናት፡፡ ሀብታተ ምስጢራት ከሚገኙበት ከመንፈሳዊ ፍቅር እስክንደርስ ድረስ የሚጠብቀን መንፈሳዊ ዕውቀት ነው፡፡
(ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ)
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯
ጌታ ሆይ ከቻናላችን #ሌፍት እሚሉትን ልቦና እና ቀልብ ስጥልኝ🙄😉
#ስለምን_ወደ_ዮሐንስ_ሔዶ_ተጠመቀ
ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዮሐንስን መጥተህ አጥምቀኝ ቢለው ኑሮ ዛሬ የዚህ አለም ነገስታቱና መኳንንቱ፣ ባለሀብቱና ባለሥልጣናቱ በጊዜው ታላቅ ነኝ ብሎ የሚያስበው ሁሉ ካህናቱን መጥታችሁ አጥምቁን (አጥምቁልን) እየሉ ይጠሯቸው ነበር። ስለዚህ ዓርአያ ለመሆን ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ወደ ዮሐንስ ሔዶ ተጠመቀ።
*8️⃣#ጌታችን_ጥምቀቱን_በዮርዳኖስ_ያደረገው
✅***ለዮርዳኖስ የተነገረዉን ትንቢት ለመፈጸም በዮርዳኖስ ተጠመቅ፡፡ መዝ 113፥3-7
✅ምሳሌዉን አማናዊ ለማድረግ፤ ዮርዳኖስ ምነጩ አንድ ነዉ፤ ዝቅ ብሎ ግን በደሴት ይከፈላል፤ ከታች ወርዶ ይገናኛል፡፡ ዮርዳኖስ ከላይ ምንጩ አንድ እንደሆነ የሰዉ ሁሉ ምንጩ አንድ አዳም መሆኑን፤ ዝቅ ብሎ በደሴት መከፈሉ እስራኤል በግዝርት አህዛብ በቁልፋት የመለየታቸዉ፣ ከታች ወርዶ መገናኘቱ እና ጌታችን መዳህኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመገናኛዉ ላይ መጠመቁ ሕዝብና አሕዛብን በጥምቀት አንድ ሊያደርግ መምጣቱን ያጠይቃል፡፡
✅እንዲሁም አባታችን እዮብ የአዳም ምሳሌ ነዉ፤ ደዌዉ የመርገመ ስጋ የመርገመ ነፍስ ምሳል ነዉ፡፡ ዮርዳኖስ የጥምቀት ምሳሌ ነዉ፡፡ የአዳም ዘር ከማህጸነ ዮርዳኖስ በጥምቀት ዳግም ተወለዶ ከመርገመ ስጋ ከመርገመ ነፍስ ይላቀቃል ብሎ በዮርዳኖስ ተጠመቀ፡፡ ኢዮ 12፥10
✅ኤልያስ ዮርዳኖስን ተሻግሮ ወደ ብሄረ ሕያዋን አርጓል ፡፡ ምእመናንም አምነው ተጠምቀው ገነት መንግስተ ሰማያት የመግባታቸውን ምሳሌ ለማስረዳት አምላካችን በዮርዳኖስ ተጠመቀ፡፡ 2ነገ 2፥8-14
✅የእዳ ደብዳቤያችንን ይደመስስልን ዘንድ፦ ዲያብሎስ የጨለማ መጋረጃ ጋርዶ በአባታችን አዳም እና በእናታችን ሔዋን ስቃይ መከራን አበዛባቸዉ፡፡ "ስመ ብኩርናችሁን ጽፋችሁ ብትሰጡኝ ፍዳዉን አቀልላችሁ አለሁ" አላቸዉ፡፡
እነሱም ስቃዩና መከራዉ ሚቀልላቸዉ መስሎአቸዉ "አዳም ግብሩ ለዲያብሎስ ሔዋን ዓመቱ ለዲያብሎስ (አዳም የዲያብሎስ ባሪያ ሔዋን የዲያብሎስ ገረድ" ብለዉ ጽፈዉ ሰጡት፡፡ እሱም በሁለት ገጽ አድርጎ አንዱን በሲኦል አንዱን በዮርዳኖስ አስቀመጠዉ፡፡ ከአምላካችን የሚሰወር ነገር የለምና በዮርዳኖስ የጣለዉን ጌታችን በጥምቀቱ ጊዜ እንደ ሰዉነቱ እረግጦ እንደ አምላክነቱ አቅልጦ ለማጥፋት ሲል በዮርዳኖስ ተጠመቀ፡፡ ቆላ 2፥14
በሲኦል ያስቀመጠዉን ጌታችን በእለተ አርብ በአካለ ነፍስ ወርዶ ነፍሳትን ሲያወጣ በመለኮታዊ ጥበብ አጥፍቶላቸዋል፡፡#ጌታችን_ለምን_በውሃ_ተጠመቀ?*
✅*ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ሲሆን ጥምቀቱን በማርና በወተት በሌሎችም በክብር ላቅ ባሉ ፈሳሽ ነገሮች ያላደረገው ለምንድነው ብለን ብንጠይቅ ምሥጢሩ አስገራሚ ነው።
