Unlock a World of Free Content: Books, Music, Videos & More Await!

Sheger Press️️

Description
Official channel of sheger press

If you want to give a suggestion or comment, contact us 👉 @birukepromo
Advertising
We recommend to visit

🌐 https://ipapkorn.github.io
Stay connected with the latest iPapkorn Bots and News 🗞️

Bots: https://t.me/iPapkornBots/2

Last updated 4 months, 2 weeks ago

Breaking News | Observing world events unfold in the grand theater of our time.

Last updated 2 weeks, 5 days ago

Freedom over censorship, truth over narrative. Question more!

Last updated 2 years, 2 months ago

2 days, 5 hours ago
Sheger Press️️
2 days, 5 hours ago
Sheger Press️️
3 days, 3 hours ago

በሰሜን ሸዋ ዞን በሁለት ወረዳዎች በተመሳሳይ ቀን በደረሰ የድሮን ጥቃት የበርካታ ሰላማዊ ሠዎች ሕይወት አለፈ!!

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቀወት ወረዳ ተሬ ቀበሌ ጉሎ በተባለ ትምህርት ቤት እና ሞላሌ ወረዳ እሁድ ግንቦት 4፤ 2016 ዓ.ም. በደረሰ የድሮን ጥቃት ከአስር በላይ ሠላማዊ ሰዎች መገደላቸውንና መቁሰላቸውን ተገለጸ።

ከቀወት ወረዳ ዋና መቀመጫ ሸዋሮቢት በግምት 20 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በሚገኘው የጉሎ (ጎጥ) አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከቀኑ 7፡30 ገደማ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት አራት ሠዎች ሲገደሉ አምስት ሠዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የዐይን እማኞችና የተጎጂ ቤተሰቦችን ዋቢ በማድረግ ቢቢሲ ዘግቧል።

ዶይቼ ቬለ የዜና ወኪል በቀዎት ወረዳ እና ሞላሌ ወረዳዎች በዕለቱ ተፈጸመ በተባለ የሰውአልባ ድሮን ጥቃት 14 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን እና በርካቶች መቁሰላቸውን ዘግቧል።

በትምህርት ቤቱ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት መምህራንና የአካባቢው ማሕበረሰብ የወላጅ መምህራን ህብረት (ወመህ) ስብሰባ ላይ በነበሩበት ቅጽበት መሆኑን ለቢቢሲ የተናገሩ አንድ የስብሰባው ተካፋይ፤ በጥቃቱ እሳቸውም ጭንቅላታቸው ላይ እንደቆሰሉ ገልጸዋል።

ከሟቾቹ ውስጥ ሁለቱ የስብሰባው ተሳታፊዎች ሲሆኑ፤ ሁለቱ ደግሞ የት/ቤቱ ዙሪያ ላይ የነበሩ ሠላማዊ ሠዎች እንደሆኑ ቢቢሲ ያነጋገራቸው ሌላ የአይን እማኝ ተናግረዋል።

የፍንዳታ ድምጽ ሰምተው ወደ አካባቢው በፍጥነት እንዳመሩ የተናገሩ አንድ የዐይን እማኝ እንደደረሱ አስከሬን ማየታቸውን ጠቅሰው፤ የአራት ሠዎች ሕይወት ማለፉንና በርካታ ሠዎች መቁሰላቸውን ተናግረዋል።

ተመሳሳይ ዞን በሞላሌ ወረዳ መዘዞ ተብላ በምትጠራው ከተማ አጠገብ በተጣለ ሌላው የድሮን ጥቃት ሶስት የፋኖ አባላት እና በመጠጥ ሽያጭ ላይ የተሰማራች አንድ ሴት ጨምሮ አራት ያልታጠቁ ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን ዶይቸ ቼለ ዘግቧል።

@sheger_press
@sheger_press

3 days, 7 hours ago

መንግሥት የመንግሥት ሠራተኞች ቅጥርና ምደባ የአገሪቱን ብሄረሰቦች ብዝኀነትና የጾታና የአካል ጉዳተኞችን ተዋጽዖ የጠበቀ እንዲኾን የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል።

ምክር ቤቱ፣ በረቂቅ አዋጁ ላይ ትናንት ተወያይቷል። ረቂቅ አዋጁ፣ በመንግሥት ሠራተኞች ደሞዝ ጭማሪ፣ ደሞዝ እርከን፣ ክፍያና ጥቅማጥቅሞች ላይ ማሻሻያ እንዳደረገም ተገልጧል።

የአነሳ ብሄረሰቦችና የማኅበረሰብ ክፍሎች በመንግሥት መስሪያ ቤቶች በቅጥር፣ ምደባ፣ ዝውውር፣ በሥራ ደረጃ እድገት፣ በትምህርትና ሥልጠና ረገድ ተጨማሪ መንግሥታዊ ድጋፍ እንዲደረግላቸውም ረቂቅ አዋጁ ይደነግጋል። ምክር ቤቱ፣ ረቂቅ አዋጁን ጉዳዩ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል።

@sheger_press
@sheger_press

3 days, 7 hours ago

ማስታወቂያ

Old telegram groups መሸጥ ለምትፈልጉ‼️

Old telegram ግሩፖች ያላችሁ
(በ2022 እና ከዛ በታች ባለው አመተ ምህረት የተከፈቱ ግሩፓች)  የGroup ሜምበር ብዛት አያስፈልግም የGroup ሜምበር 1 ሰው ቢሆንም በተመጣጣኝ ዋጋ እየገዛን ነው።  ግን የተከፈተበት አመተ ምህረቱን ነው የምፈልገው  ቢያንስ አንድ አመት የቆየ መሆን አለበት።

ቢያንስ አንድ አመት የቆየ እና ትንሽ ሜምበር ያለው ግሩፕ (ከ1 ሜምበር ጀምሮም ይቻላል) ያላችሁ ሰዎች እና መሸጥ የምትፈልጉ

👍በተመጣጣኝ ዋጋ እየገዛን እንገኛለን።

📌የተከፈተበት አመተ ምህረት ከጨመረ ጥሩ ተጠቃሚ ይሆነሉ

ማንም መሸጥ የሚፈልጉ የዋጋ ዝርዝር 👇

2018 = 500 birr
2019 = 400 birr
2020 = 300 birr
2021 = 250 birr
2022 = 200 birr

ለመሸጥ ምትፈልጉ @sorithefirst
ወይም በ 0928232227 መደወል ይችላሉ

For more information join
https://t.me/old_group_buyerchannel

3 days, 19 hours ago
NewsUpdate***‼️***

NewsUpdate‼️

በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመር በኢትዮጵያ ወቅታዊ የጸጥታና ፖለቲካዊ ኹኔታ ዙሪያ ከኦነግ ሊቀመንበር ዳውድ ኢብሳ እና ከኦፌኮ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ጋር ትናንት አሜሪካ ኢምባሲ ውስጥ ተወያይተዋል።

ኦነግ፣ ሐመር እና ዳውድ "ሰፋ ያለ ውይይት" ማድረጋቸውንና ዳውድ ኦነግ ለዓመታት ያለፈባቸውን አስቸጋሪ የፖለቲካ ኹኔታዎች ለሐመር እንዳብራሩላቸው ገልጧል።

ዳውድ የአገሪቱን ችግሮች ለመቅረፍ፣ ለዓመታት ከሕግ ውጭ የታሠሩ የኦነግ አመራሮችን "ባስቸኳይና ያለምንም ቅድመ ኹኔታ" መፍታት፣ “የተዘጉ የኦነግ ጽሕፈት ቤቶች መክፈት" እና "በመላው አገሪቱ ታስረው የሚገኙ የፖለቲካ እስረኞችን ኹሉ መፍታት" እንደሚያስፈልግ ሃሳብ ማቅረባቸውን ግንባሩ ጠውሷል።

ሐመር በበኩላቸው፣ በኢትዮጵያ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ አሜሪካ ጥረት እንደምታደርግ ለዳውድ ነግረዋቸዋል ተብሏል። [ዋዜማ]

@sheger_press
@sheger_press

4 days, 20 hours ago

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ  አስተዳደር በራያ ወረዳዎች መሠረታዊ የሕዝብ አገልግሎቶችን ለማስጀመር ከፌደራል መንግሥቱ ጋር እየተወያየ እንደኾነ ለዋዜማ ተናግሯል።

በአካባቢዎቹ የመንግሥት ተቋማት እንደተዘጉና መደበኛ እንቅስቃሴዎች ባብዛኛው መስተጓጎላቸውን ዋዜማ ከነዋሪዎች አረጋግጣለች።

ከአካባቢው የተፈናቀለ ነዋሪ የለም ሲሉ ያስተባበሉት የደቡብ ትግራይ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ሃፍቱ ኪሮስ፣ በፈረሱት አስተዳደራዊ መዋቅሮች ውስጥ ይሠሩ የነበሩ አመራሮችና ሠራተኞች ግን ተፈናቅለው ሊኾን ይችላል ብለዋል።

የተባበሩት መንግሥት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ ግን፣ በቅርቡ በትግራይ ኃይሎችና በአማራ ታጣቂዎች መካከል በተፈጠረው ግጭት ሳቢያ ከራያ አከባቢዎች ከ36 ሺህ በላይ ሰዎች መፈናቀላቸውን አስታውቆ ነበር።

ዋና አስተዳዳሪው፣ ከጦርነቱ በፊት በመንግሥታዊ መዋቅሮች ተመድበው ይሠሩ የነበሩ ሠራተኞች ወደ ሥራ እንዲመለሱ እየተደረገ መኾኑን ገልጸዋል።

@sheger_press
@sheger_press

4 days, 21 hours ago
በእነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው መዝገብ፤ የቃሊቲ …

በእነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው መዝገብ፤ የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ኃላፊ ለፍርድ ቤት ማብራሪያ እንዲሰጡ ታዘዙ‼️