✅ጌታችን ያኔ በማር ወይም በወተት ተጠምቆ ቢሆን ኖሮ እኛም እንዲሁ ማድረጋችን አይቀርልንም ነበር። እናም ለሁሉ መስጠቱን ለማሳወቅ እና ሁሉም በማንኛውም ስፍራ በሚያገኘው በውኃ ተጠምቆልናል።
✅ሰዎች ውሃ ለመዓት እንጅ ለምሕረት አልተፈጠረም ይሉ ነበርና ለምሕረት እንደተፈጠረና ሰው በረሱ ኃጢያት እንደሚጠፋ ለማሳወቅ በውሃ ተጠምቋል።
✅ውሃ በአትክልት ላይ ቢያፈሱት ያለመልማል እናንተም በውሃ ብትጠመቁ ልምላሜ ሥጋና ልምላሜ ነፍስን ታገኛላችሁ ሲል ነው።
✅ውሃ እድፍን ያነፃል በውሃ ስንጠመቅም ከኃጢአት እንነጻለን እንቀደሳለን።
✅ውሃ እሳትን ያጠፋል እናንተም ብትጠመቁ ከጋሃነመ እሳት ትድናላችሁ ሲል ነው። ውሃ የሕይወት ምልክት ነው። መዝ 1፥3 ፤ ራዕ 22፥1
✅ከወተትና ከማር ዉሃ መልክን ያሳያል እናንተም በውሃ ተጠምቃችሁ በዕለተ ምጽአት መልክዐ ሥላሴን ታያላችሁ ሲለን ነው።
🔟#ጥምቀት_አንዲት_ናት
ጥምቀት በወራጅ ውሃ ብትፈጸም፤ በገንዳ ውሃ ብትፈጸም፣ በሊቀ ጳጳስ፣ በኤጴስ ቆጶስ፣ በቄስ እጅ ብትደረግ አንዲት ናት ኤፌ 4፥5
ጥምቀት የማይደገምበት አንድ ብቻ የሆነበት ምክንያት፦
◾️ከሥጋዊ ወላጆቻችን በስጋ የምንወለደው አንድ ጊዜ ብቻ እንደሆነ ሁሉ ከመንፈሳዊ አባታችን የምንወለደው መንፈሳዊ ልደታችንም አንድ ጊዜ ብቻ ስለሆና ስለማይደገም ዮሐ 3፥6-8
◾️የጥምቀት ምሳሌ የሆነው ግዝረት አንድ ጊዜ ብቻ እንደሚፈጸም ጥምቀትም አንድ ጊዜ ብቻ ይፈጸማል። ቆላ 2፥11-13
◾️ከጌታ ሞትና ተንሣኤ ተሳታፊ የምንሆንበት ምሥጢር በመሆኑ ጌታም የሞተውና የተነሳው አንድ ጊዜ ብቻ ነውና። ቆላ 2፥12 ፤ ሮሜ 6፥3-4
~~~~~~
ቀጣይ ትምህርታችን
የምሥጢ~~ረ ጥምቀት ትምህርት ማጠቃለያ
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯
ሰላም የክርስቶስ ቤተሰቦች የኪዳነምህረት የስጦታ ልጆች🙏 #ዛሬ_ማታ ጥምቀት 👇 መቼ❓ በማን ❓ እንዴት ❓ ተመሰረ፣ በሚል ርዕስ፣ እንማማራለን እስከዛ ተወያዩበት።
★ሰውን በማዝናናት የብቃት ማረጋገጫ ያለው ብቸኛው ቻናል ሁሌም Telegram ላይ በጥበብ ደምቀን እናሸበርቃለን
💌 Contact us, @Modenyazbot
»የተመረጡ እና ማንም ያላያቸው የአማሪኛ ቀልዶች እንዲሁም የሚያስደንቁ ስዕሎችንና ቪዲዮ ያገኛሉ።
° ° [ ሙድ እንያዝ በእኛ የአራዶች መዝናኛ ] ° °
° ° Creator @Teke_Man ° °
Last updated 1 month, 3 weeks ago
እንኳን ወደ # ሉሲ የቴሌግራም ቻናል በደህና መጡ
#የሉሲ /LUCY DINKINESH E/ቤተሰብ ሰለሆኑ ደስብሎናል።
መረጃ መስጠት የምትፈልጉ በዚ አድርሱን 👉 @CACA77
# የኢትዬጵያዊነት የአሸናፊነት መገለጫ አርማችን ነው!
ነፃነታችንን 💪በፈርጣማው ጡንቻችን ይረጋገጣል
👉 ኢትዬጵያዊነት አርበኝነት የማንነት አርማች ነው
🙏🙏🙏
Last updated 3 weeks, 4 days ago
በዚህ ቻናል
⚡ህይወትን የሚያንፁ የስነ-ልቦና ምክሮች
⚡መሳጭ የፍቅር ታሪኮች እና ወጎች
⚡ጥልቅ ማህበራዊ እና ፍልስፍናዊ እይታዎች
⚡ውብ የጥበብ ስራዎች
በፅሁፍ እና በድምፅ/Audio ይቀርባሉ።
#ሼር በማድረግ ወዶጅዎን የዚህ የእውቀት እና የጥበብ ድግስ ታዳሚ እንዲሆኑ ይጋብዙ።
Last updated 9 months, 3 weeks ago