በእነ አቶ ዮሐንስ ቧያሌው መዝገብ የእስረኞችን አያያዝ በተመለከተ የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ኃላፊ ፍርድ ቤት ቀርበው ማብራሪያ እንዲሰጡ በፍርድ ቤት ታዘዘ።

አቶ ክርስቲያን ታደለ “ለቀናት” ምግብ አለመመገባቸውን ለፍርድ ቤቱ ዛሬ በዋለው ችሎት ገልጸዋል። ምግብ ያልተመገቡት፤ በማረሚያ ቤቱ “ #አማራ ተከሳሾች ስለሆናችሁ እንደሌሎቹ ተከሳሾች አትስተናገዱም” በሚል የቤተሰብ ጥየቃ ሰዓት ላይ ለውጥ በመደረጉ መሆኑን ለችሎቱ አስረድተዋል።

ዶ/ር ካሳ ተሻገርም በተመሳሳይ፤ “ የቀጠሮ እስረኞች ሆነን እያለ ነገር ግን ከፍርደኞች ጋር እንድንታሰር አድርጎናል” ሲሉ አቤቱታቸውን ለችሎቱ በቃል መግለጻቸውን ጠበቃቸው ሄኖክ አክሊሉ ለቢቢሲ ገልጸዋል።

ዶ/ር ካሳ “መንግሥት አላግባብ በተለያየ ሚዲያ ከሰራው ዘገባ ጋር በተገናኘ ፍርደኞች እኛ ላይ ዛቻ እና ማስፈራራት አድርሰውብናል” ማለታቸውን ሄኖክ ጠቅሰዋል።

በተከሳሾቹ የቀረቡ ሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተመለከተ የ #ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መርምሮ አጣርቶ ውጤቱን ለፍርድ ቤቱ እንዲያሳውቅ ችሎት ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ከዚህ በተጨማሪም ተከሳሾች “ማረሚያ ቤቱ ከማንነታችን ጋር በተያያዘ በምሳ ሰዓት ብቻ እንድንጠየቅ ተደረግን” በሚል ላቀረቡት አቤቱታ ማረሚያ ቤቱ ምላሽ እንዲሰጥ እና የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ኃላፊ በአካል ቀርበው እንዲያስረዱ መታዘዙንም ጠበቃ ሄኖክ አስረድተዋል።

@sheger_press
@sheger_press

5 days, 2 hours ago
Update

Update

ከሐዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረዉ አዉሮፕላን ዉስጥ ታይቷል የተባለዉ ጭስ በዉስጡ ያለዉ ዘይት በመቃጠሉ የተነሳ መሆኑ ተገለፀ!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሰሞኑ በአዉሮፕላኑ ላይ የተከሰተው ጉዳይን አስመለክቶ እንዳስታወቀው ከእሳት ወይም ከሌላ ነገር ጋር የተያያዘ ሳይሆን አዉሮፕላን ዉስጥ ያለዉ ዘይት ተቃጥሎ ነዉ በወቅቱ የተከሰተው ጭስ ሊፈጠር የቻለዉ ይህም አልፎ አልፎ የሚያጋጥም ችግር ነዉ ብሏል።

የአየር መንገዱ ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰዉ በተለይ ለካፒታል እንደተናገሩት " በአዉሮፕላኑ ዉስጥ ያለዉ ዘይት መጋጠሉ እና ከእርሱ ጋር ተያይዞ የተፈጠረ ጭስ ነዉ ይህ ደግሞ የተለመደ ነዉ ብለዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ET154 ሚያዝያ 29፣ 2016 ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ እያለ በአውሮፕላን ውስጥ ጭስ መታየቱን አስታዉቆ እንደነበር ይታወቃል።
( via Capital)

@sheger_press
@sheger_press

5 days, 8 hours ago

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ፣ በአማራ ክልል ነፍጥ ያነሱ ታጣቂ ኃይሎች ወደ ሰላማዊ ሕይወት እንዲመለሱ ትናንት በባሕርዳር ተገኝተው በአዲሱ የአባይ ድልድይ ምረቃ ላይ ባደረጉት ንግግር ጥሪ አቅርበዋል።

ዐቢይ በዚኹ ንግግራቸው፣ "በማይገባ ነገር መገዳደል ይብቃ” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።

ጠቅላይ ሚንስትሩ፣ ታጣቂ ኃይሎች ወደ ሰላም ተመልሰው ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ ጋር ከሠሩ፣ ፌደራል መንግሥቱም የራሱን ትብብር ለማድረግ ዝግጁ እንደኾነ ገልጸዋል።

@sheger_press
@sheger_press

We recommend to visit

🌐 https://ipapkorn.github.io
Stay connected with the latest iPapkorn Bots and News 🗞️

Bots: https://t.me/iPapkornBots/2

Last updated 4 months, 2 weeks ago

Breaking News | Observing world events unfold in the grand theater of our time.

Last updated 2 weeks, 5 days ago

Freedom over censorship, truth over narrative. Question more!

Last updated 2 years, 2 months ago